Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Revelations
Senior Member+
Posts: 33735
Joined: 06 Jan 2007, 15:44

የሶማሌ ክልል የቀድሞ ፕሬዚዳንትን ለማስለቀቅ አሲረዋል የተባሉ በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ተሰማ

Post by Revelations » 07 Aug 2019, 08:21

Please wait, video is loading...

Revelations
Senior Member+
Posts: 33735
Joined: 06 Jan 2007, 15:44

Re: የሶማሌ ክልል የቀድሞ ፕሬዚዳንትን ለማስለቀቅ አሲረዋል የተባሉ በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ተሰማ

Post by Revelations » 07 Aug 2019, 08:39

7 August 2019
ታምሩ ጽጌ

ከሐምሌ 26 እስከ 30 ቀን 2010 ዓ.ም. በሶማሌ ክልል በጅግጅጋ ከተማና ሌሎች ከተሞች ላይ በተፈጸመ ግድያ፣ አካል ማጉደል፣ ማፈናቀል፣ አብያተ ክርስቲያናትና የንግድ ተቋማትን በማቃጠል ምክንያት ክስ የተመሠረተባቸውን የሶማሌ ክልል የቀድሞ ፕሬዚዳንትን ለማስለቀቅ ሴራ አቀነባብረው የነበሩ ግለሰቦች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን የሪፖርተር ምንጮች ገለጹ፡፡

ድርጊቱ ሊፈጸም የነበረው ሰኞ ሐምሌ 29 ቀን 2011 ዓ.ም. ሲሆን፣ ተከሳሹ የቀድሞ ሶማሌ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አብዲ መሐመድ ዑመር በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራተኛ ወንጀል ችሎት የነበራቸውን ቀጠሮ ጨርሰው ወደ ማረሚያ ቤት ሲሄዱ እንደነበር ምንጮች ገልጸዋል፡፡

ቃሊቲ ማረሚያ ቤት መግቢያ አካባቢ መኪና አዘጋጅተው ነበር የተባሉት ማንነታቸው ያልታወቁ ግለሰቦች የተከሳሹን መምጣት በመጠባበቅ ላይ እያሉ፣ ያቆሙትን መኪና ከማረሚያ ቤቱ አካባቢ እንዲያነሱ በትራፊክ ፖሊስ ሲጠየቁ ‹‹አናነሳም›› የሚል ምላሽ መስጠታቸውንም ምንጮች አስረድተዋል፡፡

በዚህ ጊዜ የቆመው መኪና እንዲፈተሽ ሲጠየቁ በፈጠሩት አታካራ ሳቢያ ተኩስ መለዋወጣቸውንና ከየትኛው ወገን እንደሆነ ግልጽ ባይሆንም፣ አንድ ሰው መመታቱን ምንጮች ገልጸዋል፡፡ ከግለሰቦቹ መካከል የተወሰኑት ሲያመልጡ አንዲት ሴትን ጨምሮ አብዛኞቹ በቁጥጥር ሥር ውለው በምርመራ ላይ መሆናቸውንም ምንጮቹ ጠቁመዋል፡፡

ግለሰቦቹ በማረሚያ ቤቱ አቅራቢያ ቤት ተከራይተው እንደነበርና በርካታ የጦር መሣሪያዎችም በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ምንጮች አስረድተዋል፡፡

ድርጊቱ በተፈጸመበት ጊዜ ተከሳሹ አቶ አብዲ ከፍርድ ቤት ወደ ማረሚያ ቤት አለመመለሳቸውን ከምንጮች ገለጻ ለመረዳት ተችሏል፡፡

ተፈጽሟል የተባለውን ሙከራ በተመለከተ ማብራሪያ እንዲሰጡ የፌዴራል ማረሚያ ቤቶች ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተርን በተንቀሳቃሽ ስልካቸው ለማግኘት ቢቻልም፣ በኔትወርክ ችግር ምክንያት መነጋገር ባለመቻሉ ሙሉ መረጃውን ማካተት አልተቻለም፡፡



Za-Ilmaknun
Member
Posts: 4080
Joined: 15 Jun 2018, 17:40

Re: የሶማሌ ክልል የቀድሞ ፕሬዚዳንትን ለማስለቀቅ አሲረዋል የተባሉ በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ተሰማ

Post by Za-Ilmaknun » 07 Aug 2019, 14:21

Revelations wrote:
07 Aug 2019, 12:21
This group never fail to twist its own fate to be the Trojan horse of evil actors. The phony prof Gibasso is feeling the adrenaline of the moment for the maximum gratification with the help of TPLF, which intern is trying to ride the OLF horse for the game that it certainly is sure to score the final goal. The very first step of the play by TPLF is releasing this video that would feed in to the already established though that the duo is working together. The tolerance by the power at the palace of the hate speech by the Gibasso guy coupled with such secret meetings, could as well be interpreted by the dark world of conspiracy as the prof might be acting as a go between. :mrgreen:


Post Reply