Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Horus
Senior Member+
Posts: 30653
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

የዘመናችን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቀውስ

Post by Horus » 20 Jul 2019, 01:57

(ይህ ሃተታ በ9/2/1995 ለER መጽሄት ልልከው ከጻፍኩት በኋላ ተረስቶ ዛሬ እንዳጋጣሚ ሳነበው አሁንም ያለውን ሁኔታ ስለሚያሳይ ምንም ሳልቀይር እነሆ ከ24 አመታት በኋላ። ሃተታው ረጅም ስለሆነ ለመደምደምያው ታገሱ)

የጽሁፉ መቋጫ የቀድሞ ኢትዮጵያም የቀድሞ ጎሳዎችም ወደ ዘመናዊነት በሚደረገው አድካሚ ጉዞ ይለወጣሉ፤ አሁን የምናየው ሁሉ ግዜያዊ ነው። በዚህ የሽግግር ውጥንቅጥ መሪና አሸናፊዎቹ እጅግ አዲስና ያልታየ መፍትሄ ማመንጨት የሚችሉት ፈላስፎች፣ ነዳፊዎች፣ ሃሳቢዎችና የኪነት ፈጣሪዎች ናቸው የሚል ነው ።

ኢትዮጵያ መሰረታዊ የውድመትና የድቀት አደጋ አለባት እላለሁ ። ይህን ስል ምን ማለቴ ነው?

አንደኛ፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ በአካል አይወድሙም፤ አይጠፉም። እንዲያውም በሚቀጥሉት ሰላሳ አምስት አመታት ወስጥ የሕዝባችን ቁጥር ከ55 ሚሊዮን ወደ 140 ሚሊዮን ያድጋል። የኢትዮጵያን ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊ፣ ባህላዊ ስርዓታት ተሽካሚዎችና አንቀሳቃሾች ይህ ሕዝብ ነው። ሆኖም አሁን ካለው ሕዝብ የተወሰኑት በሽግግሩ ወቅት ይጠፋሉ። ሽግግር ስል ግዙፉን ወደ ዘመናዊነት የሚደረገው አስቸጋሪና ዝብርቅርቅ ሽግግር ማለቴ ነው ። በሽሽግሩ የሚወድሙት ግን ከፊሉ ብቻ ናቸው።

በኢትዮጵያ ካሉት ብዙ ጎሳዎች አኳያ ወደ ዘመናዊነት በሚደረገው ሽግግር ወቅት የሚወድሙት ማህበረ ሰቦች የተኞቹ ናቸው? ከወድመት የሚድኑት ከመጥፋት የሚተርፉት በምን በምን ምክንያቶች ነው? በመሰረለቱ ከውድመት የሚድኑት ሕዝብ ሆኑ ጎሳዎች አሁን ከሚያምኑበት የጥፋትና የቀውስ ባህል እየከዱ ወደ አዲስ አስተሳሰብና ባህል የሚዞሩት ናችው። ይህን መሰል እውቀትና ችሎታ የሌላቸው ግለሰቦች፣ ጎሳዎችና ቡድኖች ወዳሚዎች ናቸው። ስለዚህ የዘመኑ ቀውስና ብሶት የሚጠይቀውን ለውጥ ለማድረግ ችሎታ ያላቸው ክፍሎች ግዙፉን ሽግግር ያልፋሉ፤ ያልቻሉት ይወድማሉ። አሁን ያለው ሞራሉ የላሸቀው ሰው አዲስ ነገር አይፈጥርም።

ሁለተኛ፣ ስለ ኢትዮጵያ ውድመት በሚጠቀስበት ወቅት ሌላው ግልጽ ነገር ኢትዮጵያዊያን እስከ ዛሬ የፈጠሯቸው ቁሳዊ ባህላት፣ ቁሳዊ ግንባታዎች ሁሉ አይደመሰሱም። የፈጠሩት ሳይንስ ሆነ ቴክኒክ ሁሉ አይወድምም። ሆኖም ከቁሳዊ ባህላችን፣ ከልማት ውጤቶች ከፊሉ በሽግግሩ ጦርነት፣ አብዮት፣ አናርኪና ሁከት ይወድማሉ። ከውድመት የሚድኑት ቁሳዊ (ለምሳሌ ቤቶች፣ መንገዶች፣ መኪናዎች) ከእሴታዊ ምንነት ጋር ብዙም የተቋለፉ አይደሉም። ለምሳሌ ለዘውድ አገዛዝ የታነጸው ቤተ መንግስት ለኮሚኒስት ፓርቲና ለወያኔ መሰብሰቢያ ያገለግላል። ፈንጂ ለጥፋትም ለማእድንም ያገለግላል። ስለዚህ ቀደም ሲል ለኢትዮጵያዊነት ግንባታ የተፈጠሩት ቁሳዊ ባህላት ሆነ ተቋማት አሁን ለጎሳ ስርዓት ግንባታ መገልገያ ተደርገዋል። ምንነትና እሴት እና የነሱ ተሸካሚ የሆነው ቁሳዊ መሳሪያ ያላቸው አንድነት እጅግ የላላ ነው። ቴሌቪዝን ሃይማኖትም ሌብነትም የሰበክበታል። እነዚህ ቁሳዊ መሳሪያዎች የአዲሱ ስርወ እሴት አገልጋይ ይሆናሉ።

ሶስተኛ፣ ከዚህ ቀደም በፌውዳሉ ስርዓት ስር ተዋቅሮ የነበረው የመላ ኢትዮጵያ ስርወ እሴት መዝቀጥና መፍረስ የሁሉም ባህልና ማህበራዊነት መፍረስ ወይም መበታተን አይደለም። ቀድሞ ያልተዋሃደ ነገር ሊበተን አይችልም። ስለዚህ የዘመኑ የጎሳ ስርወ እሴት ድሮ የነበረውን የጎሳዎች ልዩነት አጽድቋል፣ አጠናክሯል፤ እስከ ተወሰነ ድረስ እያደጉ የነበሩ የመላ ኢትዮጵያ እሴቶችን ሰባብሯል። ሆኖም ተጽዕኖው የተወሰነ እንጂ ጠቅላላ መበታተንና ዝቅጠት ሊሆን አይችልም። ጠበብ ብሎ በሴምና ባማራው ዙሪያ ያደገው ባህል ስሜታዊ ሆነ ሳይንሳዊ እስከ ተወሰነ ድረስ ተለውጦ ስፋት እያገኘ ነው። ግን ይህ ምን አይነት ባህል ነው?

አራተኛ፣ የኢትዮጵያ ብሄራዊ እሴትና ምንነት ወይም ማንነት በጎሳ እሴትና ማንነት እየተተካ ሲሄድ ወይም መሄድ ማህበረሰባዊና ባህላዊ ፈጠራን ማለትም ስልጣኔን ቀጥ አድርጎ አቁሟል፤ ያቆማልም። የተፈጥሮ ስይንቲስቶች እና ቁሳዊ ፈጣሪዎች የሚሰሩለት አገራዊ ፋይዳ ሆነ ትርጉም ከጠፋ ወዲህ ስራ አቁመዋል። በመንቀሳቀስ ላይ ያለው የጎሳ ባህል፣ ተረት፣ ታሪክና አፈታሪክ የሚቆፍረው ጠባቡ የሶሻል ሳይንስ ምሁር ብቻ ነው። በአንጻሩም ለኢትዮጵያዊነት የሚሟገተው የሶሻል ሳይንስ ምሁር ፖለቲካዊና ታሪካዊ ክርክር ያደርጋል። ክዚህ ውጭ የጎሳ ሳይንስ ወይም ቴክኖሎጂ የሚባል ነገር ስለሌለ ሳይንሳዊ ፈጠራ ከእሴትና ምንነት እጦት የተነሳ ወድቋል። ይህ መቼም ትልቁ ቀውስ ነው። ይህም ሆኖ በተፈጥሮ ሳይንስ ዙሪያ እያቆጠቆጠ የነበረው ምሁር ሲበተን ጠንካራ ብሄራዊ ምሁራን በሃይማኖት፣ በፍልስፍና በስነ ፖለቲካ ዙሪያ ተነስተው ብሄራዊ ፈጠራ ሊያደርጉ አልቻሉም።

ይህ ሁለገብ ዝቅጠት እጅግ አሳሳቢው ቀውስ ነው። በኢትዮጵያ ወስጥ ለብዙ ግዜ ብሄራዊ ሳይንሳዊ የፈጠራ እንቅስቃሴ ሊኖር አይችልም፤ አገራዊ እሴትና አለኝታ ጠፍቷልና። በማህበራዊ ፍልስፍና መስክም ተመሳሳይ ቀጥ የማለት አደጋ አለ ። በአጠቃላይ አገራዊ የሆኑት የፍልስፍና መሰረቶች ማለትም የግለሰቡ ሰብአዊነት፣ እና መደባዊ ህብራዊነት በዘር ጽንስ ስለተሻሩ ጎሳ በተሰኘው የቡድን ጽንስ ዙሪያ አንድም የረባ ፍልስፍና ሊነሳ አይችልም ። የጎሳ ጽንስ ቅድመ ፍልስፍና ስለሆነ፣ ቅድመ ሰብአዊነት ስለሆነ። ስለሆነም ሶሺያ ፊሎሶፊም ከፍተኛ ዝቅጠት ወስጥ ይግኛል። ሌላው ቀርቶ መንፈሳዊ ፍልስፍና እንኳን ሊያቆጠቁጥ አልቻለም።

አምስተኛ፣ በኢትዮጵያ የማህበራዊ ሳይንስ ቀውስ አለ። የጎሳ ጽንሰ ሃሳብም ሆነ የጎሳ እንቅስቃሴ ማህበራዊ ወይም ሶሺያል ሳይንስ የለውም። ይህ አዲስ ተብዬ ፖለቲካም በጭለማ ውስጥ የሚደረግ ሙከራ ነው። ጠባብ የፖለቲካ መሃንዲሶች የሚያጨማልቁት ሙከራ ነው። ብሄራዊ ሶሺያል ሳይንሱ ስረው መሰረቱን በደንብ ለውጦና ግልጽ አድርጎ የፈጠራ ንቅናቄ ማድረግ ተስኖት ቆሟል። የሶሺያ ሳይንስ ቀውሱ የጀመረው በሃይለ ስላሴ ዘመን ነበር። የዘውድ አገዛዝን ዘመናዊ ለማድረግና ለምዕራብ ተቀባይነት ለመስጠት ሲሞከር የተፈጠረ ውዥንብር ነበር። ስለዚህ በዘውድ አስተሳሰብና በሊብራል ዴሞክራሲ መካከል የተነሳው ቀውስና ውዥንብር እልባት ሳያገኝ የአብዮቱ ዘመን መጥቶ ሁለቱም (የመለኮታዊም ሆነ የሕዝባዊ ሃይል አስተሳሰብ) ከመድረክ አስወገዳቸው።

ሶሺያሊዝም እየተባለ ይታወቅ የነበረው የተሳሳተ ወታደራዊ አገዛዝ በአንድ ቃል የፖለቲካ ሃተታ ወይም ትንተና ከህብረተሰቡ እንዲጠፋ አደረገ። ወታደራዊ የቡድን አገዛዝ ከሶሻሊዝም ጋር እንደ ተምታታ ሁሉ ዛሬ ደግሞ የጎሳ አስተሳሰብና ርዕዮት ከዴሞክራሲ ጋር እየተምታታ ቀርቧል። ስለሆነም በጎሳ አስተሳሰብ መግነን ሳቢያ አዲሱ ዴሞክራሲያዊ አስተሳሰብ ትልቅ ቀውስ እንዲወድቅ ተደርጓል። ዘመናዊ ዴሞክራሲና ጎሰኝነት እስካልተለያዩና ዴሞክራሲ ከጎሰኘነት እስካልጸዳ ድረስ በኢትዮጵያ የሶሺያል ሳይንስ ቀውስ አያበቃም።

ሌላው ትልቁ የኢትዮጵያ ቀውስ የስነ ጥበብ ውድቀት ነው። እነሱም ስዕል፣ ጠረባ፣ ሙዚቃ፣ ስነጽሁፍ፣ ውዝዋዜ፣ ቲያትር፣ ሲኒማ፣ ዚቅ፣ አርኪቴክቸር ወዘተ ። ቀደም ሲል የነበሩት ጠቢባን እያለቁ ነው። አዲስ የሚፈጠሩት አብዛኞቹ ዋጋ ቢስ ናቸው፤ ጥልቀትና ንቃት የላቸውም። ብሄራዊ ራዕይና ስረው እሴት ላይ የተመሰረተ ፈጠራ ሳይሆን ከዚህም ከዚያ የተለቃቀመ፣ ከምዕራብ የተገለበተ የተቀዳ ስራ ነው ።
የቀረው ከጎሳዎች ግላዊ ባህል፣ ሙዚቃ ወዘተ ጋር የተያያዘ ነው ። የኪነትና የስነት መስክ በውራጅ ፈጠራ ተጥለቅልቋል ። እዚህ ላይ ተደጋግሞ የሚጠቀሰው የኢትዮጵያ ኪነትና የኢትዮጵያ ስነ ጥበብ የሚባል ነገር አለ ወይ የሚለው ነው? ወይስ የ90 ብሄረ ሰቦች ስብስብ ጥርቅም ስነ ጥበብ? ይህ ያልተመለሰውና አወዛጋቢው ጥያቄ ነው።

ሌላው ትልቁ የኢትዮጵያ ቀውስ ሕግና ስነምግባር (ኤቲክስ) የተመለከተ ነው። በአንደኛ ደረጃ ዘመናዊ ወይም በተዋሃደ መልኩ የኢትዮጵያን ሕግና ስነምግባር የምንላቸው በምዕራቡ ግፊት የገባው እጅግ አለማዊና አምባገነን ባህል ሳቢያ ለብዙ አመታት የተከሰተ ኢሕጋዊነት ወይም የሕገወጥነት ክስተት አለ። ይህ የሕገወጥነትና የስነ ምግባር (ሞራል) ብልሹነት በአገሪቱ ለዴሞክራሲ አለመኖር ብቻ ሳይሆን በታሪክ ውስጥ በብሄረሰቦች መካከል የነበረውን ግንኙነት የመነጨም ነው። በተለይ ስነምግባር በተመለከተ የ90ቹ ጎሳዎች ግላዊ ኤቲክስ አለመዋሃዱና አንድ ብሄራዊ የኢትዮጵያ ስነምግባር አለመፈጠሩን ያመለክታል።

በዚህ መስክ ያለው ቀውስ እጅግ አሳሳቢ የሚሆነው የተለያዩ የብሄረ ሰብ ሴራዎችና ስነምግባራት መኖራቸው ብቻ አይደለም። የሕግ አለመከበር፣ የሃይል መግነን፣ በስልጣን መባለግና ፍርደገምድልነት፣ እኔባይነት ሌሎችን ማፈን በሃይል ሌሎችህን ማንበርከክ የዛሬን ጥቅም ባይነት ብቻ (ሄደኒዝም) እና አፍራሽነት የደምሳሽነት አመለካከት (ኒሂሊዝም) የመሳሰሉት የሁሉንም ብሄረሰብ አኗኗር ስለሚያቃውሱ አደገኛነታቸው ህብረባህል ከመሆን የባሰ ነው።

ስለዚህ በኢትዮጵያ ውስጥ ሁለት አይነት ቀውሶችን እናስተውላለን። አንደኛው የመላ ኢትዮጵያ አንድ ወጥ ስርዓት፣ እሴት፣ ባህል፣ ለማስተባበር ለማዋሃድ የሚሞክረው አዝማሚያ ነው። ይህ አዝማሚያ የተበተነና አቅጣጫ የለሽ መሆኑ ነው። ሁለትኛው የእያንዳንዱ ጎሳ እሴትና ባህል ቁንጽል ብቸኛ መሆንና በሌሎች ተቀባይነትን ማጣት እንዲሁም በዘመናዊነት መመታቱ ነው። ኢትዮጵያ አንድ ወጥ እሴት የላትም፤ ያለውም በምዕራብ ዘመናዊነት ተቃውሷል። የጎሳው እሴት አንዱም ለብሄራዊነት ብቃት ማጣቱ ብቻ ሳይሆን እሱም በዘመናዊነት ተቃውሷል። በሶስተኛ ድረጃ በኢትዮጵያ እሴትና (ካለ ማለት ነው) በጎሳው እሴት መሃል ያልተቋለጠ ግጭት ይካሄዳል። እነዚህ ሶስት ክስተቶች ሕግን፣ ስነምግባርን፣ ዴሞክራሲን፣ አስተዳደርን፣ አደረጃጀትን፣ ወዘተ ሁሉ ያካልላሉ። ለዚህ ደግሞ ይህ ነው የሚባል መፍትሄ የለንም።

በሌላ ደረጃ እየተከሰተ ያለ መሰረታዊ ችግር አለ። ኢትዮጵያ አንድ ወጥ ብሔራዊ እሴትና ባህል አለመፍጠሯ፣ በ90 ብሄረሰብ ባህሎችና በብዙ ሃይማኖቶች መከፋፈሏ ብቻ ሳይበቃ በተለይ ከምዕራቡ ዘመናዊነት ጋር የተቃመሱት የጎሳ ባህላትም የስሜታዊነት ጥራዝነጠቅነት ብልሽት ደርሶባቸዋል። ያጭር ግዜ ድል፣ ደስታ፣ ተንኮልና አፍራሽነት በሁሉም ባህላት ዘንድ እሴቶች ሆነዋል። ስለዚህ ስርወ እሴት ያጣው የኢትዮጵያዊነት ባህል (ካልቸር) ብቻ ሳይሆን እያንዳንዱ ጎሳም ተመሳሳይ ቀውስ አጋጥሞታል። ከዚህ ሁለገብ የሆነ ቀውስ ለመውጣት ሰዎች ግዙፍ የሆኑ የእምነት፣ የአንድነት፣ የትብብር፣ የፍቅር እሴቶችን ከመሻት ይልቅ በግላዊና ቡድናዊ የታሪክና የህላዌ ምርምር ወይም ቁፋሮ ላይ ስለተጠመዱ እጅግ ቅጥ ያጣ የአመለካከት ጥበትና ውዥንብር በህብረተሰቡ ሰፍኗል። ስለሆነም ኢትዮጵያ የረዥም ግዜና መሰረታዊ ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችላት ብሩህ አመለካከት፣ ብሩህ ራዕይ የላትም፤ በምሁሮችዋ ማለት ነው።

ስለዚህ ግዙፉ የኢትዮጵያ ሽግግር ከየት ወዴት የሚሄድ ሽግግር ነው? የሚለው በፍጹም ግልጽ አይደለም። ከአንድነት ወደ መበተን ወይስ ከመበተን ወደ አንድነት? ወደ አለማዊነት ወይስ ወደ መንፈሳዊነት? ከእምነት ወደ ሳይንስ ወይስ ከሳይንስ ወደ እምነት? ከጎሳዊነት ወደ ዜግነት ወይስ ወደ ባሰ ዘረኝነት? ከኢሰባዊነት ወደ ሰባዊነት ወይስ ሌላ?

ይህን ግዙፍ ሽግግር ለምፍጠር በሳይንስና ቴክኖሎጂ፣ በፊሎሶፊ፣ በሶሺያል ሳይንስ በተለይ በፕለቲካ ሳይንስ፣ በስነ ጥበብ፣ በሕግና ስነምግባር መስኮች ሊመሩ የሚችሉ የሃይማኖት፣ የሳይንስ፣ የስነት፣ የስነ ህብረተሰብ መሪዎች ኢትዮጵያ የሏትም። መፈጠር ያለበትና ሊፈጠር የሚታሰበው እምነትና ንድፈ ሃሳብ መብላላት አልጀመረም፤ ሲብላላ አይታይም።

ከላይ የቀረበው ሃተታ የሚያመለክተው ጉዳይ ቀደም ሲል በትንሹም ቢሆን በኦርቶዶክስ ክርስትና እምነትና በአማርኛ ቋንቋ ዙሪያ ተገንብቶ የነበረው የባህልና እሴት መለኪያ (ደረጃው) እጅግ መዝቀጡን ነው። የብሄረሰቦች ፉክክር ከሰፈነ ወዲህ አገሪቱ ባህላዊና እሴታዊ ህብረተሰብ መሆኗ ጠፍቶ የምዕራብና የምስራቅ ሸቀጣ ሸቀጣዊ ባህል በገፍ የሚራገፍባት ገበያ ሆናለች። በኢትዮጵያ ፖለቲከኞች እንጂ አገር መሪዎች የሉም። የዜጋዎች ደህንነት ባገር አቀፍ ድህነት ማለትም የእምነት ድህነት፣ የፍልስፍና ድህነት፣ የሳይንስ፣ቴክኖሎጂና የፈጠራ ድህነት፣ የሶሻልና ፖለተካ ሳይንስ ድህነት፣ ተዉጧል። በስነ ጥበብ ማለትም በስዕል፣ ጠረባ፣ ሙዚቃ፣ ስነጽሁፍ፣ ቲያትር፣ ውዝዋዜ፣ ስነሲኒማ፣ ስነፎቶ ሁሉ ድህነት፤ በሕግና ስነምግባር ድህነት ጭምር የታጠረ ሁኖዋል። ህብረተሰቡ በጥቂት ያልተማሩ ሃብታሞችና በብዙሃን ያልተማሩ ድሆች ተከፋፍሏል። ከላይ የተዘረዘሩትን መስኮች ሊፈጥር የሚችለው ምሁር ወይም ተሰዷል፣ አለያም ፈጽሞ የለም። ስለዚህ ኢትዮጵያዊያን በአይምሮዋቸው የሚሰሩ ሕዝቦች ሳይሆኑ መደባዊ ክፍፍሉ በሚበሉና በሚራቡ ሰዋዊ እንስሶች መካከል ነው። ይህ ሰቆቃ (ትራጀዲ) እንጂ ሽግግር አይደለም።

ከዚህ መቀመቅ እንዴት እንደሚውጣ የሚያሳይ ብርሃን አለን? ለኢትዮጵያ ወድቀትና ወድመት ምክንያት አገሩ ቀውስ መሆኑ ብቻ ኣይደለም። ከፍተኛ ያስተሳሰብና የመመራመር ድርቀት አለ። ከፍተኛ የፈጠራ አልባነት ጭለማ ሰፍኗል። ትልቁ ችግር የድንቁርና መስፈን ነው። በዚህ ጭለማ ወስጥ ከምዕራብ በሚመጣ ውራጅ ሸቀጥና ባህል አንድም ፋይዳ ለመፈየድ አይቻልም።

ስለሆነም አዲስ ቅድመ መርህ (አዲስ ፓራዳይም) አዲስ መርሃ እሴት (ቫልዩ ፕሪንሲፕል) መፈልሰፍ አለበት ። ይህን መሰል የሃሳብና የፈጠራ ብርሃን በኢትዮጵያ ምሁራን ሁሉ ይሞከራል ብሎ ማሰብ የተሳሳተ ነው። የጎሳ ፖለቲካ የምሁራንን አንድነት አፍርሷል። ተያይዞም ብሄራዊ (አገራዊ) የሃሳብ አንድነት ፈርሷል። በመሆኑም ሙሉ ባህል ወይም አሞሌ ካልቸር፣ የኢትዮጵያ ምልአተ ባህል ሊፈጥሩ አይችሉም፤ እንዳይፈጠር አድርገዋል። የኢትዮጵያ እጅግ መሰረታዊና ወሳኝ ቀውስ (ችግር) መከፋፈል፣ መበታተን ነው። የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ብትንና የቅውስ (ኬዎስ) ስርዓት ነው። ከሃይማኖት እስከ ተራ ሕይወት ሁሉም ብትን ስርዓት ነው።

ኢትዮጵያ ብትን ስርዓት እስከ ሆነች ድረስ ምልአተ ባህል፣ እሴተ ተዋህዶ ያለው ብሄራዊ ሴራ መፍጠር አለመቻል ብቻ ሳይሆን የተበታተኑት ክፍሎች እርስበርሳቸው ይጋጫሉ፣ ይጣላሉ፣ ይወድማሉ። ከላይ የተዘረዘሩት የባልና የፈጠራ መስኮች የሚንቀሳቀሱት በሰዎች፣ በቡድኖች፣ በሕዝብ ነው። እነዚህ የባህል ተሸካሚዎች እስከተበጣበጡ ድረስ አንድ ወጥ ነገር ለመፍጠር አለመቻል ብቻ ሳይሆን ምንም ነገር ሊፈጥሩ አይችሉም፤ አንዱ ሌላውን ስለሚያፈርሰው። ኢትዮጵያ ብትን ስርዓት ብቻ ሳትሆን የግጭት ስርዓት ነች ። የእርስበርስ መጠፋፋት፣ መዋደም፣ የእልቂት ስርዓት ንች ። ይህን መሰል ህብረተሰብ ወደ ታች እንጂ ወደ ላይ አይሸጋገርም። ለዚህ ሁሉ መሰረቱ ኢትዮጵያዊያን ማንም ይሁኑ ከየትም ይወለዱ፣ በአንድ ፈጣሪ የሚያምን፣ በሰው ልጅ ሰባዊነትና ልዕልና የሚያምን፣ በኢዮጵያዊያን ሁሉ ወንድማማችነት የሚያምን አንድ ሕዝብ አለመሆናቸው ነው። ይህን መሰረት፣ ይህን ቅድመ መርህ፣ ይህን ፓራዳይም እውን የሚያደርገው ትውልድ ገና የለም።

ያልኳቸውን ነገሮች በትንሹ ለመድገም፣ ኢትዮጵያ በማንኛውም መስክ ብትለካ ማለትም በሃይማኖት፣ በፍልስፊና፣ በተፈጥሮ ሳይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በሶሺያል ሳይንስ፣ በስነ ጥበብ፣ በሕግና በስነ ምግባር በሁሉም መስክ ቁርጭራጭ ስርዓት ነው። እነዚህ እጅግ ብዙ ቁርጭራጮች በግለ ህልውናቸው ፋይዳቢስ ሲሆኑ በህብረ ህልውናቸው ተጻራሪ፣ ተዋዳሚ፣ ተፋላሚና የግጭት መነሾዎች ናቸው። ስለዚህ ለየብቻም በህበረትም ዋጋቢሶች ናቸው። በግል ለድህነትና ለድንቁርና ተጋልጠዋል፤ ከተባበሩ ይተላለቃሉ ። መውጫ የለሽ ዙሪያ ጥምትም ማለት ነው።

ከላይ የተዘረዘሩት ችግሮች በኢትዮጵያ ግለሰቦች እና ቡድኖች አይምሮ ላይ ወይም አስተሳሰብ ዘንድ የሚያስከትሉት ተጽዕኖዎች አሉ። የግለሰቦች፣ ብሄረሰቦችና ቡድኖችን የማንነት ትርጉም ለውጠዋል፣ አናግተዋል። እነዚህ የምንነትና የማንነት ትርጉሞች ተበታትነዋል፣ ተፍረክርከዋል፣ ተቃውሰዋል፣ ተዘባርቀዋልም። ተያይዞም እነዚህ ግለሰቦችና ቡድኖች ያሏቸው፣ የነበራቸው እሴቶች ወይም ሰርዓተ እሴቶች፣ አስተሳሰብ፣ መርሆችና እምነቶች ተበታትነዋል፣ ተፍረክርከዋል፣ ተቃውሰዋል። የሞራል ስነስርዓታቸው ላሽቋል፣ ወድቋል። ማለትም ደግና ክፉ፣ ጥሩና መጥፎ፣ ትክክልና ስህተት፣ ፍትህና ግፍ፣ ጠቃሚና ጎጂ፣ ገምቢና አፍራሽ፣ እድገትና ወድቀት፣ ልማትና ወድመት፣ ነጻነትና ባርነት፣ ትልቅነትና ትንሽነት፣ ክብርና ውርደት፣ ራዕይና መታወር፣ ብርሃንና ጭለማ፣ ፍቅርና ጥላቻ፣ የሰላምና ሽብር፣ ስርዓትና ቀውስ በአንድ ቃል ደህንነትና ድህነትን የሚለይ የግምትና የህሊና ተቋማቸው ወይም ችሎታቸው ተቃውሷል። ከላይ የተጠቀሰው መበታተንና መጋጨት የግለሰቦችን አስተሳሰብና ሰነምግባር በመበታተን ላይምሮና የሞራል አናርኪ ዳርጓቸዋል። ማሀበራዊ አናርኪና ያስተሳሰብ ምስቅልቅልነት አይነጣጠሉም። አንዱ ሌላውን ይወልዳል፤ እንዲያውም ያስተሳሰብና የሞራል ስርዓት ሳይኖር ማህበራዊ ስርዓት ሊኖር አይችልም። ብትን ሃይማኖት፣ ብትን ፍልስፍና፣ ብትን እሴት፣ ብትን ፖለቲካ፣ ብትን ስነት፣ ወዘተ የሚፈጥሩት ብትን ህብረተሰብን ነው።

ያስተሳሰብ፣ የህሊናና የሞራል ቀውስ ወይም አናርኪ ውጤቱ የተፋፋመ ቅራኔ ፣ ግጭት፣ ሁከትና ጦርነት ነው። በኢትዮጵያ የሃይልና የጉልበተኝነት ሚና እየገነነ ይሄዳል። ጦርነት፣ አብዮት፣ አመጽ፣ ወንጀል፣ ሕግ አልባነት በአገሪቱ ይስፋፋሉ። በሰው ሕይወት ላይ እልቂት ይከተላል። የሕዝቦች ቁሳዊ መደላደል (አኗኗር) ይፈርሳል። ያገሪቱ ቁሳዊ ሃብት ይወድማል። ይህ የመጨረሻ ወድመትና ጥፋት ከሚከተሉ ሶስት አዝማሚያዎች አንዱን ሊወስድ ይችላል።

አንደኛው አዝማሚያ፣ የኢትዮጵያ ህብረተሰብ በብትንትንነቱና በቀውሱ ለረጅም ዘመን ሊቀጥል ይችላል። ይህም ማለት አገሪቱ ምንም አይነት መሰረታዊ መፍትሄ ሳታገኝ በሞትና በህይወት መካከል አሳዛኝ የሆነው ህልውናዋ እንደ ተንጠለጠለ ሊቀጥል ይችላል።

ሁለተኛው አዝማሚያ፣ የኢትዮጵያ ህብረተሰብ በተወሰኑ ሰፋፊ መሬቶች ፣ ባህሎች፣ ቋንቋዎች፣ ግዛቶች፣ ተከፋፍሎ በአዲስ ፌዴራላዊ ወይም ኮንፌዴራላዊ ስብስብ ሊቀጥሉ ይችላሉ። ኢትዮጵያ በብዙ አገሮች የምትከፋፈለቅ ይህ አዝማሚያ እውን ከሆነ ነው።

ሶስተኛው አዝማሚያ፣ የኢትዮጵያ ህብረተሰብ መሰረታዊ ያስተሳሰብና የእስትራተጂ ለውጥ አድርጎ ስርወ እሴታችን የአንድ ፈጣሪ ገናናነት፣ የሰው ልጅ ልዕልናና የኢትዮጵያዊያን አንድ ቤተሰብነት ሆኖ አገሪቱ ከውድቀት ልትድን ትችላለጭ

ከነዚህ ሶስት አዝማሚያዎች የትኛው እውን እንደሚሆን የሚወሰነው በኢትዮጵያ ምሁራን መካከል ባለው የሃይል ሚዛንና የማሰብ ችሎታ ነው። ለምሳሌ ያንድነትም ሆነ የብሄረሰብ ምሁራን ከደከሙና አዲስ መፍትሄ ማቅረብ ካልቻሉ ወይም አንዱ ከለላው በልጦ ማሸነፍ ካልቻለ አንደኛ አዝማሚያ እውን ይሆናል።

የብሄረሰብ ምሁራን የበላይነት ይዘው የጎሳ ክፍፍል አሁን ባለው ቀጥሎ ካደገና ካሸነፈ ሁለተኛ አዝማሚያ እውን ይሆናል። የኢትዮጵያ አንድነት ምሁራን ከጠነክሩ ሶስተኛ አዝማሚያ እውን ይሆናል።

ለምሳሌ ሶስተኛው አዝማሚያ ሃይማኖትን በተመለከተ የኢትዮጵያዊያን እምነት ሆነ አምልኮ መሆን ያለበት እግዚአብሄር፣ ክርስቶስ፣ አላህ፣ ያዌ፣ ጂሆቫ፣ ዋቃ፣ ሌላም ሌላም በሚል መናቆር ሳይሆን በአንድ ፈጣሪ ማመን ነው። ቤተ እምነት ሆነ ቤተ አምልኮ ሁሉ የአንድ ፈጣሪ ቤተመቅደስ ሆኖ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ የአንድ እምነት አማኝ አንድ ሕዝብ መሆናቸውን መቀብለና ያንን ማስተማር አለበት ። የኢትዮጵያ ብሄረሰብ ግለሰቦች ሁሉ ማለትም ኢትዮጵያዊ ሰው ሁሉ የአንድ ፈጣሪ ፍጡራን እንደ ሆኑ። እነሱም አንድ ኢትዮጵያዊ ብሄር እንደሆኑ ተቀብሎ የኢትዮጵያ ጎሳ እንደሆኑ ማመንና ማስተማር አለበት ። በተመሳሳይ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ አንድ ቤተሰብ ፣ ወንድማማች እንደሆኑ ማመንና ማስተማር አለበት ።

በእነዚህ ሶስት ስረወ እሴቶች መሰረት የቋንቋ፣ የሃይማኖት፣ የፍልስፍና፣ የስነ ጥበብ፣ የማህበራዊ ሳይንስ፣ የሕግና የስነ ምግባር ውህደቶችን የሚያንጸባርቅ ባህል፣ ፈጠራ፣ ንድፈ ሃሳብ መቀመር ግድ ይላል። የኢትዮጵያ አንድነት ምሁራን ይህን ማድረግ ካልቻሉ የጎሳ ምሁራን አሁን በጀመሩት አጀንዳ ቀጥለው ሕዝቡን በብዙ አማልክጥ በብዙ ጎሳዎች፣ በብዙ ቋንቋዎች፣ በብዙ ባህሎች በመከፋፈል ይህም ውሎ አድሮ ወይ ኢትዮጵያ መከፋፈል ወይም ወደ ኢትዮጵያ ወድመት ማምራቱ አይቀሬ ነው።

ይህን ያልኩት የዛሬ 24 አመት ነበር
Last edited by Horus on 27 Jul 2019, 20:17, edited 18 times in total.

Horus
Senior Member+
Posts: 30653
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: የዘመናችን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቀውስ

Post by Horus » 21 Jul 2019, 23:04

አንድ ሰው የኢትዮጵያ ቀውስ መነሾ የካልቸሮች መጋጨት ነው ሲል ያኖረውን ሃረግ አየሁ ከላይ ባለው መጣጥፌ ወስት ብዙ የምለው አለኝ ። ጠብቁኝ

Horus
Senior Member+
Posts: 30653
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: የዘመናችን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቀውስ

Post by Horus » 22 Jul 2019, 01:09

አምስተኛ፣ በኢትዮጵያ የማህበራዊ ሳይንስ ቀውስ አለ። የጎሳ ጽንሰ ሃሳብም ሆነ የጎሳ እንቅስቃሴ ማህበራዊ ወይም ሶሺያል ሳይንስ የለውም። ይህ አዲስ ተብዬ ፖለቲካም በጭለማ ውስጥ የሚደረግ ሙከራ ነው። ጠባብ የፖለቲካ መሃንዲሶች የሚያጨማልቁት ሙከራ ነው። ብሄራዊ ሶሺያል ሳይንሱ ስረው መሰረቱን በደንብ ለውጦና ግልጽ አድርጎ የፈጠራ ንቅናቄ ማድረግ ተስኖት ቆሟል። የሶሺያ ሳይንስ ቀውሱ የጀመረው በሃይለ ስላሴ ዘመን ነበር። የዘውድ አገዛዝን ዘመናዊ ለማድረግና ለምዕራብ ተቀባይነት ለመስጠት ሲሞከር የተፈጠረ ውዥንብር ነበር። ስለዚህ በዘውድ አስተሳሰብና በሊብራል ዴሞክራሲ መካከል የተነሳው ቀውስና ውዥንብር እልባት ሳያገኝ የአብዮቱ ዘመን መጥቶ ሁለቱም (የመለኮታዊም ሆነ የሕዝባዊ ሃይል አስተሳሰብ) ከመድረክ አስወገዳቸው።

ሶሺያሊዝም እየተባለ ይታወቅ የነበረው የተሳሳተ ወታደራዊ አገዛዝ በአንድ ቃል የፖለቲካ ሃተታ ወይም ትንተና ከህብረተሰቡ እንዲጠፋ አደረገ። ወታደራዊ የቡድን አገዛዝ ከሶሻሊዝም ጋር እንደ ተምታታ ሁሉ ዛሬ ደግሞ የጎሳ አስተሳሰብና ርዕዮት ከዴሞክራሲ ጋር እየተምታታ ቀርቧል። ስለሆነም በጎሳ አስተሳሰብ መግነን ሳቢያ አዲሱ ዴሞክራሲያዊ አስተሳሰብ ትልቅ ቀውስ እንዲወድቅ ተደርጓል። ዘመናዊ ዴሞክራሲና ጎሰኝነት እስካልተለያዩና ዴሞክራሲ ከጎሰኘነት እስካልጸዳ ድረስ በኢትዮጵያ የሶሺያል ሳይንስ ቀውስ አያበቃም።

(ይቀጥላል/ይህ ገና መግቢያው ነው)

Horus
Senior Member+
Posts: 30653
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: የዘመናችን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቀውስ

Post by Horus » 22 Jul 2019, 03:26

ሌላው ትልቁ የኢትዮጵያ ቀውስ የስነ ጥበብ ውድቀት ነው። እነሱም ስዕል፣ ጠረባ፣ ሙዚቃ፣ ስነጽሁፍ፣ ውዝዋዜ፣ ቲያትር፣ ሲኒማ፣ ዚቅ፣ አርኪቴክቸር ወዘተ ። ቀደም ሲል የነበሩት ጠቢባን እያለቁ ነው። አዲስ የሚፈጠሩት አብዛኞቹ ዋጋ ቢስ ናቸው፤ ጥልቀትና ንቃት የላቸውም። ብሄራዊ ራዕይና ስረው እሴት ላይ የተመሰረተ ፈጠራ ሳይሆን ከዚህም ከዚያ የተለቃቀመ፣ ከምዕራብ የተገለበተ የተቀዳ ስራ ነው ።
የቀረው ከጎሳዎች ግላዊ ባህል፣ ሙዚቃ ወዘተ ጋር የተያያዘ ነው ። የኪነትና የስነት መስክ በውራጅ ፈጠራ ተጥለቅልቋል ። እዚህ ላይ ተደጋግሞ የሚጠቀሰው የኢትዮጵያ ኪነትና የኢትዮጵያ ስነ ጥበብ የሚባል ነገር አለ ወይ የሚለው ነው? ወይስ የ90 ብሄረ ሰቦች ስብስብ ጥርቅም ስነ ጥበብ? ይህ ያልተመለሰውና አወዛጋቢው ጥያቄ ነው።

Horus
Senior Member+
Posts: 30653
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: የዘመናችን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቀውስ

Post by Horus » 22 Jul 2019, 03:55

ፕረዘንት፣
እርግጥ ለጥያቄህ መልሱ ረጅም ቢሆንም ባጭሩ የጎሳ ማህበራዊ አደረጃጀትና አስተዳደር ከንጉሳዊ ሰርአት እጅግ ቀድሞ የነበረ ሰዎች ከትንሽ ቤተ ሰብ ወደ ኤክቴድድ አሚሊ ከዚያም ወደ ክላን ብሎም ትራይብ በለው በአለቃ በዘፈቀደ በልማድ የሚሰራበት ነበር ። እሱን ተክቶ የመጣው የፊኡዳል ወይም ዘውድ አዛዝ የቆመበት ሃሳብ መለኮታዊ ተረት እንጂ ሳይንሳዊ አልነበረም ። ለምሳሌ አንድ የንጉስ ዘር በዘር ማንዘሩ የሚነግሰው የንጉስ ደም አለው በሚለው ተረት ወይም ሚትዝ እንጂ ፋክት ወይም እውነት ስለሆነ አይደለም ። ግን ተረትም ቢሆም ያንድ ንጉስ የመግዛት መብት የሚመነጨው ከየት ነው ቢባል ከአግዚአብሄር ነው ። ንጉስ በመሬት ላይ የአምላክ ወኪል ነው ይባላል። ደሮ ንጉሱና ፓፓሱ አንድ ሰው ነበሩ ። ይህ ለዘመኑ ከጎሳ የሰፈር አለቃ ጉልበተኛ ወይ ሽማግሌ አስተዳደር የተሻለ ነበር። አሁን አንድ የጎሳ አለቃ የምግዛት መብቱ ከየት መጣ ቢባል ያ ህዝብ ያንድ አባት ልጆች ስለሆኑ ጎሳ ማለት ባባቱ የሚስተዳደር ማለት ነው። ግ ና ከጊዜ ብዛት የተደባለቁ ሰዎች በስመነጋ አባታቸው ባልሆነ አለቃ መገዛት ቆሞ ሃይል የሚመጣው ከአምላክ ነው ተብሎ ጎሳ ተሻረ። እነዚ ሁሉ የሶሻል ሆነ የፖለቲካ ሳይንስ አለነበሩም ፤ የነበረው እምነት እንጂ ሳይንስ አልነበረም ። ሳይንስ ከ 16ኛ ዘመን ግለሰብ፣ ነጻነት፣ የግለሰብ አንድ ድምጽ የራሱን ግላዊ የተፈጥሮ ሃይልና መብት በድምጽ ወይ ቮት አማካይነት መንግስት አቁሞ የሚሾሙና የሚሻሩ መሪዎች ፈጥሮ ሕገ መንግስታዊ የፖለቲካ ማህበር ሲሆን ነው የፖለቲካ ሳይንስ የተፈጠረው ።

ስለዚህ የጎሳ ፖለቲካ እምነት እንጂ ሳይንስ አይደለም። ጉራጌ መሆን አማራ መሆን እምነት እንጂ ሳይንስ አይደልም ። ኦሮሞ የሚባል ሳይንስ ወይም ጂን የለም ።

Horus
Senior Member+
Posts: 30653
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: የዘመናችን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቀውስ

Post by Horus » 22 Jul 2019, 22:57

ሌላው ትልቁ የኢትዮጵያ ቀውስ ሕግና ስነምግባር (ኤቲክስ) የተመለከተ ነው። በአንደኛ ደረጃ ዘመናዊ ወይም በተዋሃደ መልኩ የኢትዮጵያን ሕግና ስነምግባር የምንላቸው በምዕራቡ ግፊት የገባው እጅግ አለማዊና አምባገነን ባህል ሳቢያ ለብዙ አመታት የተከሰተ ኢሕጋዊነት ወይም የሕገወጥነት ክስተት አለ። ይህ የሕገወጥነትና የስነ ምግባር (ሞራል) ብልሹነት በአገሪቱ ለዴሞክራሲ አለመኖር ብቻ ሳይሆን በታሪክ ውስጥ በብሄረሰቦች መካከል የነበረውን ግንኙነት የመነጨም ነው። በተለይ ስነምግባር በተመለከተ የ90ቹ ጎሳዎች ግላዊ ኤቲክስ አለመዋሃዱና አንድ ብሄራዊ የኢትዮጵያ ስነምግባር አለመፈጠሩን ያመለክታል።

Horus
Senior Member+
Posts: 30653
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: የዘመናችን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቀውስ

Post by Horus » 22 Jul 2019, 23:54

በዚህ መስክ ያለው ቀውስ እጅግ አሳሳቢ የሚሆነው የተለያዩ የብሄረ ሰብ ሴራዎችና ስነምግባራት መኖራቸው ብቻ አይደለም። የሕግ አለመከበር፣ የሃይል መግነን፣ በስልጣን መባለግና ፍርደገምድልነት፣ እኔባይነት ሌሎችን ማፈን በሃይል ሌሎችህን ማንበርከክ የዛሬን ጥቅም ባይነት ብቻ (ሄደኒዝም) እና አፍራሽነት የደምሳሽነት አመለካከት (ኒሂሊዝም) የመሳሰሉት የሁሉንም ብሄረሰብ አኗኗር ስለሚያቃውሱ አደገኛነታቸው ህብረባህል ከመሆን የባሰ ነው።

Horus
Senior Member+
Posts: 30653
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: የዘመናችን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቀውስ

Post by Horus » 23 Jul 2019, 00:28

ስለዚህ በኢትዮጵያ ውስጥ ሁለት አይነት ቀውሶችን እናስተውላለን። አንደኛው የመላ ኢትዮጵያ አንድ ወጥ ስርዓት፣ እሴት፣ ባህል፣ ለማስተባበር ለማዋሃድ የሚሞክረው አዝማሚያ ነው። ይህ አዝማሚያ የተበተነና አቅጣጫ የለሽ መሆኑ ነው። ሁለትኛው የእያንዳንዱ ጎሳ እሴትና ባህል ቁንጽልና ብቸኛ መሆንና በሌሎች ተቀባይነትን ማጣት እንዲሁም በዘመናዊነት መመታቱ ነው። ኢትዮጵያ አንድ ወጥ እሴት የላትም፤ ያለውም በምዕራብ ዘመናዊነት ተቃውሷል። የጎሳው እሴት አንዱም ለብሄራዊነት ብቃት ማጣቱ ብቻ ሳይሆን እሱም በዘመናዊነት ተቃውሷል። በሶስተኛ ድረጃ በኢትዮጵያ እሴትና (ካለ ማለት ነው) በጎሳው እሴት መሃል ያልተቋለጠ ግጭት ይካሄዳል። እነዚህ ሶስት ክስተቶች ሕግን፣ ስነምግባርን፣ ዴሞክራሲን፣ አስተዳደርን፣ አደረጃጀትን፣ ወዘተ ሁሉ ያካልላሉ። ለዚህ ደግሞ ይህ ነው የሚባል መፍትሄ የለንም።

Horus
Senior Member+
Posts: 30653
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: የዘመናችን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቀውስ

Post by Horus » 23 Jul 2019, 13:37

በሌላ ደረጃ እየተከሰተ ያለ መሰረታዊ ችግር አለ። ኢትዮጵያ አንድ ወጥ ብሔራዊ እሴትና ባህል አለመፍጠሯ፣ በ90 ብሄረሰብ ባህሎችና በብዙ ሃይማኖቶች መከፋፈሏ ብቻ ሳይበቃ በተለይ ከምዕራቡ ዘመናዊነት ጋር የተቃመሱት የጎሳ ባህላትም የስሜታዊነት ጥራዝነጠቅነት ብልሽት ደርሶባቸዋል። ያጭር ግዜ ድል፣ ደስታ፣ ተንኮልና አፍራሽነት በሁሉም ባህላት ዘንድ እሴቶች ሆነዋል። ስለዚህ ስርወ እሴት ያጣው የኢትዮጵያዊነት ባህል (ካልቸር) ብቻ ሳይሆን እያንዳንዱ ጎሳም ተመሳሳይ ቀውስ አጋጥሞታል። ከዚህ ሁለገብ የሆነ ቀውስ ለመውጣት ሰዎች ግዙፍ የሆኑ የእምነት፣ የአንድነት፣ የትብብር፣ የፍቅር እሴቶችን ከመሻት ይልቅ በግላዊና ቡድናዊ የታሪክና የህላዌ ምርምር ወይም ቁፋሮ ላይ ስለተጠመዱ እጅግ ቅጥ ያጣ የአመለካከት ጥበትና ውዥንብር በህብረተሰቡ ሰፍኗል። ስለሆነም ኢትዮጵያ የረዥም ግዜና መሰረታዊ ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችላት ብሩህ አመለካከት፣ ብሩህ ራዕይ የላትም፤ በምሁሮችዋ ማለት ነው።

ስለዚህ ግዙፉ የኢትዮጵያ ሽግግር ከየት ወዴት የሚሄድ ሽግግር ነው? የሚለው በፍጹም ግልጽ አይደለም። ከአንድነት ወደ መበተን ወይስ ከመበተን ወደ አንድነት? ወደ አለማዊነት ወይስ ወደ መንፈሳዊነት? ከእምነት ወደ ሳይንስ ወይስ ከሳይንስ ወደ እምነት? ከጎሳዊነት ወደ ዜግነት ወይስ ወደ ባሰ ዘረኝነት? ከኢሰባዊነት ወደ ሰባዊነት ወይስ ሌላ?

ይህን ግዙፍ ሽግግር ለምፍጠር በሳይንስና ቴክኖሎጂ፣ በፊሎሶፊ፣ በሶሺያል ሳይንስ በተለይ በፕለቲካ ሳይንስ፣ በስነ ጥበብ፣ በሕግና ስነምግባር መስኮች ሊመሩ የሚችሉ የሃይማኖት፣ የሳይንስ፣ የስነት፣ የስነ ህብረተሰብ መሪዎች ኢትዮጵያ የሏትም። መፈጠር ያለበትና ሊፈጠር የሚታሰበው እምነትና ንድፈ ሃሳብ መብላላት አልጀመረም፤ ሲብላላ አይታይም።

Horus
Senior Member+
Posts: 30653
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: የዘመናችን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቀውስ

Post by Horus » 24 Jul 2019, 00:15

ከላይ የቀረበው ሃተታ የሚያመለክተው ጉዳይ ቀደም ሲል በትንሹም ቢሆን በኦርቶዶክስ ክርስትና እምነትና በአማርኛ ቋንቋ ዙሪያ ተገንብቶ የነበረው የባህልና እሴት መለኪያ (ደረጃው) እጅግ መዝቀጡን ነው። የብሄረሰቦች ፉክክር ከሰፈነ ወዲህ አገሪቱ ባህላዊና እሴታዊ ህብረተሰብ መሆኗ ጠፍቶ የምዕራብና የምስራቅ ሸቀጣ ሸቀጣዊ ባህል በገፍ የሚራገፍባት ገበያ ሆናለች። በኢትዮጵያ ፖለቲከኞች እንጂ አገር መሪዎች የሉም። የዜጋዎች ደህንነት ባገር አቀፍ ድህነት ማለትም የእምነት ድህነት፣ የፍልስፍና ድህነት፣ የሳይንስ፣ቴክኖሎጂና የፈጠራ ድህነት፣ የሶሻልና ፖለተካ ሳይንስ ድህነት፣ ተዉጧል። በስነ ጥበብ ማለትም በስዕል፣ ጠረባ፣ ሙዚቃ፣ ስነጽሁፍ፣ ቲያትር፣ ውዝዋዜ፣ ስነሲኒማ፣ ስነፎቶ ሁሉ ድህነት፤ በሕግና ስነምግባር ድህነት ጭምር የታጠረ ሁኖዋል። ህብረተሰቡ በጥቂት ያልተማሩ ሃብታሞችና በብዙሃን ያልተማሩ ድሆች ተከፋፍሏል። ከላይ የተዘረዘሩትን መስኮች ሊፈጥር የሚችለው ምሁር ወይም ተሰዷል፣ አለያም ፈጽሞ የለም። ስለዚህ ኢትዮጵያዊያን በአይምሮዋቸው የሚሰሩ ሕዝቦች ሳይሆኑ መደባዊ ክፍፍሉ በሚበሉና በሚራቡ ሰዋዊ እንስሶች መካከል ነው። ይህ ሰቆቃ (ትራጀዲ) እንጂ ሽግግር አይደለም።

Horus
Senior Member+
Posts: 30653
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: የዘመናችን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቀውስ

Post by Horus » 24 Jul 2019, 00:53

ከዚህ መቀመቅ እንዴት እንደሚውጣ የሚያሳይ ብርሃን አለን? ለኢትዮጵያ ወድቀትና ወድመት ምክንያት አገሩ ቀውስ መሆኑ ብቻ ኣይደለም። ከፍተኛ ያስተሳሰብና የመመራመር ድርቀት አለ። ከፍተኛ የፈጠራ አልባነት ጭለማ ሰፍኗል። ትልቁ ችግር የድንቁርና መስፈን ነው። በዚህ ጭለማ ወስጥ ከምዕራብ በሚመጣ ውራጅ ሸቀጥና ባህል አንድም ፋይዳ ለመፈየድ አይቻልም።

ስለሆነም አዲስ ቅድመ መርህ (አዲስ ፓራዳይም) አዲስ መርሃ እሴት (ቫልዩ ፕሪንሲፕል) መፈልሰፍ አለበት ። ይህን መሰል የሃሳብና የፈጠራ ብርሃን በኢትዮጵያ ምሁራን ሁሉ ይሞከራል ብሎ ማሰብ የተሳሳተ ነው። የጎሳ ፖለቲካ የምሁራንን አንድነት አፍርሷል። ተያይዞም ብሄራዊ (አገራዊ) የሃሳብ አንድነት ፈርሷል። በመሆኑም ሙሉ ባህል ወይም አሞሌ ካልቸር፣ የኢትዮጵያ ምልአተ ባህል ሊፈጥሩ አይችሉም፤ እንዳይፈጠር አድርገዋል። የኢትዮጵያ እጅግ መሰረታዊና ወሳኝ ቀውስ (ችግር) መከፋፈል፣ መበታተን ነው። የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ብትንና የቅውስ (ኬዎስ) ስርዓት ነው። ከሃይማኖት እስከ ተራ ሕይወት ሁሉም ብትን ስርዓት ነው።

Horus
Senior Member+
Posts: 30653
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: የዘመናችን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቀውስ

Post by Horus » 24 Jul 2019, 12:57

ኢትዮጵያ ብትን ስርዓት እስከ ሆነች ድረስ ምልአተ ባህል፣ እሴተ ተዋህዶ ያለው ብሄራዊ ሴራ መፍጠር አለመቻል ብቻ ሳይሆን የተበታተኑት ክፍሎች እርስበርሳቸው ይጋጫሉ፣ ይጣላሉ፣ ይወድማሉ። ከላይ የተዘረዘሩት የባልና የፈጠራ መስኮች የሚንቀሳቀሱት በሰዎች፣ በቡድኖች፣ በሕዝብ ነው። እነዚህ የባህል ተሸካሚዎች እስከተበጣበጡ ድረስ አንድ ወጥ ነገር ለመፍጠር አለመቻል ብቻ ሳይሆን ምንም ነገር ሊፈጥሩ አይችሉም፤ አንዱ ሌላውን ስለሚያፈርሰው። ኢትዮጵያ ብትን ስርዓት ብቻ ሳትሆን የግጭት ስርዓት ነች ። የእርስበርስ መጠፋፋት፣ መዋደም፣ የእልቂት ስርዓት ንች ። ይህን መሰል ህብረተሰብ ወደ ታች እንጂ ወደ ላይ አይሸጋገርም። ለዚህ ሁሉ መሰረቱ ኢትዮጵያዊያን ማንም ይሁኑ ከየትም ይወለዱ፣ በአንድ ፈጣሪ የሚያምን፣ በሰው ልጅ ሰባዊነትና ልዕልና የሚያምን፣ በኢዮጵያዊያን ሁሉ ወንድማማችነት የሚያምን አንድ ሕዝብ አለመሆናቸው ነው። ይህን መሰረት፣ ይህን ቅድመ መርህ፣ ይህን ፓራዳይም እውን የሚያደርገው ትውልድ ገና የለም።

Horus
Senior Member+
Posts: 30653
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: የዘመናችን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቀውስ

Post by Horus » 25 Jul 2019, 21:04

ያልኳቸውን ነገሮች በትንሹ ለመድገም፣ ኢትዮጵያ በማንኛውም መስክ ብትለካ ማለትም በሃይማኖት፣ በፍልስፊና፣ በተፈጥሮ ሳይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በሶሺያል ሳይንስ፣ በስነ ጥበብ፣ በሕግና በስነ ምግባር በሁሉም መስክ ቁርጭራጭ ስርዓት ነው። እነዚህ እጅግ ብዙ ቁርጭራጮች በግለ ህልውናቸው ፋይዳቢስ ሲሆኑ በህብረ ህልውናቸው ተጻራሪ፣ ተዋዳሚ፣ ተፋላሚና የግጭት መነሾዎች ናቸው። ስለዚህ ለየብቻም በህበረትም ዋጋቢሶች ናቸው። በግል ለድህነትና ለድንቁርና ተጋልጠዋል፤ ከተባበሩ ይተላለቃሉ ። መውጫ የለሽ ዙሪያ ጥምትም ማለት ነው።

Tog Wajale
Member
Posts: 4918
Joined: 23 Dec 2017, 07:23

Re: የዘመናችን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቀውስ

Post by Tog Wajale » 25 Jul 2019, 21:36

Yes Low Life * Horus *. Blame It On The Liggaggamm Pentte Ahmed Abiyot & Tebettabba Galla Berhanu Nega & You Dingai Rass * Horus *

Horus
Senior Member+
Posts: 30653
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: የዘመናችን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቀውስ

Post by Horus » 25 Jul 2019, 21:44

ከላይ የተዘረዘሩት ችግሮች በኢትዮጵያ ግለሰቦች እና ቡድኖች አይምሮ ላይ ወይም አስተሳሰብ ዘንድ የሚያስከትሉት ተጽዕኖዎች አሉ። የግለሰቦች፣ ብሄረሰቦችና ቡድኖችን የማንነት ትርጉም ለውጠዋል፣ አናግተዋል። እነዚህ የምንነትና የማንነት ትርጉሞች ተበታትነዋል፣ ተፍረክርከዋል፣ ተቃውሰዋል፣ ተዘባርቀዋልም። ተያይዞም እነዚህ ግለሰቦችና ቡድኖች ያሏቸው፣ የነበራቸው እሴቶች ወይም ሰርዓተ እሴቶች፣ አስተሳሰብ፣ መርሆችና እምነቶች ተበታትነዋል፣ ተፍረክርከዋል፣ ተቃውሰዋል። የሞራል ስነስርዓታቸው ላሽቋል፣ ወድቋል። ማለትም ደግና ክፉ፣ ጥሩና መጥፎ፣ ትክክልና ስህተት፣ ፍትህና ግፍ፣ ጠቃሚና ጎጂ፣ ገምቢና አፍራሽ፣ እድገትና ወድቀት፣ ልማትና ወድመት፣ ነጻነትና ባርነት፣ ትልቅነትና ትንሽነት፣ ክብርና ውርደት፣ ራዕይና መታወር፣ ብርሃንና ጭለማ፣ ፍቅርና ጥላቻ፣ የሰላምና ሽብር፣ ስርዓትና ቀውስ በአንድ ቃል ደህንነትና ድህነትን የሚለይ የግምትና የህሊና ተቋማቸው ወይም ችሎታቸው ተቃውሷል። ከላይ የተጠቀሰው መበታተንና መጋጨት የግለሰቦችን አስተሳሰብና ሰነምግባር በመበታተን ላይምሮና የሞራል አናርኪ ዳርጓቸዋል። ማሀበራዊ አናርኪና ያስተሳሰብ ምስቅልቅልነት አይነጣጠሉም። አንዱ ሌላውን ይወልዳል፤ እንዲያውም ያስተሳሰብና የሞራል ስርዓት ሳይኖር ማህበራዊ ስርዓት ሊኖር አይችልም። ብትን ሃይማኖት፣ ብትን ፍልስፍና፣ ብትን እሴት፣ ብትን ፖለቲካ፣ ብትን ስነት፣ ወዘተ የሚፈጥሩት ብትን ህብረተሰብን ነው።

Horus
Senior Member+
Posts: 30653
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: የዘመናችን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቀውስ

Post by Horus » 26 Jul 2019, 02:08

ያስተሳሰብ፣ የህሊናና የሞራል ቀውስ ወይም አናርኪ ውጤቱ የተፋፋመ ቅራኔ ፣ ግጭት፣ ሁከትና ጦርነት ነው።

Horus
Senior Member+
Posts: 30653
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: የዘመናችን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቀውስ

Post by Horus » 27 Jul 2019, 02:26

ያስተሳሰብ፣ የህሊናና የሞራል ቀውስ ወይም አናርኪ ውጤቱ የተፋፋመ ቅራኔ ፣ ግጭት፣ ሁከትና ጦርነት ነው። በኢትዮጵያ የሃይልና የጉልበተኝነት ሚና እየገነነ ይሄዳል። ጦርነት፣ አብዮት፣ አመጽ፣ ወንጀል፣ ሕግ አልባነት በአገሪቱ ይስፋፋሉ። በሰው ሕይወት ላይ እልቂት ይከተላል። የሕዝቦች ቁሳዊ መደላደል (አኗኗር) ይፈርሳል። ያገሪቱ ቁሳዊ ሃብት ይወድማል። ይህ የመጨረሻ ወድመትና ጥፋት ከሚከተሉ ሶስት አዝማሚያዎች አንዱን ሊወድ ይችላል።

Horus
Senior Member+
Posts: 30653
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: የዘመናችን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቀውስ

Post by Horus » 27 Jul 2019, 19:05

አንደኛው አዝማሚያ፣ የኢትዮጵያ ህብረተሰብ በብትንትንነቱና በቀውሱ ለረጅም ዘመን ሊቀጥል ይችላል። ይህም ማለት አገሪቱ ምንም አይነት መሰረታዊ መፍትሄ ሳታገኝ በሞትና በህይወት መካከል አሳዛኝ የሆነው ህልውናዋ እንደ ተንጠለጠለ ሊቀጥል ይችላል።

ሁለተኛው አዝማሚያ፣ የኢትዮጵያ ህብረተሰብ በተወሰኑ ሰፋፊ መሬቶች ፣ ባህሎች፣ ቋንቋዎች፣ ግዛቶች፣ ተከፋፍሎ በአዲስ ፌዴራላዊ ወይም ኮንፌዴራላዊ ስብስብ ሊቀጥሉ ይችላሉ። ኢትዮጵያ በብዙ አገሮች የምትከፋፈለቅ ይህ አዝማሚያ እውን ከሆነ ነው።

ሶስተኛው አዝማሚያ፣ የኢትዮጵያ ህብረተሰብ መሰረታዊ ያስተሳሰብና የእስትራተጂ ለውጥ አድርጎ ስርወ እሴታችን የአንድ ፈጣሪ ገናናነት፣ የሰው ልጅ ልዕልናና የኢትዮጵያዊያን አንድ ቤተሰብነት ሆኖ አገሪቱ ከውድቀት ልትድን ትችላለጭ

beekkaa
Member
Posts: 8
Joined: 19 Jun 2019, 18:59

Re: የዘመናችን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቀውስ

Post by beekkaa » 27 Jul 2019, 19:50

This so-called crisis is the result of a struggle between groups who want to get free from a dependant empire and those who try to save it. But empires can't be saved. That is what happened in Europe. Those small countries in Europe we see today as nation-states were once a lot smaller than ethnic groups in Ethiopia. But they survived by switching sides in the long war for dominance by the big countries. Tribes became countries.

Horus
Senior Member+
Posts: 30653
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: የዘመናችን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቀውስ

Post by Horus » 27 Jul 2019, 20:14

ከነዚህ ሶስት አዝማሚያዎች የትኛው እውን እንደሚሆን የሚወሰነው በኢትዮጵያ ምሁራን መካከል ባለው የሃይል ሚዛንና የማሰብ ችሎታ ነው። ለምሳሌ ያንድነትም ሆነ የብሄረሰብ ምሁራን ከደከሙና አዲስ መፍትሄ ማቅረብ ካልቻሉ ወይም አንዱ ከለላው በልጦ ማሸነፍ ካልቻለ አንደኛ አዝማሚያ እውን ይሆናል።
የብሄረሰብ ምሁራን የበላይነት ይዘው የጎሳ ክፍፍል አሁን ባለው ቀጥሎ ካደገና ካሸነፈ ሁለተኛ አዝማሚያ እውን ይሆናል። የኢትዮጵያ አንድነት ምሁራን ከጠነክሩ ሶስተኛ አዝማሚያ እውን ይሆናል።
ለምሳሌ ሶስተኛው አዝማሚያ ሃይማኖትን በተመለከተ የኢትዮጵያዊያን እምነት ሆነ አምልኮ መሆን ያለበት እግዚአብሄር፣ ክርስቶስ፣ አላህ፣ ያዌ፣ ጂሆቫ፣ ዋቃ፣ ሌላም ሌላም በሚል መናቆር ሳይሆን በአንድ ፈጣሪ ማመን ነው። ቤተ እምነት ሆነ ቤተ አምልኮ ሁሉ የአንድ ፈጣሪ ቤተመቅደስ ሆኖ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ የአንድ እምነት አማኝ አንድ ሕዝብ መሆናቸውን መቀብለና ያንን ማስተማር አለበት ። የኢትዮጵያ ብሄረሰብ ግለሰቦች ሁሉ ማለትም ኢትዮጵያዊ ሰው ሁሉ የአንድ ፈጣሪ ፍጡራን እንደ ሆኑ። እነሱም አንድ ኢትዮጵያዊ ብሄር እንደሆኑ ተቀብሎ የኢትዮጵያ ጎሳ እንደሆኑ ማመንና ማስተማር አለበት ። በተመሳሳይ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ አንድ ቤተሰብ ፣ ወንድማማች እንደሆኑ ማመንና ማስተማር አለበት ።
በእነዚህ ሶስት ስረወ እሴቶች መሰረት የቋንቋ፣ የሃይማኖት፣ የፍልስፍና፣ የስነ ጥበብ፣ የማህበራዊ ሳይንስ፣ የሕግና የስነ ምግባር ውህደቶችን የሚያንጸባርቅ ባህል፣ ፈጠራ፣ ንድፈ ሃሳብ መቀመር ግድ ይላል። የኢትዮጵያ አንድነት ምሁራን ይህን ማድረግ ካልቻሉ የጎሳ ምሁራን አሁን በጀመሩት አጀንዳ ቀጥለው ሕዝቡን በብዙ አማልክጥ በብዙ ጎሳዎች፣ በብዙ ቋንቋዎች፣ በብዙ ባህሎች በመከፋፈል ይህም ውሎ አድሮ ወይ ኢትዮጵያ መከፋፈል ወይም ወደ ኢትዮጵያ ወድመት ማምራቱ አይቀሬ ነው።

Post Reply