Re: የዘመናችን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቀውስ
Posted: 01 Sep 2019, 00:36
በኢትዮጵያ የጎሳ ፌዴሬሽን መፍጠር አይቻልም
በጎሳ ፌዴሬሽን ወስጥ መተማመን በፍጹም ሊኖር አይችልም። በኢትዮጵያ ውስጥ ፌዴሬሽን የሚለው ቃልና ጽንሰ ሃሳብ ምናልባት ከ60 አመታት በላይ እድሜ አለው፤ ከኤርትራ ፌዴሬሽን እንኳ ብንጀርምር። በአሁን ሰአት በየቀኑ ይህን ቃል ሳንሰማ አንውልም። ነገር ግን አንድም ቦታ ስለዚህ ቃል ሆነ ስንጸ ሃሳብ እውነተኛ ትርጉም ሲጠቀስ ስምቼ አላውቅም ።
ፌዴሬሽን ምን ማለት ነው? የቃሉ ስረ ምንጭስ ምንድን ነው? ለመሆኑ የጎሳ ፌዴሬሽን በእውን በተግባር ሊኖር ይችላልን?
ፈደረ ማለት አመነ ማለት ነው፤ ማለትም ፈደርነት እምነት፣ ኪዳን፣ ማመን፣ አንድን ነገር እንደ እውነት መቀበል፣ አንድን ነገር ማተለቅ፣ ማግነን፣ ማክበር ማለት ነው። ሰው ከአምላኩ ጋር ያለው አንድነት በኪዳን፣ በፈደር፣ በእምነት ላይ የተመሰረተ ነው። ማህበርተኞች እቁብ የሚጠጡት በፈደር፣ በእምነት ላይ ተመስርተው ነው። ስለዚህ ያለ እምነት፣ ያለ መተማመን ፌዴሬሽን የሚባል ጽንስ፣ ልምድም ሆነ ንድፈ ሃሳብ በአለም የለም።
ስለሆነም በአላማ፣ በቁጥር፣ በባህል፣ በራእይ ሆነ በፍላጎት የተለያዩ ብቻ ሳይሆን የሚጠርጠሩ፣የሚፎካከሩ፣ የሚጣሉ ጎሳዎች በእምነት፣ በኪዳን በመተማመን ቃል ኪዳን ላይ የተመሰረተ ህብረትም ሆነ መንግስት ሊያቆሙ አይችሉም። ራሱ የፌዴራላዊ ህብረትም ሆነ የጋራ መንግስት ሊያቆሙ የሚችሉት በፈጣሪም ሆነ በሕግ ፊት እኩል የሆኑት የኢትዮጵያ ግለሰቦች ናቸው። በኢትዮጵያ ውስጥ የተፈለገው አይነት ፌዴራሊዝም ሊቆም ሊጽና የሚችለው በኢትዮጵያ ዜጋዎችና በዜጋ ፍልስፍና፣ በዜጋ ፖለቲካ ንድፈ ሃሳብ እና በዜኘት ካልቸር ላይ ነው።
በጎሳ ፌዴሬሽን ወስጥ መተማመን በፍጹም ሊኖር አይችልም። በኢትዮጵያ ውስጥ ፌዴሬሽን የሚለው ቃልና ጽንሰ ሃሳብ ምናልባት ከ60 አመታት በላይ እድሜ አለው፤ ከኤርትራ ፌዴሬሽን እንኳ ብንጀርምር። በአሁን ሰአት በየቀኑ ይህን ቃል ሳንሰማ አንውልም። ነገር ግን አንድም ቦታ ስለዚህ ቃል ሆነ ስንጸ ሃሳብ እውነተኛ ትርጉም ሲጠቀስ ስምቼ አላውቅም ።
ፌዴሬሽን ምን ማለት ነው? የቃሉ ስረ ምንጭስ ምንድን ነው? ለመሆኑ የጎሳ ፌዴሬሽን በእውን በተግባር ሊኖር ይችላልን?
ፈደረ ማለት አመነ ማለት ነው፤ ማለትም ፈደርነት እምነት፣ ኪዳን፣ ማመን፣ አንድን ነገር እንደ እውነት መቀበል፣ አንድን ነገር ማተለቅ፣ ማግነን፣ ማክበር ማለት ነው። ሰው ከአምላኩ ጋር ያለው አንድነት በኪዳን፣ በፈደር፣ በእምነት ላይ የተመሰረተ ነው። ማህበርተኞች እቁብ የሚጠጡት በፈደር፣ በእምነት ላይ ተመስርተው ነው። ስለዚህ ያለ እምነት፣ ያለ መተማመን ፌዴሬሽን የሚባል ጽንስ፣ ልምድም ሆነ ንድፈ ሃሳብ በአለም የለም።
ስለሆነም በአላማ፣ በቁጥር፣ በባህል፣ በራእይ ሆነ በፍላጎት የተለያዩ ብቻ ሳይሆን የሚጠርጠሩ፣የሚፎካከሩ፣ የሚጣሉ ጎሳዎች በእምነት፣ በኪዳን በመተማመን ቃል ኪዳን ላይ የተመሰረተ ህብረትም ሆነ መንግስት ሊያቆሙ አይችሉም። ራሱ የፌዴራላዊ ህብረትም ሆነ የጋራ መንግስት ሊያቆሙ የሚችሉት በፈጣሪም ሆነ በሕግ ፊት እኩል የሆኑት የኢትዮጵያ ግለሰቦች ናቸው። በኢትዮጵያ ውስጥ የተፈለገው አይነት ፌዴራሊዝም ሊቆም ሊጽና የሚችለው በኢትዮጵያ ዜጋዎችና በዜጋ ፍልስፍና፣ በዜጋ ፖለቲካ ንድፈ ሃሳብ እና በዜኘት ካልቸር ላይ ነው።