Page 1 of 4

ተስፋሚካኤል ትኩእ (1892 – 1964)] - ወለዶና ክነቦ ዝግባእ መኽዘን ታሪኽ

Posted: 06 Jun 2019, 10:02
by Meleket
ናይ ኑረነቢ ማህደር ዚብል ርእስ ዘለዎ ታሪክ ዝኸዘነት መጸሐፍ መሳጢ ብዝዀነ አገባብ ብቋንቋ አምሓርኛን ትግርኛን ብ2017 ተጻሒፉስ ነቢብና አሎና። ዓሰርተ ዓመታት አቐዲሙ፡ ብኣርታኢ ደረጄ ገብሬ ብ2006 ናይ ኣርትዖት ስራሕ ዝተገብረላ “ሀገሬ የህይወቴ ጥሪ” ዚብል ርእስ ዘለዋ መጸሓፍ ናይ ሓደ አቶ ተስፋሚካኤል ትኩእ ዝተባህለ ብመንነቱ ሕቡን ኤርትራዊ ተጋዳላይ ንናጽነትን ሓርነትን፣ ንመግዛእቲ ጥልያን ንምስዓር ብብረት ጥራሕ ዘይዀነ በተሓሳስባን ብብርዒን ዝተቓለሰ ኣቦ “ግለ ታሪክ” ብቋንቋ አምሓርኛ ተጻሒፋስ ነቢብናያ። ሓርበኛ አቶ ተስፋሚካኤል ትኹእ ንዝነበሩሉ ዘመን ብግቡእ መርሚሮምን ተንቲኖምን፡ ንእከይ አተሓሳስባታት እቱይ ዘመን፣ ንሽጣራታት ጥልያንን ኃይለሥላሴን እንግሊዝን ብዉህልነት ዝመልኦ ልቦናን ፖለቲካዊ ብስለትን ዝተንተኑ፣ ኣብ መንጎ ደቂ ኢጦብያ ንዝነበረ ሕድሕዳዊ ምጉርፋጥን ሳዕቤናቱን፡ ኣብ ሞንጎ መራሕቲ ጦብያ ዝነበረ ናይ ስልጣን ሕርፋንን ርኡይ አድልዎታትን ብጭብጢ ብምምጓትን ብምትንታንን፡ ንዝኣመኑሉ ኩሉ ብዘይቀለዓለም ብምትግባር፡ ድንቂ ብዝዀነ ግሉጽነትን ምቕሉል አገባብን ውልቃዊ ታሪኾም “ግለ ታሪኾም” ጽሒፍምልና፡ ንስለ ትግሃቶምን ተወፋይነቶምን ነመስግኖም አሎና። እዞም ሓርበይናዊ ምቕሉል ኣቦ ኣብ ሃገሮም አብ ኤርትራ፣ አብ ዓዲ ጥልያን፣ አብ ሊቢያ፣ አብ ሶማል፣ አብ ሱዳን፣ ኣብ ኢትዮጵያዉን ወዘተ ብጅግንነትን ነቱይ ዝኣመኑሉ መትከል አብ ግብሪ ንምትግባር ዝተቃለስዎ ኩሉ ታሪኾም ብ፲፱፻፵፰ (1948 ኣቆጻጽራ ግእዝ) ጽሒፎም ገዲፎምልናስ ደቆም ብ2006 ንሓንቲ ካብተን 9 መጻሕፍቶም አሕቲመን ንነበብቲ ቀሪበንኣ ኣለዋ። እንተክኢልኩም ሃሰስ ኢልኩም ደሊኹም ንበብዎ። ቅድሚ ሚእቲ ዓመታት ብስለትን ፖለቲካዊ ንቕሓት ኤርትራዉያን አቦታት ማዕረ ክንደይ ልዑል ምንባሩ ክትግንዘቡ ኢኹም።

ገሊኦም ንፉዓት፡ ንትሕዝቶ እዙይ መጸሓፍ ናብ ትግርኛ ክሳብ ዝትርጉምዎ እቶም አምሓርይና ዝርድኣኹም ኣሕዋትን ኣሓትን ቅድሚ 100 ዓመታት ዝነበረ ታሪክን ፖለቲካዊ ሃዋህው ከባቢና ክትፈልጡ እንተደኣ ደሊኹም አብዙይ አለኹም ብዘይቃል ዓለም ዝተጻሕፈ ታሪኽ!!! ነዙይ መጽሐፍ አብ ሕትመት ንዘብቕዓ ደቆም ድማ ነመስግን። ንፉዓት ቢልናዉን ነተን ተሪፈን ዘለዋ ጽሑፋቶምዉን ከሕትማ እሞ ብፍልጠቶምን ብስለቶምን ጥበቦምን ትብዓቶምን “ርእሰ መዃንንት” ናይዝዀኑ ናይ ክቡር አቦና ኣቶ ተስፋሚካኤል ትኹእ ፍልጠትን ልቦናን ጥበብን ትብዓትን ክንካፈል ክተክእሉና ንላቦ።


http://www.mereb.shop/rs/?prodet=true&p ... 283&vid=88



ታሪኽ እሞ ድማ ብኤርትራዉያን ቀዳሞት ኣቦታት ዝተጻሕፈ ታሪኽ ኽንነብቦ ይግባእ እቱይ ምንታይ ንፍተዎ አይንፍተዎ ኣካል ታሪኽናን ታሪኽ ኅብረተሰብናን ስለዝዀነ!ብርግጽ ንታሪኽ እዞም እሙንን መትከላዊን ኣቦ ግን ክንፈትዎ ኢና፣ ብዙሕ ድማ ክንመሃረሉ ኢና! ምስ ነበብናዮን ምስ ኣዀማሳዕናዮን! :mrgreen:

Re: ተስፋሚካኤል ትኩእ (1892 – 1964)] - ወለዶና ክነቦ ዝግባእ መኽዘን ታሪኽ

Posted: 07 Jun 2019, 11:55
by Meleket
ካብ ትሕዝቶ እቱይ መጸሐፍ ሕልፍ ሕልፍ እናበልና እስከ ክነንክሰኩም፣ ንቐደም በሉ! :mrgreen:

በሕግ የተወልደ ሰው ሁሉ ሕግን ያከብራል፤ የሚፈረድለትንና የሚፈረድበትን በትክክል አስቀድሞ ያውቃል።" ገጽ 1

"ከዕለታት አንድ ቀን ሁለት ሴቶች ወደ እናቴ ወደ ወይዘሮ ሥላስ ዓንዱ ዘንድ መጡና የባለታሪኩ የከንቲባ ዓንዱ ልጅ ሆነው እንዴት ጌጥ በጆሮዎና ባንገትዎ፣ በጣትዎና በእግርዎም አያስሩም ብለው ቢሉዋቸው እኔና ፫ቱ ወንድሞቼን ጠሩንና እፊታቸው አቁመው “ተስፋሚካኤል፣ ሰሎሞን፣ በርሔና ዮሐንስ እነዚህ ናቸው የኔው ጌጥ” ብለው መልስ ሲመልሱላቸው እነዚህ ሴቶች በወይዘሮ ሥላስ ንግግር ተደንቀው ዝም ብለው ቀሩ።” ገጽ 4

“አባቴ አቶ ትኩእ ተመልሶ ፲ ዓመት ያህል ሲሆነኝ ቄስ ትምሕርት ቤት በተመላላሽነት ቢያስገቡኝ እኔ ግን የትምህርት ጥቅም ሳልረዳው መሳይ በሌለው ስንፍናዬ የተነሳ ከናቴና ካባቴ ሳልለይ ወተት መጠጣት እንዳይጓደልብኝ ብዬ ገና ትምህርቱን ከመጀመሬ እምቢ ብዬ ካባቴ የከብት እረኞች ጋር ጥጆችና ላሞች እየጠበቅኩ እረኛ መሆኔን በመምረጤ ምን ጊዜም ቢሆን እየከነከነኝ እጅግ ከመጸጸቴ ምንም አላቋረጥኩም።” ገጽ 4

“ላብነት አባቴ በሌሉበት ቀን ሰዎች ተቸግረው ገንዘብ ብድር ወይም ስጦታም ቢጠይቁዋቸው ካባቴ እናቴ ሙሉ ፍቃድ ስለተሰጣቸው መልካምዋ እናቴ ፫፻ ጥሬ ብር ያለ ደረሰኝ፣ ያለ እማኝ ብድር ሲያበድሩ አየሁ፤ ሀገሬውም ራሱ ይመሰክራል። ዛሬ ግን የሸዋ ሰው እንዃንስ ያለ እማኝና ያለደረሰኝ ገንዘብ ማበደሩ ይቅርና በዕማኞች ፊት ራሱ ደረሰኝ ብሎ ለተበደረው ገንዘብ ሁሉ “ፊርማየ አይደለም” “ፊርማህ ነው” በመባባልና ፈጽመው በመካካዳቸው በዬ ፍርድ ቤት ሲመላለሱ በማየቴ በብዙ ተደነቅሁ፤ የትውልድ ሀገሬንም በብዙ አመሰገንሁ። . . ." ገጽ 5

ጠባቂ የሌለው ሕዝብ ጨው እንደሌለው ምግብ ነው። ጠባቂ የሌለው ሕዝብ ሽባ ሆኖ ማንም እንደሚጫወትበት እንደዚሁም ጨው የሌለው ምግብ የሚመገብ ሕዝብ ሁሉ የእከክ ደውዬ ወርሶት ያንቀላፋል፤ ደስታ ተለይቶትም በኅዘን ይኖራል፤ የእከካሞችና የበሽታዎችም መጫወቻ ሆኖ ማንም እንደሚጫወትበት እንደዚሁም ጨው የሌለው ምግብ የሚመገብ ሕዝብ ሁሉ የእከክ ደውዬ ወርሶት ያንቀላፋል፤ የእከካሞችና የበሽታዎችም መጫወቻ ሆኖ ይቀራል።” ገጽ 9

“ባሪያና ጨዋ ማለትም፤ በጥቁረቱና በቅላቱ ወይም በነጭነቱ ቀለም ልዩነት አይደለም። ባሪያ ማለት የፈቀደውን ለመሥራት የማይችል፣ በሰው ኅሳብና በሰው ፈቃድ፣ በሰው ትእዛዝ ተመርቶ የሚሔድ ዓይነ ስውር፣ ሕይወቱ በጌታው እጅ የሆነ ሰው ነው። ጨዋ ማለትም የገዥ ዘር በመሆኑ አይደለም። ለሕዝቡና ለሀገሩ፣ ለመንግሥቱና ለወገኖቹ ብሎ መስዋዕት የተሰዋና ትልቅ ባለታሪክ ሠሪ ከመሆኑ በቀር።" ገጽ 9

"ምንም እንኳ በጀግናው አጼ ቴዎድሮስ መንግሥት ጊዜ ኤውሮጳና ኢየሩሳሌምም በወንድነታቸው ተንቀጥቅጠው ቢሸበሩም አጼ ቴዎድሮስም ራሳቸው ባባታቸው ሐማስኔም ቢሆኑ እስከ ኃላይም ቢመጡ በሠራዬ ወደ ወልቃይት ተመለሱ እንጂ ወታደር በሀገራችን ሳይገባ ያመት ግብር ብቻ በባላባቶቹ እጅ እንልክ ነበር” ። ገጽ 11

“በዚያን ጊዜ በደጃዝማች ባህታ ሐጐስ የትንሹ አጎቴን ልጅ ፊታውራሪ መሐሪ ሰለሞንንና የደጃዝማች ሰንጋልን ልጅ ፊታውራሪ ሐብተዝጊንና ብዙ ሹማምንት እንዲሁም ወታደር ይዘው ከዓገመዳም ለመራቅ ወደ ዘመዶቻቸው ሀገር ወደ አስገደ ሀባብ፣ ወደ ከንቲባ ኦስማን ሀገር ሔደው ተቀምጠው ሳለ፣ በእንግሊዝ ሰንሰለት የተጐተተው የጣሊያን ንጉሥ ወታደር በ፲፰፻፸፰ ዓ.ም. በደሴትዋ ምጽዋዕ ገባ። ከዚሁም ደሴት ቱርክና ግብፆች ለጣሊያን አንለቅለትም ቢሉ እንግሊዝ አስገድዶ፣ ረዳት እንዲሆንለት ብሎ እንግሊዝ አስወጥቶ ጣሊያን እንዲስፋፋ አድርጎ ወደ ገነትዋ ኤርትራ አስገባው፤ ረዳውም።" ገጽ 13

"አልጋ ፈላጊ ሆነው በአሳኦርታና በጠልጣል እያሉ በጽናት ሲቀመጡ የነበሩበትን የደጃዝማች ደበብ አራአያም የ፲፪ ዓመት ልጅ ወንድማቸው ልጅ አብርሃ አርአያን መያዣ ሰጥተው ፫፻ ወጨፎ ጠበንጃ ከነ ጥይቱ ከጣሊያን መቀበላቸውን ደጃዝማች ባህታን ለመግደል መሰናዳታቸውን ስለ ሰሙ የደጃዝማች ባህታም ከሀባብ ወደ ምፅዋዕ በመምጣት ለጣሊያን እጃቸውን ሰጡ።" ገጽ 13

"እኔ ተስፋሚካኤል ትኩእ ካባቴ በዘላኒነት ከብት ጠባቂዎች ጋር ለብቻዬም ሁኜ ከብት ስጠብቅ ሳር ሳላጠግባቸው፣ ጥሩ ወኃ ሳላጠጣቸው ወደ ቤቴ እንደማልገባ ማንም ሰው ዘንድ የታመነና የተመሰከረም ነበር። ያለ ኅሳብ ባባቴ ቤት ስኖር ረሀብና ጥጋብ፣ ኅዘንና ደስታ ምን እንደሆነ ሳላስብ፣ ሕይወቴንም ሳልቆጥብ፣ ትዕግሥትና ትህትና ለሚያሳየኝ ሰው ሁሉ ስታዘዘውና ስገዛው፤ እበልጥህአለሁ ብሎ ለሚለኝ ሰው ያለ ማቋረጥ በፍጥነት የምጣላ አደገኛው ልጅ ነበርሁ። ምንም እንኳ ያባቴና የናቴ ቅጣት ከፍ ያለ ስለሆነ ብፈራም ለሚመታኝ ይቅርና ለሚሰድበኝም ሰው ቢሆን እምሰጠው መልስ ወዲያው ፈጣን በሆነው ብትር ደሙን ማፍሰስ ነበር።" ገጽ 17

"ከብትም ሳግድ ሳለሁ እነዚህ የጠላት ከብቶች ናቸውና ልተዋቸው፣ እነዚህ ግን የወዳጆቼ ናቸውና ልሰብስባቸው ብዬ እማደርገው አንዳች ልዩነት ምንም አልነበረኝ፤ ለሰው ሁሉ ከመታዘዝ በቀር፣ ስለምን ያባቴንና የናቴ ፊት ለማየት ባለመቻሌና ኅሊናየም እሽ ስለማይለኝ ነው። ተጋፊ ሆኖ ለሰደበኝ ልጅ ግን ፈንክቸው ቅጣት ቢቀጡኝም ምንም ዓያመኝም ነበር፤ ስለምን ኅሊናየ እሽ ዓይለኝም፤ እንኳን በራሴ ይቅርና በማንንም ሰው ጥቃትና ውርደት ሲደርስበት እንቅልፍና ዕረፍት ስለማይወስደኝ ምክንያት ነው።" ገጽ 17

"እኔም እንጀራ እናቴን እንዳየሁ እለቱን ካባቴ ቤት ወጥቼ የጠላሁትን ትምሕርት ቤት ፍለጋ ሁለት ብር ብቻ ስንቅ ሰንቄ ከዓገመዳ ከነ እንጋሎ ከተባለው ቦታ በጋደትና ዘአረዳ ደቡብ ዓዳረሶ ግንዳዕ አስመራ ወጣሁ።" ገጽ 18

"ከሁለት ወር በኋላም እኔና ሁለቱ ጓደኞቼ መብራህቱ ኪዳነ የዛሬ ብላታ መብራህቱና ገብረ ማሪያም የሚባል የአኩሩር ልጅ ሆነን ከአሥመራ ወደ ከረን ትልቁ ትምህርት ቤት ለማለፍ ስለተፈቀደልን በብዙ ደስታ እንደ አበባ ፈንድተን ስንሔድ፣ በመንገድ መሳይ የሌለው ትኩሳት ጀመረኝና በግድ አተከሌዛን በአሰብ ታሥረው የሞቱት ደጃዝማች ሐድጎ አምበሳ ሀገር ገባን።" ገጽ 18

"ገብረማርያምም በምጽዋዕ ግምሩክ በ፷ ሊሬ ለወር ገባና ተደነቀለት፤ እኔም የምጽዋዕን ሙቀት ብጠላ ነው እንጂ ፴ ሊሬ ይቀበሉኝ ነበር። የአሥመራን ፲፭ ሊሬ በወር መርጨ የመንግሥት የጽሕፈት መኪና ትምሕርት ሥራ ገባሁ፤ በዚሁም ሥራ ለራሴ ከመማርና ወረቀት ከመጨረስ በቀር እምሠራው ሥራ አልነበረኝምና ግዙፍ በሆነው ድንቁርናዬ ምክንያት፣ ከዚህ ቀደም ከ፭ኛ በጦሎኒ ትሪፓሊ ወርደው፣ ሮማ ጐብኝተው የመጡት ዘመዶቼ ስብከት ቢሰባብኩኝ አምኜ፣ እኔም ሰው ሀገር ኸጄ ለመሞትና ሰው ለመግደልም ሞያ መስሎኝ ፈቃድ ጠይቄ በአነጋጋሪነት ከነሱ ጋር ከ፰ኛ በጦሎኒ ከአሥመራ በታህሣሥ ወር ፲፱፻፮ዓ.ም. ቸረናይካ አደርና ከተማ ወረድን።" ገጽ 21

"እውነትም ወደ ትሪፓሊ የኼደ ሰው በ፫ት ክፍል ይከፈላል። ፩ኛ እንደኔ ስብከት ተሰብኮ ፪ኛ በጥጋብ ጦርነት ኸጄ ሰው እገድላለሁ፤ ሞያ እሠራለሁ የሚል ሲሆን ፫ኛ በሬ ገዝቼ አርሳለሁ፤ ላም ገዝቼ አልባለሁ ከድህነት ብረታዊ ቀንበር እወጣለሁ በሚል ኅሳብ ሲሔዱ በስብከት ትሮፓሊን ያህል ሩቅ ሀገር ኸጄ አንዳች ደምነት ከሌለው ሕዝብ ጋር ለመጋደል ሔዶ የሀገሩን ሰው መግደል ከሕግ ውጭ የሆነ ዕብድነት ሲሆን፤ ለባዕድ መንግሥት ሞያ እሠራለሁ ማለትም ከሁሉ የባሰ ስህተት ነው። በሬ ገዝቼ አርሳለሁ፤ ላም ገዝቼ አልባለሁ፤ ከድህነት ብረታዊ ቀንበር እወጣለሁ ማለትም እንሞታለንን ረስተው ነው። በዚሁ የማያቋርጥ የ፲፫ ዓመት ጦርነት ከሞቱ በኋላ ምኑን አለፈላቸው? "ገጽ 22

"በዚህ ጊዜ ሁሉ ትሪፓሊ ሲሄዱና ሲመለሱም የነበሩት ሰዎች ኤርትራዊያን ብቻ ናቸው ወይ? አይደለም፤ ከሁሉ የበለጡ ጎጃሞች ሲሆኑ፣ ይመላለሱ የነበሩት ሰዎች ከድፍን ኢትዮጵያ ናቸው። ለዚሁም ከድፍን ኢትዮጵያ ተሰብስበው ትሪፖሊ እየሄዱ እንደ ቅጠል ረገፉ። ከረገፉትም ካ፲ አንድ ቀርተው፣ ጥቅት ብሮችም ይዘው ከአሥመራ ወደ የሀገራቸው ለመሔድ መረብ ሲያልፉ እንዳይገቡ ኅዘኔታ የሌላቸው የኢትዮጵያም ሀገር ገዥዎች በፈቃዳቸው የእነዚህን ድሆች ቀረጥ መቅረጫ በሮች አበጅተው ቀረጥ መቅረጣቸውም መንግሥት እያየና እየሰማም አላስጣላቸውም ነበር።" ገጽ 22

"ንጉሥ ተክለሃይማኖት ገንዘብ የናቁ ነበሩ፤ ከራስ በዛብኽ እና ከደጃዝማች በለው ሌላ ደጃዝማች ሥዩም የተባሉ፣ ገንዘብ ወዳድ በመሆናቸው የታወቁ፣ አማርኛ አዋቂ ራስ ኃይሉ ተብለው ሞላው ጎጃምን ገንዘባቸው አደረጉ። ልጅ የሌለውንና ትሪፖሊ ሂዶ ገንዘብ፣ ልብስ ያመጣውን ወረሱ። እሳቸውንም በፈንታቸው መንግሥት ወረሳቸው። በ፲፱፻፪ ዓ. ም. ራስ ኃይሉ ለሐማሴኔው ለፊታውራሪ ጊላጊዮርጊስ አባቴ ንጉሥ ተክለሃይማኖት ፬፻ ብር ዕዳ ትተውልኝ ሞቱ እኔ ግን ይኸው ፲፮ ዓመቴ ነው፤ ጎጃምን በብዙ ሀብትና በብዙ ደስታ አስተካክዬ እገዛለሁ ብለው አሉዋቸው። “እርስዎ ራስዎ ጎጃምን መልካም አድርጌ እገዛለሁ ይላሉ፤ ነገር ግን የጣሊያን መንግሥት ወዳጅዎ ስለሆነ ትሪፖሊ ሔደው ስንቱ ጎጃሞች እንደሞቱና ስንቱ አካላታቸውን እንደተቆረጡ፣ ስንቱስ በጦርነቱ እንደሚያገለግሉት ለይቶ ዝርዝራቸውን ቢጠይቁት በደስታ ይሰጥዎታል። በከንቱ ትሪፖሊ እየሄደ ያለቀውን የጎጃም ሕዝብ ቁጥር ሲያውቁት በደስታ መኖሩንና ለጠላቱ መንግሥት ሲያገለግል በብዙ ሺህ የሚቆጠር ጎጃሜ መሞቱን ሊረዱት ይችላሉ”። ሲሉዋቸው ልዑል ራስ ኃይሉ አንተኮ የማትናገረው የለህም” በማለት መልሰው ዝም አሉዋቸው። ስለምን የጎጃም ልጅ በከንቱ ጠላት ሀገር እየሔደ ቅኝ ሀገር ማበጀቱንና በከንቱ እንደቅጠል መርገፉን አላሰቡም፤ ከሞት የቀረው የሚያመጣላቸውን ብርና ምንጣፍ ፣ ልብሳልብስ እና ዕቃ በቀር።" ገጽ 23

"አንድ ለመንግሥቱ ታማኝ የሆነ እንግሊዛዊ ሻምበል በነጭ ዓባይና በጋምቤላ ወኃ መገናኛ የሚኖሩትን ኑወር ለመመርመር አንበሳ አድናለሁና ከኢትዮጵያ መንግሥት በመንግሥቱ በኩል ጠይቆ ፈቃድ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስተር ተሰጥቶት በደስታ አደን አድናለሁ ብሎ መጥቶ የኢትዮጵያ መንግሥት የውጭ ጉዳይ ሚኒስተር ፊርማና ባለ አንበሳ ማኅተም ለባላባቱ ሰጠሁት። እሱም በደንብ ተቀበለኝና እኔም ደመወዝ እምሰጣቸው ሰዎች ስጠኝ ብዬ ጠየቅሁት፤ ብጠይቀው፣ ልብስ የሌለው፣ ፊደል የማይውቅ የኑወር የሻንቅሎች ባላባት፣ ለኔ ለእንግሊዝ ካፒቴን እንዲህ ሲል መልስ ሠጠኝ፤ አንተ አደን አድነህ የሀገሬን አንበሳ እንድትገድል ከኢትዮጵያ መንግሥት ተፈቅዶልሀልና ግደል፤ እኔ ግን የሀገሬን አንበሳ እንዲያጋድሉህ ብዬ እምሰጥህ ሰዎች የለኝም” ብሎ በቁጣ ቃል መልስ መለሰልኝ ሲል እንግሊዛዊ ካፒቴን ራሱ መሰከረ።" ገጽ 24

"በዚህ ግዜ ይህ ሰው በዱር እንደሚያስገድለኝ ተረዳሁት፤ እና ተመልሼ በመጣሁበት መንገድ አደን የሚሉት ሳላድን ካርቱም ተመልሼ ገባሁ። እንደዚህ ያለ በሀገር ፍቅር የተነደፈ ብርቱ የኢትዮጵያ “ላቅንሻ” ገጠመኝ የሀገሩም አንበሳ እንዳይሞትበት በማሰቡ ከፍ ያለውን ምስጋና ይገባዋል ሲል እውነተኛው ጨዋው የእንግሊዝ ጦር ሠራዊት ካፒቴን በጽሁፍ አመሰገነው። ይህ ባለ ታሪክ የኑወር ባላባት ለሀገሩ አንበሳ ይህን ያህል ሲያስብና አጥብቆ ሲያዝንለት እንዴት ለጠላት መንግሥት ትሪፓሊ ሔደው ለሚሞቱትና ከሞትም የተረፉትን ሳይታዘንላቸው ቀሩ?" ገጽ 24

"የቼሬናይካ ስጋና ወተት፣ ማርና ቅቤ ጣዕሙ እንደ ኤርትራ የተዋበ፣ ባለመዓዛ ጣፋጭም ነው። በዚህ ቀንና በዚህ ቦታ መድፍ በከተማይቱ ላይ ተኩስ ተተኩሶባት ስለነበረ አንድት የዐረብ ሴት መድፍ አቁስሎዋት ሞታ ሳለች ሕፃን ልጅ ሲጠባት ስላየሁት ሰውነቴ ተለዋወጠ፤ አዘነ፤ ዛሬም ሳስበው አዝናለሁ። ሕፃኑ ልጅ ለሐኪም ተሰጠ። እናቱ ግን በመድፍ ከወደቀችበት ቀረች።" ገጽ 25

"እኛም እምቢ ብለን ሮማ ለመሄድ ማርሳሱሳ ወረድን፤ ፲ኛው ባታዮም ለውጣችን ከኤርትራ ደረሰና ተክኒስ ሔደው ከ፬ኛ ዲቪዚዮን ኣዛዥ ጀኔራል ቶረሊ አልፎንሶ ጋር በዐረብ ጦርነት ሁሎቹ ወዲያውን በመገደል ተፈጸሙ። አለቁም። እኔም በድንቁርናየ ብዛት ቼረኢናይካ፣ ማርሳሱዛና ሮማም በመሔዴ አዝናለሁ።" ገጽ 25

"ገና ከቼሬናይካ ሳንነሳ በማርሳሱዛ እንደገባ ዕለቱን ንዳድ በሽታ ያዘኝ፤ ለሞት አደረሰኝ፤ ስወድቅ ሳልነሳም በመርከብ ናፓሊ ደረሰን። ዑፍሴፎቹም አስቀድመው ሀገራችን ሌባ ዘማዊ ሀገር ነውና በብዙ ተጠንቀቁ ብለው ቢያስጠነቅቁንም ከሰዋቺን እጅግ ብዙ ሰዎች ተሰረቁ። የናፓሊም ሕዝብ ከሌብነቱም በላይ ለማኝነቱ ሊወራ ዓይቻልም።" ገጽ 26

". . . ስለዚህ መጥፎ ሥራ መሠራቱ ያሳዝናል፤ በዚሁ ምክንያት አንስተን ከወርቅ መሐንዲስ ከሙሴ ፓራሶ ጋር በ ፲፱፻፵፩ ዓ.ም. ለቀምት በኒኖ ሄቴል ስንነጋገር “እኔ ፓራሶ በዚህ ሀገር ስኖር ፵ ዓመት አልፎኛል፤ እንኳንስ ለመጥፎ የዙረት ሥራ ይቅርና ለምሽትነት በጋብቻ ቢሉዋትም እሽ የምትል ሴት አልነበረችም፤ ዛሬ ግን ያ የረከሰው የጣሊያን ወታደር ክፉ የዝሙት ሥራ መሥራት ስላስተማራቸው ሴቶቹ ለወንዶቹ በግድ ሲያስገድዱዋቸው በማየቴ እጅግ አድርጌ በብዙ አዝናለሁ” ብሎ አለቀሰ። ስለ የኢትዮጵያ ቅዱስ ሕዝብ በኢጣሊያኖች ምክንያት መርከሱን እየደጋገመ ነገረኝ። ይህም ፓራሶ ራሱ ጣሊያን ሆኖ በኢትዮጵያ ለቀምትና አዲስ አበባ ሴቶች መለወጥ አስፍቶ በኅዘን ነገረኝ-የድሮም ደግነታቸውን ጭምር።" ገጽ 28

"ከሠልፉም ቦታ እንደተመለስን ሳንቆይ ወደ ሲኦላዊ እሳተ ጐመራ የሆነው ናፓሊ ተመልሰን ገባንና ከምድር ባቡር ወደ ባህር መርከብ ተላለፍን፤ ምጽዋዕ በ፲፭ ቀን ደረስን፤ ሕመሜ እየባሰ ሔደ፤ የባሰብኝም በሻይ ላይ ያለ ልክ ሱኳር እየጨመርሁ በመጠጣቴ መሆኑን ተረዳሁት፤ ሐሞትም ራሴን አዞረው። በአልጋ ላይ እንደወጣሁም ምጽዋዕ ገባሁ፤ ሙቀቱ እጅግ ነበር፤ ወሩ ሐምሌ ስለሆነ በሙቀቱ ላይ ትኩሳት ሲጨመርበት በሽታዬ ሌላ ሆነ፤ ሰው በህመም ብዛት ዓይሞትም በሰማይ ካልተወሰነ በቀር።" ገጽ 29

"በዚሁ ሆስፒታል ከ፷ የማያንሱ የኛ ሰዎች ከኔ ጋር ገቡ። ከጦርነቱ የቀሩትም ብዙ ሰዎች በየቀኑ ፫ና ፬ት እየሞቱ አለቁ። እኔም ምንጊዜም ሐኪሞቹ ባላምንና ብፈራም በብዙ ተጠራጠርሁ፤ ሲያነጋግሩኝም የነበሩትም ሰዎች እንደገና በሞት ረገፉ፤ በየሰዓቱም በቅጽበት ተለዩኝ። እኔም አሁንም አሁንም በበለጠ ሐኪሞቹን ፈራሁዋቸው፤ ያለማቋረጥም እንድጠረጥራቸው እውነት ነበረኝ፤ ስለምን ጣሊያን የኢትዮጵያን ሕዝብ ቁጥር ለመቀነስና ወጣቶችዋ ሲፈጸሙ ሰተት ብሎ ገብቶ ለመያዝዋ ባለብዙ ምኞት መሆኑን በብዙ መንገድ አረጋገጥኩና በጥንቃቄ ላይ ጥንቃቄ ጨመርሁ። እግዚአብሄር ስላልፈቀደም ከዐረብ ጥይት የባሰውን ከሐኪሞች በተለየም “የዶክቶር ሮኮ” ሕክምና መርፌና መድኃኒት ተረፈሁ። ተመስገን አምላኬ።" ገጽ 29

"ከሐኪም ከሮኮ ጋር ከተጣላን ወዲህ የሰጠኝ የማናቸው መድኃኒት ሁሉ በአፍዬ አገባሁት እንጂ እያወጣሁ ወዲያውን ወደ ባህር እንደምወረውረው ምንም አላወቀብኝምና “፲፭ቀን አሥመራ እንድታርፍ ፈቅጀልህ አለሁ” ብሎ ጻፈልኝ።" ገጽ 30

"ጀግናው የኢትዮጵያን ንጉሠ ነገሥት ደፋሩ አጼ ቴዎድሮስ “እግዚአብሔር የሰውን ኃጢያት የሚሰፍርበትን ቁና ነው ሲሠፋ የሚውለው” ብለው ያሉት እውነት ነው። እግዚአብሄር ይግባኝ የሌለበት እውነተኛው ፍርድ ስለሆነ ፍርዱ በሰው ሲጫወት የነበረውን ዶክቶር ሮኮ እንደተጫወተ አልቀረምና እሱም የእጁን አገኘ። በሰው እጅ አብዶና ስቃይ ተሰቃይቶ ተዋርዶ በመጥፎ ሞት ስለሞተ ሰው ሁሉ የእግዚአብሔርን መንክራትና ተአምራ በብዙ አደነቀ፤ አመሰገነውም።" ገጽ 30


Re: ተስፋሚካኤል ትኩእ (1892 – 1964)] - ወለዶና ክነቦ ዝግባእ መኽዘን ታሪኽ

Posted: 08 Jun 2019, 06:03
by Meleket
በያንዳንዱ አንቀጽ ውስጥ ያለውን ረቂቅ መልእኽት ከቻላችሁ ፈልፍላችሁ አግኙት! ሰውየው የዋዛ አይመስሉም! :mrgreen:

“በእብደቴ ከሔድሁበት የቼሬናይካ ጦርነት ተመልሼ የጣሊያንን ሀገር ሮማን ጎብኝቼ ከተመለስኩ በኋላ ሰው ያልሆኑ ልዩ የእግዚኣብሔር ፍጡሮች አድርገን ስናያቸው የነበሩትን ኢጣሊያኖች እንደ እኛ አንዳች ብልጫና ልዩነትም የሌላቸው ሰዎች የዓዳምና የሄዋን ልጆች መሆናቸውን በትክክል አውቀን ትንሽ በትንሽም አእምሮ ገዛን።” ገጽ 31

“በሥራዮ መመለሴም ከቁም ነገር ቆጠርሁት፣ ፈረንሣዊ ለመማርም አሰብሁና ፊደል ስቆጥር ኢጣሊያኖች እንዳይጣሉኝ ስለፈራሁ የጽሕፈት ቤቱ ደብዳቤዎች በጣሊያንኛ አጻጻፍ ከወዳጄ ከጴጥሮስ ኢዶ ስማር ወደ የአሥመራ ከተማ ዙሪያ ገዥ ጽሕፈት ቤት አዞሩኝ። የዚሁም አለቃ አንድ ጥዮ ቢኒፋስ የተባለ በጉቦ የታወረ የጣሊያን ጸሓፊ አጥብቆ ጠላኝ፤ እያሳደደም ክፉ ደብዳቤ ጻፈብኝ፤ በሐሰትም አጠቃኝ። ንቀት መናቁንና ኩራት መኩራቱም ከልኩ አልፎ የተረፈ ነበር፤ ቅጥፈቱ ታውቆ ከሥራ እስክያስወግዱት ድረስ እውነት በሌላቸው ራፖሮቹ እኔን ሽባ አደረገኝ።” ገጽ 31

“የአሥመራ ዙሪያ ሀገረ ገዢም ኮመንዳቶረ ካቫሊ የተባለ በጥየ ቦኒፋስ የሐሰት ስብቅ ምክንያት የኔን ስም ለማንሳት ከመጥላቱ ብዛት የተነሳ “ያን ኩራተኛውን ጥሩት” ሲለኝ ነበር። ስለምን ወደ ቢሮው ሲገባና ሲወጣም ጫማውን ለሚጠርጉለት ለነ ባሻይ ምሕረተአብ ጫማውን በመጥረጋቸው ስድብ ስለምሰድባቸውባ ጐንበስ ብዬ እጅ ሳልነሳው እየተጋፋሁት በመግባቴና በመውጣቴም ብቻ ሳይሆን ቦኒፋስ በሚሰጠው የዕለቱ ወሬ በብዙ ጠላኝ። ከሁሎቹም ጋር አውቆ አጣላኝ።” ገጽ 31

“ወደ ፈተናም ተጠርቼ ቀረብሁና “ፈተናውን ወጥተሃል” አሉኝ፤ በሁለተኛው ፈተና ግን ወድቀህ ስለቀረህ ከሥራም ወጥተሐል” ሲሉኝ ጊዜ ዕለቱን ከአቶ ተክለ የኃላይ ልጅ ጋር ካሥመራ ወጥተን ቅናፍና አደርን። ከዚያም በኣንጉያ አድርገን፣ በባለ ታሪክ በአባ ገሪማ አድርገን ዓድዋ ገባን፤ በዚያም ጊዜ ትግሬን የሚገዙ ልዑል ራስ ሥዩም ነበሩ፤ ደፋሩ ልጃቸው ደጃዝማች ካሣም ሸፍተው በእርቅ ፩ሺህ ያህል ሰው ይዘው በታህሣሥ ወር ፲፱፻፲ዓ. ም. ሲገቡ ዓየሁ። ከዚያም ጓደኛዬ ተክለ ዓድዋ ስለቀረ ብቻዬን ወደ መቀለ መንገድ ስቀጥል ገና ከዓድዋ ስወጣ አንድ ከአኵሱም መጣሁ የሚል ጐበዝ ገጠመኝና ለጦቢት የሸኘው ቅዱስ ሩፋኤል ለኔም መጣልኝ ብዬ ፈጣሪዬ አመሰገንሁ። ከሽፍቶቹም ድነን መቀለ ገባን፤ ከዚያም ደሴ።” ገጽ 32

“በዚሁም ጊዜ በእንድርታ የነበረውን ሀብትና ለምለም፣ ቄጠማና ወኃ፣ በበለጠም ከአምባ አላጄ እስከ አላማጣ የነበረው ቦታ ሁሉ የፊተኛውን ዓመት ክምር ሳይወቃ እንደገና የገብስና ስንዴ ክምር ሲከመርና ግማሹ አብቦና እሸት ሆኖ፣ ግማሹም በቡቃያ አጌጦ የደስደስ ያለበት ሀገር የምድር ገነት ማለት አምባ አላጄና ማይጨው ኮሮም ነበር። ጣሊያን በ፲፱፻፲፩ዓ.ም. ከረገጠው ወዲህ በ፲፱፻፵፩ ዓ.ም. ሳየው ግን ያ ሀብቱንና ወኃው አልቆ፣ ዛፉ ተቆርጦ፣ አበባው ረግፎ ግርማው ተገፎ ሳየው አስለቀሰኝ። በኃጢያቴም አዛንሁ፣ ከአሥመራ እስከ ደሴም እባካችሁ ኑ ብሉልን፤ ኑ ጠጡልን ኣየተባልን ጥቂት ብሮች ስንቅ ይዘን በሰላም ያለ አንዳች ችግር እንኳንስ ልንታመም የታመመውን ሰው ምንም ሳናይ ወሎ ገባን፤ በወሎም ብዙ ሹም ሺር ሲደረግ ደረሰን። ደሴም ከሠራዊት ብዛት ድንኳን መትከያ ቦታ አልነበረም።” ገጽ 32

“በደሴ እንደገባን የጣሊያ አነጋጋሪ ብላታ መሐመድ ፈረጅ፣ የባንዳ አለቃ ባሻይ ተፈሪ ሌሎቹም የአከለጕዛይ ሰዎች ከቆንሱሉ ከኮንተ ፊሊጶስ ማላሳኒ ጋር አገኘሁዋቸውና “አትሔድም ትጣፋለህ ብላችሁ ተከራከሩት” የተባሉ ይመስል ለመሔድ ከለከሉኝና ቁንስሉም ነግረውት ጠርቶ የጣሊያን ቋንቋ አስተማሪና ጸሐፊም ሆኑህ ሥራ አለኝ። እኔም እሽ ብዬ ሥሠራ ኮንተ ማላሳኒ ወደ ሀገሩ ለመሔድ ሲነሳ በለውጡ ካቫሊዬር ዶሮሲ መጥና የዚሁ ልጅ አደራህን ብሎ አለው፤ ለኔም አስጠነቀቀኝ ወድ አሥመራ ተነስቶ ሄደ። እማስተምራቸውም የነበሩት የመኳንንት ልጆች ዣንጥራር አስፋው ገብረ መድኅን፣ ሐሰን በላይ ተፈሪ፣ አምሳለ ሰሎሞንና ሴቶችም ልጆች ነበሩባቸው። የፈረንጂ እጅ ለመጨበጥ የሚጸየፉ ራስ አባተም በዚያን ሀገር እሥረኛ ሆነው፣ ነዋሪነታቸው በዓዲ አቡን የነበረ አቡነ ጴጥሮስም ከአጼ ዮሐንስ ዘር በአዅሱም እንዳያነግሱ ተብሎ በማስገደድ ከትግሬ ወሎ አምጥተው የንጉሥ ሚካኤል አቡን አድርገው በደሴ ተቀማጭ ስለነበሩ፤ ለምሣ ቁንሱል ጋብዞዋቸው አሳማ መብላታችውን ሲጠይቃቸው አነጋጋሪ ነበርሁና ”ና አም” አዎን ሲሉ መለሱለት። ቅዳሴም በዐረብኛ ሲቀድሱ እሠማቸው ነበር።” ገጽ 32

“በ፲፱፻፷ ዓ.ም ንጉሥ ሚካኤል በብዙ እጀብ ታጅበው ከቢተወደድ ወሌ ቤት ተመልሰው ወደ ግቢ ሲሔዱ በጣሊያን ቆንሱል ደጃፍ ቁመው በበቅሎ ላይ ሆነው “ኮንቴ ማላሳኒ አለ” ብለው ጠየቁኝ፤ እኔም “ንጉሥ ሆይ የሉም” ብዬ መለስሁላቸውና ሔዱ። ንጉሥ ሚካኤል ብርቱ፣ ባለ ግርማ፣ ጢማምና ቁመተ ረጅም፤ ሃያማኖተኛ የአጴ ዮሐንስ የክርስትና ልጅ፣ ትግሮቹን የወደዱና ያከበሩ እውነተኛው ሚካኤልም ነበሩ።” ገጽ 32

“ከዚያም ቀን በፊት የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት መሪ ልጃቸው ልጅ ኢያሱ ሚካኤል ደሴ መጥተው ሳሉ የጣሊያን መንግሥት በግፍ የያዛትን ኤርትራ አያቴ ደጃዝማች ይማም ከሠራዬ ስለሚወለዱበት በመጭው ፲፱፻፱ ዓ.ም. መስከረም ሐማሴንን ለማስለቀቅ ዘመቻ እንዘምታለን ብለው ከወራሴ መንግሥት ከልጃቸው ጋር ውሳኔ ወስነው ስለነበርበዚሁ ትልቁ የዓለም ጦርነት የኛን የቃል ኪዳን ጓደኝነት እምቢ ብለው የተሰወረ የጀርመንን ቄሣር ወዳጅነት አበጅተዋልና “ነገ ጡዋትም ኢትዮጵያ በኛው ላይ በባላጋራነት ጦርነት ያስነሱብናልና በፖለቲካ ባለ ትልቅ ዋጋ ሰው የሚሆኑ ደጃዝማች ተፈሪ በመርዳት ልጅ ኢያሱ የወደቁበት እውነተኛው ምክንያት በመጀመሪያ ጠብ ያነሳሱባቸው ፈረንሣዊዎችና እንግሊዞች ናቸው” ሲል ሔንሪ ደ ምንፍረድ ወደ ጠበኞች የሆኑት የኢትዮጵያ ሀገሮች በሚል መጽሐፍ መሰከረባቸው።” ገጽ 33

“በዚሁም መጸሐፍ በመቅደላ የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት አጼ ቴዎድሮስ እንደ ሞቱ፣ ቱርኮች የሐረርን አውራጃ ለቀው ለመሔድ ውሳኔ እንደወሰኑ፣ እንግሊዞች ወደ ሐረር ገዢ ጦራቸውን ላኩ ሞግዝትነቱን ይቀበለናል ብለው፤ መታያቸውን ተቀብሎ ባንዴራቸውን ባጥር ግቢው ብቻ ተከለና እንግሊዞች የመጡበትን ጉዳይ በመፈጸማችው በብዙ ደስ ብሎዋቸው ከሐረር ግቢም ገና እንደወጡ፣ ከእንግሊዞች የባሰው ተንኮለኛው የሐረር ገዢ ገና በደስታ ወደ ባህር እንደተነሱና የሐረርን በሮች እንደወጡ በሚያንፀባርቅ ጌትነቱ ሕዝቡን በበዓላዊ ጥሪ ሰብስቦ የእንግሊዝን ባንዴራ በትልቁ ገበያ አቃጠለው። የእንግሊዝን ባንዴራ በድፍረት ካቃጠለው በኋላ አንድ ጦር እንግሊዞችን የሚደርስ ላከ። እነሱም ዙሪያቸውን ተከበው ሌት በመታረድ ተገደሉ። ቆይቶም ከጣሊያን መንግሥት ጋር አንድ የወዳጅነት ውል ከተዋዋለ በኋላ በሶማል ሀገር ከገቡ በኮንት ፓሮ የሚመሩት ዶክቶር ሳታርዲና፣ ዶክቶስ ዛኒኒ፣ ፕሮፌሰር ሊካታ፣ ኮንት ካርሎ ኮካስተሊ ከነተከታዎቻቸው በ፲፰፻፸፱ ዓ.ም በኢሳዎች ፈጽመው በመገደል አለቁ። በእነዚህ ሁለት ጊዜ መግደል በቀል ለመበቀል እንግሊዝ በዘይላዕ ቢሰናዳ ንጉሥ ምኒልክ “እኔ ደምህን እመልስልህ አለሁ” ብለው ለወንድማቸው ፲፭ሺህ ጦር አዛዥ አድርገው ቢልኩበት የሐረር ገዥ ግን ፭ሺ ብቻ ሰው ነበረውና ጣሊያን በሰጠው መድፍ ቢተኩስበት ከጨርጨር በሽሽት ደንግጠው ቢመለሱ ንጉሥ ምኒልክ አሩሲ ነበሩና በመላላክና በሰላዎችም ውስጥ ለውስጥ ሰሩበት፤” ገጽ 34

“በወራሴ መንግሥት ለልጅ ኢያሱ ሚካኤልም እንደዚህ ተብሎ ዘፈን ተዘፈነላቸው፤ “ኣባ ጤና ኢያሱ ሰባቱ መሳይ፣ ከደሴ ገስግሶ ግሚራ ገዳይ”። ስለምን ከደሴ ሔደው በግሚራ ዝሆን ስለገደሉና ከዚያም ወደ ሰዩ አቢጋር ዞረው በእንግሊዝ ጦር ላይ ግጭት አንስተው ፬ት መኰንኖችና ወታደሮችም ገድለው፣ ራሳችውም ቆስለው አዲስ አበባ ግቢ አገባለሁ ቢሉ ዘበኞች አናስገባም ብለው ቢሉዋቸው በኃይል ተጋፍተው ገቡ። እኔም ወዲያው ከዶሮሲ ጋር ተጣላሁና “እዚህ እኮ ኣሥመራ አይምሰልህ፤ ሥራህንም አልፈልግም ብዬው ወጣሁ” ፪ኛ ጦቢት አቶ ይዕብዩ ዑቁባዝጊን እግዚአብሔር ከአሥምመራ ዕለቱን አመጣልኝና አንድላይ ተነስተን በአልቡኮ፣ ደብረ ብርሃን አድርገን አዲስ አበባ ገባን።” ገጽ 34

“የላዛሪስት ሚሲዮን አባ ተስፋሥላሴ ወልደ ገሪማ ወደ ካፑቺን ሚሲዮን ለማስገባት ይዘውኝ ሔደን ትምሕርት ቤት አግቡኝ ብዬ ብለምናቸው፣ “ከኤርትራ ለመጣ ልጅ ሁሉ ምንም እንዳናገባ የጣሊያን መንግሥት በጥብቅ ከልክሎናልና ተማሪ ቤት ልናገባህ አንችልም” ስለ መለሱልኝ በብዙ ኅዘን አዘንሁ። የኢትዮጵያ መንግሥትንም አማሁ፤ ኣማደርገውም ጠፋኝ። በዚሁ እድፋም፣ እጅግ አዳፋ በሆነው የኢትዮጵያን ሕዝብ ለያይተው እጅ ለማድረግ በሚደክሙበት የማያቋርጥ ፖለቲካቸው ተደነቅሁ።” ገጽ 34

“. . . እኔም በዚያን መጥፎ ሌት ከቀን የተኩስ ጊዜ አዲስ አበባ መቀመጥ የጠላሁበት ምክንያት የሀገሩን አቀማመጥና የጊዜውም ፖለቲካ መለዋወጡንና የሰውም ልጅ ሥራ ሠርቶ በሰላም ለመኖር አለመቻሉንና አስፈላጊውን መብት አጥቶ ፀጥታም ባለማግኘቱ ምክንያት የልብ እረፍት በማጣቴ ነው።” ገጽ 35

“የዛሬ ንጉሠ ነገሥት ደጃዝማች ተፈሪም ራስ ተብለው ሐረርን ለቀው ከፋ እንዲሾሙ ብሉዋቸው ሐረርን አልለቅም ብለው ፲፭ አሽከሮች ይዘው አዲስ አበባ ባባታቸው ቤት ተቀምጠው ወደ የባለቤታቸው እናት ወደ ወይዘሮ ሲሂን ሚካኤል ቢተወደድ ኃይለ ጊዮርጊስን አግብተው ነበርና እሳቸው ዘንድ ከመመላለሳቸው በቀር ግቢ ዓይዘልቁም ነበር። የልጅ ኢያሱ ጸሐፌ ትእዛዝ አቶ ግዛው ሹምዬ ጩፋ ሰሜናኛው ነበርና የሱን ኮሮጀ ያዥ፣ በ፲፱፻፳፷ ዓ.ም. ለጣሊያን ሆኖ የከዳቸው፣ ተክለ ማርቆስ የተባለ የውራጌ “ያሪባ” ሲላላካቸው ስለነበረ የዚሁን ውለታ ብለው ደጃዝማች ተፈሪ ልጅ ኢያሱ በሰገሌ ማግስት በአንኮበር ዘልቀው ባደረጉት ግጭት አቶ ግዛው ሹሚዬ ሲሞት ተክለማርቆስ ተይዞ በራስ ተፈሪ ዘንድ ዚቀርብ፣ በግዛው ሹምዬ ጊዜ ይረዳቸው ስለነበረ፣ በተሰወረ ርዳታው ምክንያት በ፲ ወር እሥራት ብቻ ፈተው ለቀቁት። ብዙ የደከሙ ያባታቸው አሽከሮች ሳሉ ከእሥራት የተፈታውን የዛሬው ተክለ ማርቆስ አንስተው በግላቸው ጸሐፊ አደረጉት፤ ሰውም አየባቸው፣ አዘነም።” ገጽ 35

“ሰው ቢያዝን ቢያይባቸውም ራስ ተፈሪ ለተክለ ማርቆስ እያከታተሉ ባላምባራስ፣ ቀኛዝማች ብለ የጽሕፈት ሚኒስቴር ዋና ዲረክተርና የፖስታ ሚኒስተርም ቢሾሙት ያለ ድካም የተሾመውን ሱመት ባልታወቀ ምክንያት ጌታውን በክህደት ሸጦ የጣሊያን መንግሥት ሠላይ ሆነ፤ እነፍቅረ ሥላሴ ከተማም፤ ወርቁ አስታጥቄም አስቀድመው በግልጽ ወደ ጣሊያን ዞሩ። ቀኛዝማች ገብረአብና ቀኛዝማች ተሰማ አቡኔ፣ ቀኛዝማች ተክለ ማርቆስ፣ ቀኛዝማች ከልክሌ ወርቁ፣ እነ ብላቴን ጌታ ኅሩይ፣ ሊጋባ ሀብተ ሚካኣኤል አጥብቀው ቢወዱዋቸውም ንጉሠ ነገሥት ጋር ተጣልተው ርዳታቸውና ፍቅራቸው ለጣሊያን ሆኑ ብላቴን ጌታ ኅሩይም ለእንግሊዝ።” ገጽ 36

“ደጃዝማች ተፈሪ መኰንን ራስ ተብለው ወደ ከፋ ይህዱ ቢሉዋቸው አልሔድም ብለው ሲከራከሩ የሸዋ ሰው መስተንግዶ ሲያዘንብላቸው፣ በሐረርም ለስሙ ፊተውራሪ ገብሬ ቢሆኑ ሥራዉን የሚያኬዱት ጨዋ የጨዋ ልጅ ቀኛዝማች እምሩ ኃይለ ሥላሴ አባይነህ የ፲፭ ደጃዝማጮች እንደራሴ( የዛሬው ራስ) ነበሩ። እኔም በዚህ ጊዜ ምክር አዋቂው የኢትዮጵያ ጦር ሚኒስተር ባለ ታሪክ ፊተውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስን ለማየት ምኞት ስለነበረኝ ፫ት ቀን በአጀባቸው መካከል ሆነው በበቅሎ ሲሔዱ አየሁዋቸውና መልካቸውና የፖለቲካቸውም ረቂቅ ሁናቴ ሳመዛዝነው ስለተራራቀብኝ ተገረምሁ። በዛሬም ኢትዮጵያ ባለሥልጣኖች ዘንድ ፊተውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ፣ ደጃዝማች ባልቻ የመንግሥት ጉዳይ አሳቢዎች፣ በእውነተኛው የሀገር ፍቅር ፈረንጅ የማይፈቅዱ ነበሩ።” ገጽ 36

"ደጃዝማች አብርሃ አርአያ ከዚያው ትምሕርታቸውና ወጣቱ ሰውነታችው፣ ወርቅ ከመሰለ ወደረኛ ከሌለው ቅላታቸው ጋር፣ ከኣኒያ እሳቶች የሆኑት የትግሬ አሽከሮቻቸው ሲሔዱ እንደመብረቅ፣ ዓይቻቸው ሳልጠግባቸው ከእውቀትና ከወንድነት ጋር ከፈ ያለ ድፍረትና ንቃትም ያላቸው ሰው ሆነው ታዩኝ። የልጅ ኢያሱ ወገን ነበሩና በሰገሌ ጊዜ ደጃዝማች አብርሃ አርአያና ደጃዝማች አመዴ ወሌ ብጡል ሁለቱ ትግሮች ባንድግዜ ሞቱ ማለትን ሰማን፤ በዚሁም ጊዜ አዲስ አበባ በጭቃ የተሞላች “ፊንፍኔ” የተባለች ዱርና ገደል ነበረች። ይህም ከተማ አጼ ምኒልክ በሌሉበት ከኣንጦጦ ፍልወኃ ለመታጠብ ወርደው ኮረብታይቱን ለከተማነት የመረጡዋት፣ የቆረቆሩዋት የሸዋን ቤተ መንግሥት በችሎታዊው ድፍረትና እውቀታቸው ብዛት ያቋቋሙት እቴጌ ጣይቱ ብጡል ናቸው። የሸዋ ንጉሥ ምኒልክ ግን ውራጌዎችንንና ኦሮሞዎችን ስለፈሩ ቆጥ በመሰለው የኣንቶቶ ገደል ሠፈሩ፤ ወድትዋ የሴቶች መመክያ እቴጌ ጣይቱ ግን በትግሮችና በሰሜነኞች አሽከሮቻቸውና በእውቀታቸው ብዛት ዘው አስጭነው ኢትዮጵያን አስገዙዋቸው።" ገጽ 36

"የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ጃንሆይ አጼ ዮሐንስ በምጽዋዕ ያለ ማቋረጥ ከቱርክ በጎዳጉድና በጕራዕ፣ ከጣሊያን በሰሐቲ እየተዋጕ ለንጉሥ ምኒልክ ሐረርና አሩሲ፣ ጂማና ከፋ፣ ለቀምት እንትይዝ ብለው ፫ ጊዘ የቁጣ ቃል ጻፉላቸው፤ ያልሰማና ያላየ ሰውም ምኒልክ አሥፋፋት ብሎ ያላል። ይህኑኑም ሀገር ሁሉ በጀግንነት ያቀኑት ደጃዝማች ጐበና ናቸው፤ እሳቸው በያዙት ሀገር ሱኡን ራስ ተባለበት። ጀግናው ደጃዝማች ጐበና ግን ጉዳታቸው ለአጼ ዮሐንስ እንኳ አቤቱታ ሳይልኩ የራስ ማዕረግ አልተሰጣቸው፤ ስለምን የጀግና ጠላቶች ቁጥር የላቸውም እና ከሽሽታዎቹ (ከሸሽዎቹ ከፈሪዎቹ) በኋላ በመቀበላችወ አስደነቀ። አጼ ዮሐንስ ለሸዋ ንጉሥ ምኒልክ ጣሊያኖች ፈጽመው ከሸዋ መሬት ለቀው በግዴታ እንዲወጡ፣ አንተም ገረርና አሩሲን ጂማና ከፋ ለቀምትና ምዕራብ ሀገሮች ሁሉ በፍጥነት እንድትይዛቸው ይሁን እያሉ ፫ት ጊዜ መጻፋቸው ለማንም ሰው የተሰወረ አለመሆኑን አስገነዝባለሁ። እውነተኛው ጽሑፍና ሐሰተኛው የኣፍ ታሪክ ለየራሱ ስለሆነ፣ እውነትን ወደ ሐሰት ለመለወጥ ስለማይቻል በከንቱ ለደከሙና ለሚደክሙ ሰዎች አዝንላቸው አለሁ እንጂ አላዝንባቸውም።" ገጽ 37

ባለታሪኩ “ከአዲስ አበባ በጂቡቲና በአደን መንገድ መቃድሾ ስለሜሔዳቸው” ትረካቸውን ይቀጥሉልናል!

Re: ተስፋሚካኤል ትኩእ (1892 – 1964)] - ወለዶና ክነቦ ዝግባእ መኽዘን ታሪኽ

Posted: 10 Jun 2019, 05:32
by Meleket
እኒህ ድንቅ አባት በዛሬው ትረካቸው ስለ ልጅ ኢያሱ፣ ጂቡቲን በተመለከተ ስለነበራቸው አቋም፣ ከጀርመኖች ጋር ስለነበራቸው መቀራረብ እንዲሁም ስለ ፫ቱ መንግስታት አካሄድ ተንትነውልን በጂቡቲ አድርገው ሞቃዲሾ ደርሰው አስመራ ተመልሰዋል። :mrgreen:

“በአዲስ አበባ ትምሕርት ቤት ገብቼ ለመኖር ተስፋ ከቆረጥሁ በኋላ ከወዳጄ ከመልካሙ ከአቶ የዕብዮ ዑቁባዝጊ ጋር ተሳስመን በቅሎ ተከራይቼ ከአዲስ አበባ አቃቂ ደረስሁ። በነሐሴ ፲፭ ቀን ፲፱፻፱ ዓ.ም. በፈረንሣዊ ምኞትና ብርታት ከጂቡቲ አቃቂ በደረሰው ምድር ባቡር ተሣፍረን ከትግሬው ቀኛዝማች ካሣና ከቀኛዝማች ተአፍራ በለው፣ ከሞስኮናዊው ፊተውራሪ ባብሽፋ ጋር ባንደኛው ክፍል ሆነን ማታ ሐዋሽ፣ በ፪ኛ ቀን ድረደዋ ገባን።” ገጽ 38

እኔም ጅቡቲ እንደደረስሁ የኢትዮጵያ መራሔ መንግሥት ልጅ ኢያሱ በጂቡቲ ሀገረ ገዢ አዳራሽ ፎቅ ወጥተው ለሶማሌ ሕዝብ አሰባስበው ፲ሺህ ብር አፈሰሱለትና ሽሚያ ተሻማው፤ እጅግም በቡ ደስ አለው፤ ሀገረ ገዢው አዳራሽ በመግባቱም አደነቀ። ልጅ ኢያሱም ለፈረንሣይ መንግሥት እንደራሴም ሀገሬን ለቀህ እንድትሔድ ቢሉት አባትዎ አጼ ምኒልክ ሰጥተውኛልና እንዴት እለቃለሁ ቢላቸው፤ ያባቴ ስጦታ አይረጋምና ያለ አንዳች ክርክር ሀገሬ ጅቡቲን ለቀህ እንድትሔድ ብለው አስገደዱትና ፈረንሣይ ተጨነቀ፤ ከፋውም። ስለዚህ፣ የሚስማማውን ሰው በኢትዮጵያ ለማንገሥ በብዙ ደከመ።” ገጽ 38

መራሔ መንግሥት ልጅ ኢያሱ ሚካኤልም በኢትዮጵያ ዙሪያ ካሉት የእስላም ሕዝቦች ጋር ፍቅርና የወዳጅነት ስምምነት ካደረግሁ ኤውሮጶችን ባንድ ቀን ከሞላው አፍሪካ ለማስወጣት እችላለሁ ብለው፣ ለማንም ሰው ያላማከሩት ፖለቲካ ለብቻቸው መሥርተው ከእስላም ባላባቶችና መኰንኖች ጋር የግል ወዳጅነት አበጅተው ነበር እንጂ አልሰለሙም። በዚህ ጊዜ አውሮጳ ከጀርመን ጋር ባደረገቹ ትልቅ የዓለም ጦርነት እንኳንስ በአፍሪካ ይቅርና በሀገራቸው የአመሪካ ጦር ርዳታ ባይደርስላችው ኑሮ እጃቸውን ለጀርመን ማስረከባቸው የማይጠረጠር ስለሆነ፣ አስቀድመን ልጅ ኢያሱን ካላጠፋን በቀር ኢትዮጵያን አስነስተው ይደመሱስናል በሚል ፍራት ልጅ ኢያሱ ሰልመዋል ብለው ፈረንሣይና እንግሊዝ፣ ጣሊያን መንግሥታት የኣኢትዮጵያን ሕዝብ በማሳመን ቀስቅሰው ያስወጡዋቸው በትክክል ፫ቱ ናቸው።” ገጽ 38

“ በዚህ ጊዜ እነዚህ ፫ቱ ጓደኞች የሆኑት፣ መንግሥታቶች ለራሳቸው ፖለቲካ ጥቅም ብለው አንዳንድ ሚሊዮን ብር በድምሩ ፫ ሚሊዮን ብር አዋጥተው ለኢትዮጵያ ሕዝብ ፕሮፓጋንዳ ስብከት ብለው ገንዘቡን አፈሰሱት፤ “ልጅ ኢያሱ አስልመዋል፤ የእስላምም ሴቶች አግብተዋል፤ መንግሥት ዓይገባቸውምና አወግጂአለሁ ብለው የእንግሊዝ ዜጋ የሆኑት አቡነ ማቴዎስ በሐሰት ስብከት ሰበኩ፤ የዋሁ የኢትዮጵያ ሊቃውንትና መኳንንት፣ ሕዝብና ወታደርም ከልብ አመነ፤ እየተከታተለም ተሳደበ። ነገሩ ምን እንደሆነ ሳያጣራ ጠላቶች ባወሩት ወሬ መንገድ ተከታትሎና አምኖም እስከዚህ በመሥራቱ ሕዝቡ አልተመሰገነበትም፤ ስለምን አቡን ቢያወግዙ በአቡን ቃል ብቻ ከማመን የጠላቶቹም ረዳት ከመሆን ይልቅ ራሱ መረዳትና ማስረዳት፣ መፍረድም ነበረበት።” ገጽ 39

“ልጅ ኢያሱም ከዚህ ቀደም ብለው ወደ ጀርመን ሀገር ለወንድማቸው ልጅ ለደጃዝማች በላይ ኣሊ ልከው በጂቡቲ ተጥለው የነበሩት መድፎች አስመጥተው፣ ራሳቸውም ጀርመን ሀገር ሔደው የልባችውን ለመነጋገር ኅሳብ አስበው ልጅ ኢያሱ በሥውር ቢነሱ፤ በጂቡቲ የነበሩ የኢትዮጵያ ቆንሱል አዋቂው አቶ ዮሴፍ የሚባሉ ዓይሔዱም ብለው ኣምቢ ቢሉኝ እርስዎን ገድዬ በራሴ ሽጉጥ እራሴን እገድላለሁ፤ የኢትዮጵያ መሬ ሆነው፣ ዘውድ ተሸክመው ወደሰው ሀገር ምንም አይሄዱም ብለው ከለከሉዋቸውና ልጅ ኢያሱም ዝም ብለው ከጂቡቲ ወደ ሐረር ከየባላባቱ ጋር ኣያደሩና በወዳጅነትም ሰፊውን ፍቅር ማሳየታቸውንና እስላሞችን ማቅረብ ሐሰት አልነበረም፤ መስለማቸው ነው እንጂ ሐሰት የተባለው።” ገጽ 39

“ልዑል ልጅ ኢያሱም ሐረር እንደወጡ ወዲያውን ቀኛዝማች እምሩ ኃይለ ሥላሴን አሥረው ባረፉበት ፎቅ ቢያስቀምጡዋቸው ከነ ቁራኛቸው በመሰላል ወርደው መጋላ አቶ ሙጨ ቤት ተቀምጠው ተላላኩ፤ ፕላናቸውንም አበጁ። ገጽ 39

“ልጅ ኢያሱም የሐረር መኳንንት ወደ ራሳቸው በማባበል ብዙዉን አዞሩት፤ ወደ መዔሶም አሽከሮቻቸው ደጃዝማች ጉግሣ አሊዩና ፊተውራሪ ከበደ ያዘ፣ ግራዝማች ንጋቱ አመዴን አድርገው ላኩ፤ . . . ልጅ ኢያሱም የመዔሶን ድል ሳይሰሙ ለመከላከል ድሬዳዋ ወርደው ግምጃቤቱን ከፍተው ብሩን ለማንም ሰጡት። አንድ ጀርመንም ከዚያን በፊት ለድሬዳዋ እንደ አሠልጣኝነት አስቀምጠዉት ነበር።” ገጽ 40

“ቀኛዝማች እምሩ ኃይለ ሥላሴ አባይነህ ልዑል ልጅ ኢያሱ ከሐረር ባንድ ሽንቁር ሲወጡ በቀር ባሩድ ቤቱን ከፍተው ለየ ወታደርና ለሕዝቡ እየሰጡ ፭ቱ የሐረር በሮች ዘግተው የልጅ ኢያሱ ወገን የሆንኑት ሁሉ ክርስቲያንና እስላም ሳይለዩ ወግተው ያዙት። ከአዲስ አበባም በየቀኑ ቁጥር የሌላቸው ልዑል ልጅ ኢያሱን የሚያወግዙ የአቡነ ማቴዎስ፣ የቶር ሚኒስተር የፊታውራሪ ኃብተ ጊዮርጊስ ማህተሞች ደረሱ፤ የሐረር ሕዝብም ያረጋጋው ሀገረ ገዥ ተብለው የተላኩትን ደጃዝማች ባልቻ እንዲመለሱ በመታዘዛቸውና ከፋሌ አምጥተው ወይዘሮ ዘውዲቱ ነገሡ፤ ደጃዝማች ተፈሪ መኰንንም ራስ ተብለዋልና በፍጥነት ወደ አዲስ አበባ እንዲመለሱ ሐዲሱ መንግሥት አጥብቆ አዘዎታል ሲሉ አዋቂው ቀኛዝማች እምሩ ኃይለ ሥላሴ አጥብቀው ሲጽፉላቸው ሐረር ለመግባት ተቃርበው የነበሩት ደጃዝማች ባልቻ ተመለሱ፤ መሬቱም ረጋ።” ገጽ 40

"እኔም ከጂቡቲ አደን ተሻገርሁና ወደ መቃድሾ የሚሔደውን መርከብ ስጠባበቅ ከበረንዳ በመተኛቴ ግሃነብ እሳታዊ የሆነውን የአደን ሙቀት ስለተጋለጽሁ በብዙ ታመምሁ። ብታመምም ከመርከቡ ለመቅረት አልቻልሁም ኣና እንደ ደረሰ ተሳፍሬ መቃድሾ ገባሁ፤ ከዚያም ጊዘ ለጓደኞቼ ከፍ ያለ ደመወዝና መልካም ባለ ክብር አስተዳደርም ነበራቸውና ለኔም ተሰጠኝ። በ፲፱፻፳፰ ዓ.ም. የተነሳውም ጦርነት ገና በኢዝያን ጊዜ ዕለቱን የሚያነሱ ይመስሉ ነበር ኢጣሊያኖች። ስለምን፤ ልጅ ኢያሱ ከአልጋ በመውረዳቸው ምክንያት በብዙ ተደሰቱ፤ ምንም እንኳ በጀግናው የጀርመን ሕዝብ ሀገራቸው ጦርነት ድል እንሆናለን ብለው ቢሰጕ፤ ቢንቀጠቀጡም።" ገጽ 40

እኔም በመቃድሾ ከተማና በራስ ሉል ሰገድ ምሽግ በልዓድ ከተባለው ከመቃድሾ ፴፫ ኪሎ ሜትር የሚሆን ቦታ በታች በሆነው አውደዓላ በተባለው የወይብ ሸበል የሚያጠጣው ፈሳሽ ወኃ በመጠጣቴንና ትንኝም ስለበላኝ ንዳድ ያዘኝና በብዙ ታመምሁ። በየጊዜው አባቴ ወደ ኤርትራ እንድመለስ ያለማቋረጥ ስለሚጽፉልኝ አባቴን ደስ ለማሰኘት ብዬ አሠመራ ለመመለስ የተገደድሁ ሆንኩና የመቃድሾ ሀገረ ገዥው እንደራሴ ያዕቆብ ጋስፓሪኒ አወደዓሌ መጥቶ ስንብት ብጠቀው "ዛሬ የጦርነት ጊዜ ስለሆነ ስንብት አይሰጥህም" ሲል አለኝእኔም ጦርነት ቢሆን ባይሆን ወታደር አይደለሁምና እናንተ ባታሳፍሩኝም በራሴ ገንዘብ ከፍዬ ያባቴን ፈቃድ የሚከለክለኝ የለም አልሁና ከፋው። ይህም ክርክር ስንከራከር ለጋስፓሪኒ ወዳጅ ያልሆነ በአወደዓለ ረሲደንቴ ለኮንተ ካተሪኒ አስጠናሁና በጥቅምት ወር ተነስቼ አሥመራ ገብቼ በህዳር ፮ ቀን ፲፱፻፲ ዓ.ም. በተክሊል ስላገባሁ ያባቴን ፈቃድ ፈጸምሁ።” ገጽ 41

በቀጣዩ ክፍል ባለታሪኩ በኤርትራ ሥራ ስለመያዛቸው፣ “የተሰወረ የኢትዮጵያ መንግሥት ቆንሱል” ተብለው ቁም ስለመታሠራቸው እያዋዙና የጊዚያቸውን ሁኔታ እየተነተኑ ያወጉናል። :mrgreen:

Re: ተስፋሚካኤል ትኩእ (1892 – 1964)] - ወለዶና ክነቦ ዝግባእ መኽዘን ታሪኽ

Posted: 11 Jun 2019, 03:32
by Meleket
እኒህ ቆፍጣና አርበኛ፡ ኤርትራ ተመልሰው በዳሎል የፖታሽ ሥራቸው ያጋጠማቸውን ሁኔታ፡ የዓዲ አቡኑ ሰላይ የተስፋሁነኝ ሸፍጥ፣ በወቅቱ ከፖታስ ይገኝ የነበረውን ትርፍ በኣኃዝ አስደግፈው ይተነትናሉ፣ አያይዘውም በኢትዮጵያ መንግሥት ስም ያለልክ እጅግ ከፍ ባለው ዋጋ ከፈረንሣይ ሀገር አጭር ውጅግራ ጠበንጃ የገዙ ደጃዝማች ጌታቸው አባተ በምጽዋዕ ስላጋጠማችወ ጉዳይ ተንትነው ጨው እንዴት እንደሚመረትም ሂደቱን ገልጸው የፋብሪካውንም ዲዛይን ማን እንደነደፈው ሳይቀር ዘርዝረው ይገልጹልናል። ከገለጡ አይቀር እንዲ አርጎ እውነቱን ቁልጭ አድርጎ መግለጥ ነው እንጂ! በርግጥ እንዲህ አድርገው እውነታን የሚገልጹ ኤርትራውያን አባቶች እና ቅድመ አያቶች መኖራቸው ያኮራናል! :lol: ይህን ጽሑፍና ትንታኔ እጅግ ብርቅ የሚያደርገው ዋነኛ ምክንያት፣ አሁን ያለው ትውልድ ገሚሱ ገና ሳይወለድ፣ ገሚሱም ገና ባንቀልባ ላይ ታዝሎ እያለ የነበረን ሁኔታን ፍንትው አድርጎ መግለጡ ነው!!! መልካም ንባብ። :mrgreen:

ባባቴ ቤት በሀገሬ በሠገነይቲ አንድ ወር ስቀመጥ ከዘመዶቼ ብዙ ስልቻ ማር ስጦታ መጣልኝ፤ በዚያም ፲፱፻፲ ዓ.ም. ወሰን የሌለው ማር ከየ ጫካውና ከየ ቤቱም ሲቆረጥ በብዙ አስደነቀ፤ ዘመኑም የቅቤ ፣ የእህል፣ የማር ዘበን ተባለ። ስለዚሁ መልካም ዘበን ሰው ሁሉ በፍቅር ተሳስሮ ተስማማ፤ መሬቲቱም ፍሬዋን ሰጠች፤ እኔም ያለ ኅሳብና ያለወጭ ገንዘብ ባባቴ ቤት ቶይቼ አሥመራ የገባሁኝ ቀን የተማሪ ቤት ጓደኛዬ አቶ ወልደማርያም ተወልደን አገኘሁና በብዙ ደስታ ተቀብሎ ጋበዘኝ። በዚሁም ግብጃ መካከል “እኔ መርሳ ፋጢማ ኤረሰለ የደሎል ፖታሳ ሥራ እሔዳለሁና መቃድሾ ከመመለስ ይልቅ በዋናው መሥሪያ ቤታችን የኔው የጸሐፊነቱ ቦታ አለና ነገ ጡዋትና” አለኝ። እኔም አባቴ መቃድሾ መመለሴን ስላልፈቀዱ ደስ ለማሰኘታቸው ብዬ ኅሳቡን ተቀበልሁት።” ገጽ 42

በማግሥቱም የፖታሳ(ማዕድን) ኩባንያ ዲረክሲዩ ወደ ኮመንዳቶረ ጆቫኒ ደል ኮርሶ ፊት በቅጽበት አቶ ወልደማርያም አቀረበኝ፤ ወዲያውም ጆቫኒ ደል ኮርሶ በመኪና ጽሕፈት ፈተና አደረገልኝና ስለወጣሁ ዕለቱን በ፻ ሊሬ የወር ደመወዝ ቆርጦ ስለተቀበለኝ። እኔም በመቃድሾ እማገኘው ደመወዝ ብልጫው ትንሽ ስለሆነ በሀገሬ መቅረቴን ፈቀድሁና በአሥመራ ቀረሁ። አቶ ወልደማርያም ሥራዉን አስረካክቦኝ ሔደና ከኮመንዳቶረ ጆቫኒ ደል ኮርሶ ጋር በደስታና ስምምነት ሥሠራ ሳለሁ፤ አንድ በኩራት የተሞላ፣ ክርስትያኖቹን የጠላ፣ በየሰዓቱ ልብሱን የሚለውጥ ጋንተስ የተባለ ግምጃ ቤት በክፉ ዓይን ተመለከተኝ፤ እኔም እኔን የሚጠላበትን ምክንያት ስላላወቅሁት በብዙ ደነቀኝ። ይህም ያለ ልክ በኩራት የተሞላው ከንቱ የሆነው ዮሴፍ ጋንተስ የግምጃ ቤቱን ሒሳብ አማትቶ ፴፭ሺህ ሊሬ አጥፍቶ በስንብት ወደ ጣሊያን ሀገር ተነስቶ ሔደ። ደል ኮርሶም ገቢን ወጭውን፣ በባንክ ያለውንም ገንዘብ ሲያመዛዝን ሳለ ፴፭ሺህ ሊሬ ጉድለት ስለተገኘበት አታላው ጋንተስ ናፓሊ እንደደረሰ ታሥሮ አሥመራ እንዲመለስ አስቀድሞ በቴሌግራም አስታውቆ አሥመጣው።” ገጽ 43

“የሠገነይቲ አቶ ወልደ ማርያም ተወልደ ጤና ስላጣ ወደ የኔው ሥራ አሥመራ ሲመጣ እኔም በሱ ሥራ የ፻፶፭ ሊሬ ደመወዝ ወደ እሳታዊው ፋጢማ ኤረ ተዛውሬ እንድሠራ ከደል ኮርሶ ታዝዤ ሔድሁ። ገና በዚህ ሀገር ስገባ የዓጋሜው ወጣት ፊታውራሪ ለበን ስብሐት መጡና ሰንብተው ሲሔዱ ፊታውራሪ ተድላ የሚባሉትም ሹም ከዓጋሜ በአሥመራ መንገድ መጡ። እንደመጡም ፈልገው ተገናኙኝና ስለ ፓታሳም ፈጥነው ጠየቁኝ፤ እኔም አላውቅም ስል መለስኩላቸው። በማግሥቱ እሁድ ቀን ነበርና ለማየታቸው ባረፉበት ቦታ ስሔድ ፊታውራሪ ተድላ በደስታ ፈጥነው ተቀበሉኝና ወዲያው ቁጭ ብለን ስንነጋገር “ባክዎ ይህንን የደሎል ማዕድን ወዴት ነው የሚወስዱት? ምንስ ጥቅም ያገኙበታል? ይንገሩኝ” ብለው አጥብቀው ጠየቁኝ። እኔም ጥያቄአቸው ደስ ስላለኝ “ከፍ ያለ ብዙ ጥቅም ባያገኙበት በከንቱ የሀገራችንን አፈር እየቆፈሩ የባቡር መንገድ እስከ ባህር ዘርግተው ባላጓዙት ነበር። የኢትዮጵያ መንግሥት እውቀት ቢኖረው ከባለ ብዙ ጥበብ እንደ ጀርመን መንግሥት ከመሰለው ጋር ውል ተዋውሎ ቢያሠራው ኑሮ ብዙ ጥቅም ባገኘበት ነበር”። ገጽ 43

“የዚሁም ኢትዮጵያው ደሎል አንድ ኩንታል አፈር፣ በአደን ፮፻ በኤውሮጳ ሺህ ፸ በአመሪካ ፪ ሺህ ሊሬ ይሸጣል፤ ባሩድ ይሠሩበታል፤ መድኃኒት ይቀምሙበታል፤ ጥቅማቸውም ወሰን የለውም ብዬ” ስላቸው ተከትሎዋቸው ከመጡት ከ፰ቱ ልብስ ከሌላቸው አሽከሮቻቸው ውስጥ የዓዲ አቡን ተስፋሁነኝ ከዚህ በላይ የተጻፈውን ቃል በቅጽበት ለቢያንኪ ነገረውና ፷ ብር ዋጋ ተቀበለብኝ። ለዚሁ ሥራ ዋና ሹም የሆነው ቢያንኪም “ተስፋሚካኤል ትኩእ የተባለው ጸሐፊ የተሰወረ የኢትዮጵያ መንግሥት ቈንስል ሆኖ ሲሠራ ስለተገኘ በፖሊስ ጥበቃ ወደ አሥመራ ልከነዋልና በቀጥታ ወደ አሰብ እሥር ቤት ተልኮ እንዲታሰር” ብሎ ለኮመንዳቶረ ጆቫኒ ደልኮርሶ በቀጥታ ጻፈለት። ለኔ” ወደ አሥመራ እንድትወጣ” አለኝ። “አልወጣም የደል ኮርሶ ትእዛዝ ካልደረሰኝ” ብዬ ፫ት ቀን በቤቴ ተቀምጨ ሳወጣ ሳወርድ ሰነብትሁና ወደ የኢትዮጵያዉን አፍቃሪ የሆነው የመድፈኞች ሻምበል የጨዋ ልጅ አምፕሪሮሪ በአሥመራ መሥያ ቤት ስለማውቀው እሱ ዘንድ ኼጄ “የላከኝ ደል ኮርሶ ነው፤ ያለ የደል ኮርሶ ትእዛዝም ቢያንኩ ወደ አሥመራ እንድትወጣ ብሎ አለኝ፤ እኔም የላከኝ ኮመንዳቶረ ደል ኮርሶ ስለሆነ ያለ የሱ ፌርማ አልሔድም አልሁት፤ ነገሩስ ምን ይመስልሃል” አልሁት። እምፐራቶሪም በብያንክ መጥፎ የስለላ መሠለልን ሥራ አዘነ፤ ነገሩንም ስለፈራ “ዝም ብለህ መሔድ ይሻላል” እያለ ካጽናናኝ በኋላ ለአሽከሩ፣ ቢያንኪ ተንኮል እንደሠራብኝ ነግሮት ኑሮ ተከተለኝ እና ዳርዳሩን ነገረኝ። እኔም ከመርሶ ፋቲማ ኤረ ወደ ዓጋሜ ለመውጣት አሰብሁ፤ ዳሩ ግን ዓጋሜ ሳልደርስ በወኃ ጥም ብሞት ወይም በመንገድ በማላውቀው ሀገር ሞያ ሳልሠራ በከንቱ ብያዝ፣ ለአባቴና ለዘመዶቼ ከማስወረሴ በላይ ማሳዘኔን አሰብሁና ወደ አሥመራ ወጥቼ የሚመጣብኝን አሥራትና መከራ መቀበል ይቻላል ብዬ ወደ ሠፈሬ ተመለስሁና ሻንጣየን አሸክሜ ወደ ጀልባይቱ ገባሁ።” ገጽ 43

" በዚህ ጊዜ እኔን የሚጠብቁ ሁለት ፖሊሶች በፍጥነት መጡና በቀኝና በግራ ሆነው ተሣፈሩ። . . . ምጽዋዕም እንደ ደረስን አንደኛው ቀረና ሁለተኛው ከኔ ጋር ከምፅዋዕ አሥመራ ድረስ ወጣ። እኔም በቀጥታ ወደ መሥሪያ ቤት ወደ ደጕ ኮመንዳቶሪ ጆቫኒ ደል ኮርሶ ዘንድ ኸጄ “አንተ ለሥራ ላከኝ፤ ግፈኛው ቢያንኪ ግን በፈቃዱ መለሰኝ፤ ምክንያቱስ ምንድር ነው” ብለው፣ እኔ ላኩህ እኔም አሥጠራሁህ፤ የሚያናግርህ ጉዳይ የለምና ፭ት ቀን አርፈህ ና” አለኝና ቢያንኪንና ለ፷ ብር የሸጠኝን ተስፋ ሁነኝን በፍጥነት በሥልክ ተጠሩና አሥመራ መጡ።" ገጽ 44

"ደል ኮርሶም በቁጣ ቃል ለቢያንኪና ለተስፋ ሁነኝ “አንተ አለ አገባብ የሰጠሀው ፷ ብር፣ አንተም በሐሰት የተቀበልካትን ለ፷ ብር መልሱ” ብሎ አስጨንቆ ሁለቱንም ያዛቸው። “የተሰወረ የኢትዮጵያ መንግሥት ቈንስል ሆኖ ተስፋሚካኤል ትኩእ ፖለቲካ ሲሠራ ስላገኘው ለተስፋሁነኝ የሰጠሁትን ፷ ብር ስለምን እከፍላለሁ? ተስፋሚካኤል ትኩእስ ይህን ያህል ከፍ ያለው ጉዳት በጣሊያን መንግሥት ላይ የሠራውን ሣይታሠር እንዴት ይቀራል” ብሎ መለሰ። “ተስፋሚካኤል ትኩእ ለክቡር ራስ ሥዩም መንገሻ ዮሐንስ ለልጃቸው ለደጃዝማች ካሣ ስዩም፣ ለደጃዝማች ተካም ጋር ደብዳቤዎች ስንጻጻፍ ሳስተረጕመው ተስፋሚካኤል ትኩእ ምንጊዜም ምስጢር ውጭ አውጥቶብኝ አያውቅም ነበር። እኔ መርጨ ያመጣኹትን ሥራተኛ አለማመንህ እሱን አይደለም እኔን ነው፤ ተስፋሚካኤልም አንተ እንደምትለው ክስ ዓይነት ዓይሠራም ቢሠራም እኛን የሚያገባን ጉዳይ ዓይደለም። ይህም ወጣት ልጅ በዚሁ ፖለቲካ አሰብ እሥር ቤት ቢታሠር እኛ ምን እንጠቀምበታል፤ አንተም በማያገባህ ሥራ አትግባ! የፖለቲካ ሠራተኛ ዓይደለህምና ተጠንቀቅ” ብሎ ደልኮርሶ በቁጣ በቢያንኪ ላይ በይፋ ተቆጣውና ተንቀጠቀጠ፤ በፍራትም ያለልክ ተሸበረ።" ገጽ 45

"ኮመንዳቶሪ ጆቫኒ ሰል ኮርሶም “ተስፋሁነኝ የሚባል ዘበኛ እኛንና እናንተን የሚያጣላን መጥፎ ሰው ስለሆነ ከደሎል ሥራ እንዲወገድ፣ ወደ ኤርትራም ኣንዳይመለስ እንድታደርጉልን አጥብቀን ለክቡርነትዎ እንለምናለን” የሚል ደብዳቤ ለክቡር ራስ ሥዩምና ለደጃዝማች ካሣ ጻፈና እጁንም በኤርትራ መንግሥት በኩል ወደ ዓድዋ ተልኮ በደጃዝማች ካሣ ዘንድ ውርደትና አለንጋም ተቀበለ። ተስፋሁነኝ ፷ብር እበላለሁ ሲል ተበላ፤ ተዋረደ። እግዚአብሔር ግን በሰፊ ቅን ትክክለኛው ፍርዱ ከቢያንኪና ተስፋሁነኝ ሰብቅና እሥራት ሰውሮ ስላተረፈኝ አመሰገንሁት፤ አመሰግነዋለሁም።" ገጽ 46

"ለኢትዮጵያ ሕዝብ እማኝና ጠበቃም የሆነው መልካሙ ደል ኮርሶ ይህን ጭቅጭቅ ከፈጸመ በኋላ እኔን ጠራኝ እና “የምጽዋዕ የጨው መስሪያ ቤት አለቃው እኔ ስለሆንኩ ለዛሬ በ፻፷ ሊሬ ለወደፊቱም ደመወዝ እንዲጨመርለት፣ ቤትም እንዲሠጠው” ብሎ ጽፎ ላከኝ፤ በጥር ወር ፲፱፻፲፱ ዓ.ም. በጸሐፊነት ፪፻ ሊሬ ደመወዝ ስሠራ ሳለሁ፣ በየቀኑ የሚመጡትን የእንግሊዝ መርከቦች የሚጭኑትን ጨው ዋጋ በወርቅ ለውጥ ብዙ ሚሊዮን የወር ገቢ ነበራቸው፤ የጨው ሀብትና ሥራም የምጽዋዕን የመሰለ የተከናወነ ሥራ በዓለም ዓይገኝም። የምጽዋዕ ጨውና ዓሳም ጣፋጭነቱና ማማሩም ልዩ በመሆኑ በብዙ ተመስግነዋል። ገጽ 46

በኢትዮጵያ መንግሥት ስም ያለልክ እጅግ ከፍ ባለው ዋጋ ከፈረንሣይ ሀገር አጭር ውጅግራ ጠበንጃ የገዙ ደጃዝማች ጌታቸው አባተ ከነጓደኞቻቸው ምጽዋዕ ወረዱና በታሪኩ የታወቀውን የግራርን ጨው አመጣጥና ካንድ ሽህ የበለጠውን ሠራተኛ ሲሠራ፣ ጨው ትልቅ ወሰን የሌለው ክምር ሲከመር፣ ከተከመረበትም በምድር ባቡር ተሞልቶ ወደ ባህር ዳር ባለው መጋዜን ውስጥ ገብቶ ሲያፈሰው፣ ከዚያም ጥበባዊው የእውቀት ሥራ ሽቅብ አውጥቶ ወደ ወፍጮ ራሱ እየወረወረ ፈጭቶ መልሶም ወደሌላው መጋዜን ያገባዋል፣ ከዚሁም መጋዜን አንስቶም ወደ ባህር ውስጥ ያሉትን መርከቦች በፍጥነት ሲሞላ በማየታቸው፤ የኢትዮጵያ መላክተኞች ይቅርና ሞላው የዓለም ሕዝብ አደነቀው፤ አመሰገነውም።" ገጽ 46

“በዚሁ ጊዜ የመንግሥት የምጽዋዕ ጕምሩክ ሹሞች የሆኑት በትምህርታቸውና በእውቀታቸው ከፍ ያሉት ግራዝማች ተድላ ጋብርና ፊተውራሪ ዘወልደማርያም ዘገርጊስ፣ ብላት ዘርኤ ግርሙ ዘጠና ሊሬ ደመወዝ ለየ አንዳንዳቸው ሲሠሩ እኔ “፪፻፶ ሊሬ ካልተሠጠኝ በ፪፻ ሊሬ ደመወዝ ምንም አልሠራም” ብየ በ፮ ወር ወደ አሥመራ እምቢ ብዬ ሥወጣ በማየታቸው በብዙ ተደነቁ። “የተስፋሚካኤል ትኩእ ዕድል ድንጋይ የሚፈልጥ ዕድል ነው” ሲሉ መሰከሩ።" ገጽ 46

"ይህንኑ የምጽዋዕን ጥበባዊ የጨው ፋብሪካ ሥራ የሠራ ዓይምነ የሚባል አዋቂ መሐንዲስ ብዙ ምስጋና ከኤርትራዊያን ይገባዋል።" ገጽ 46

አርበኛው ከምፅዋዕ አሥመራ ተቀይረው ስራ እንደጀመሩ፣ ኤርትራ ዉስጥም ድርቅ እንደገባ፣ እሳቸውም ከአስመራ ሞቃዲሾ በጂቡቲ በኩል እንደተመለሱ፣ ጂቡቲ ላይም ልጅ በየነ ህብትዝጊን እንዳገኙ፣ ኃይለሥላሴም ልጅ በየነን በአ/አ ስራ ሊቀጥሯቸው እንዳሰቡ፣ ልጅ በየነ ግን ወደ ሮማ መመለስና ቀጥሎም የትሪፓሊ የእርሻ ዋና ዲራክተ ሆኖ ከእንደነበር ይገልጻሉ። መብራህቱ (ሎሬንሶ) ታእዛዝም በአደን ሥራ እንደጀመረና የኢትዮጵያን አልጋወራሽ በብዙ ዓይነት ፓለቲካ እንደረዳቸው፣ በኤደን እንዳገኛቸው፣ አ/አ መጥቶ ሥራ እንዲዝ ቢጠይቁት ፈረንሣይ ሄዶ መማር እንደሚሻ እንደገለጠላቸው፣ እሳቸውም እንደፈቀዱት፣ እሱም ፓሪስ ሂዶ በየዓመቱ አንደኛ እየሆነ በሕግ ሊቅነት ምስክር እንደተቀበለ ይገልጻሉ

መቃድሾ ከተመለሱ በኋላ ያጋጠማቸውን ሁሉ በሶማልያ የነበሩ ኤርትራዉያን ለኢትዮጵያ መንግሥት በመስራታቸው ያጋጠማቸውን እንግልትና ሞትም ስም እየጠቀሱ እንዲሁም ስለ ልጅ ኢያሱ በቀጥዩ ክፍል ይዘከዝኩልናል! ይህ ሁሉ ደግሞ ያሁኑ ትውልድ ማለትም አዳሜ ገና ሳይወለድ በአንቀልባም እንኳ ገና ሳይታዘል የተፈጸመ ነው!!! :mrgreen:

Re: ተስፋሚካኤል ትኩእ (1892 – 1964)] - ወለዶና ክነቦ ዝግባእ መኽዘን ታሪኽ

Posted: 11 Jun 2019, 09:54
by Degnet
Meleket wrote:
08 Jun 2019, 06:03
በያንዳንዱ አንቀጽ ውስጥ ያለውን ረቂቅ መልእኽት ከቻላችሁ ፈልፍላችሁ አግኙት! ሰውየው የዋዛ አይመስሉም! :mrgreen:

“በእብደቴ ከሔድሁበት የቼሬናይካ ጦርነት ተመልሼ የጣሊያንን ሀገር ሮማን ጎብኝቼ ከተመለስኩ በኋላ ሰው ያልሆኑ ልዩ የእግዚኣብሔር ፍጡሮች አድርገን ስናያቸው የነበሩትን ኢጣሊያኖች እንደ እኛ አንዳች ብልጫና ልዩነትም የሌላቸው ሰዎች የዓዳምና የሄዋን ልጆች መሆናቸውን በትክክል አውቀን ትንሽ በትንሽም አእምሮ ገዛን።” ገጽ 31

“በሥራዮ መመለሴም ከቁም ነገር ቆጠርሁት፣ ፈረንሣዊ ለመማርም አሰብሁና ፊደል ስቆጥር ኢጣሊያኖች እንዳይጣሉኝ ስለፈራሁ የጽሕፈት ቤቱ ደብዳቤዎች በጣሊያንኛ አጻጻፍ ከወዳጄ ከጴጥሮስ ኢዶ ስማር ወደ የአሥመራ ከተማ ዙሪያ ገዥ ጽሕፈት ቤት አዞሩኝ። የዚሁም አለቃ አንድ ጥዮ ቢኒፋስ የተባለ በጉቦ የታወረ የጣሊያን ጸሓፊ አጥብቆ ጠላኝ፤ እያሳደደም ክፉ ደብዳቤ ጻፈብኝ፤ በሐሰትም አጠቃኝ። ንቀት መናቁንና ኩራት መኩራቱም ከልኩ አልፎ የተረፈ ነበር፤ ቅጥፈቱ ታውቆ ከሥራ እስክያስወግዱት ድረስ እውነት በሌላቸው ራፖሮቹ እኔን ሽባ አደረገኝ።” ገጽ 31

“የአሥመራ ዙሪያ ሀገረ ገዢም ኮመንዳቶረ ካቫሊ የተባለ በጥየ ቦኒፋስ የሐሰት ስብቅ ምክንያት የኔን ስም ለማንሳት ከመጥላቱ ብዛት የተነሳ “ያን ኩራተኛውን ጥሩት” ሲለኝ ነበር። ስለምን ወደ ቢሮው ሲገባና ሲወጣም ጫማውን ለሚጠርጉለት ለነ ባሻይ ምሕረተአብ ጫማውን በመጥረጋቸው ስድብ ስለምሰድባቸውባ ጐንበስ ብዬ እጅ ሳልነሳው እየተጋፋሁት በመግባቴና በመውጣቴም ብቻ ሳይሆን ቦኒፋስ በሚሰጠው የዕለቱ ወሬ በብዙ ጠላኝ። ከሁሎቹም ጋር አውቆ አጣላኝ።” ገጽ 31

“ወደ ፈተናም ተጠርቼ ቀረብሁና “ፈተናውን ወጥተሃል” አሉኝ፤ በሁለተኛው ፈተና ግን ወድቀህ ስለቀረህ ከሥራም ወጥተሐል” ሲሉኝ ጊዜ ዕለቱን ከአቶ ተክለ የኃላይ ልጅ ጋር ካሥመራ ወጥተን ቅናፍና አደርን። ከዚያም በኣንጉያ አድርገን፣ በባለ ታሪክ በአባ ገሪማ አድርገን ዓድዋ ገባን፤ በዚያም ጊዜ ትግሬን የሚገዙ ልዑል ራስ ሥዩም ነበሩ፤ ደፋሩ ልጃቸው ደጃዝማች ካሣም ሸፍተው በእርቅ ፩ሺህ ያህል ሰው ይዘው በታህሣሥ ወር ፲፱፻፲ዓ. ም. ሲገቡ ዓየሁ። ከዚያም ጓደኛዬ ተክለ ዓድዋ ስለቀረ ብቻዬን ወደ መቀለ መንገድ ስቀጥል ገና ከዓድዋ ስወጣ አንድ ከአኵሱም መጣሁ የሚል ጐበዝ ገጠመኝና ለጦቢት የሸኘው ቅዱስ ሩፋኤል ለኔም መጣልኝ ብዬ ፈጣሪዬ አመሰገንሁ። ከሽፍቶቹም ድነን መቀለ ገባን፤ ከዚያም ደሴ።” ገጽ 32

“በዚሁም ጊዜ በእንድርታ የነበረውን ሀብትና ለምለም፣ ቄጠማና ወኃ፣ በበለጠም ከአምባ አላጄ እስከ አላማጣ የነበረው ቦታ ሁሉ የፊተኛውን ዓመት ክምር ሳይወቃ እንደገና የገብስና ስንዴ ክምር ሲከመርና ግማሹ አብቦና እሸት ሆኖ፣ ግማሹም በቡቃያ አጌጦ የደስደስ ያለበት ሀገር የምድር ገነት ማለት አምባ አላጄና ማይጨው ኮሮም ነበር። ጣሊያን በ፲፱፻፲፩ዓ.ም. ከረገጠው ወዲህ በ፲፱፻፵፩ ዓ.ም. ሳየው ግን ያ ሀብቱንና ወኃው አልቆ፣ ዛፉ ተቆርጦ፣ አበባው ረግፎ ግርማው ተገፎ ሳየው አስለቀሰኝ። በኃጢያቴም አዛንሁ፣ ከአሥመራ እስከ ደሴም እባካችሁ ኑ ብሉልን፤ ኑ ጠጡልን ኣየተባልን ጥቂት ብሮች ስንቅ ይዘን በሰላም ያለ አንዳች ችግር እንኳንስ ልንታመም የታመመውን ሰው ምንም ሳናይ ወሎ ገባን፤ በወሎም ብዙ ሹም ሺር ሲደረግ ደረሰን። ደሴም ከሠራዊት ብዛት ድንኳን መትከያ ቦታ አልነበረም።” ገጽ 32

“በደሴ እንደገባን የጣሊያ አነጋጋሪ ብላታ መሐመድ ፈረጅ፣ የባንዳ አለቃ ባሻይ ተፈሪ ሌሎቹም የአከለጕዛይ ሰዎች ከቆንሱሉ ከኮንተ ፊሊጶስ ማላሳኒ ጋር አገኘሁዋቸውና “አትሔድም ትጣፋለህ ብላችሁ ተከራከሩት” የተባሉ ይመስል ለመሔድ ከለከሉኝና ቁንስሉም ነግረውት ጠርቶ የጣሊያን ቋንቋ አስተማሪና ጸሐፊም ሆኑህ ሥራ አለኝ። እኔም እሽ ብዬ ሥሠራ ኮንተ ማላሳኒ ወደ ሀገሩ ለመሔድ ሲነሳ በለውጡ ካቫሊዬር ዶሮሲ መጥና የዚሁ ልጅ አደራህን ብሎ አለው፤ ለኔም አስጠነቀቀኝ ወድ አሥመራ ተነስቶ ሄደ። እማስተምራቸውም የነበሩት የመኳንንት ልጆች ዣንጥራር አስፋው ገብረ መድኅን፣ ሐሰን በላይ ተፈሪ፣ አምሳለ ሰሎሞንና ሴቶችም ልጆች ነበሩባቸው። የፈረንጂ እጅ ለመጨበጥ የሚጸየፉ ራስ አባተም በዚያን ሀገር እሥረኛ ሆነው፣ ነዋሪነታቸው በዓዲ አቡን የነበረ አቡነ ጴጥሮስም ከአጼ ዮሐንስ ዘር በአዅሱም እንዳያነግሱ ተብሎ በማስገደድ ከትግሬ ወሎ አምጥተው የንጉሥ ሚካኤል አቡን አድርገው በደሴ ተቀማጭ ስለነበሩ፤ ለምሣ ቁንሱል ጋብዞዋቸው አሳማ መብላታችውን ሲጠይቃቸው አነጋጋሪ ነበርሁና ”ና አም” አዎን ሲሉ መለሱለት። ቅዳሴም በዐረብኛ ሲቀድሱ እሠማቸው ነበር።” ገጽ 32

“በ፲፱፻፷ ዓ.ም ንጉሥ ሚካኤል በብዙ እጀብ ታጅበው ከቢተወደድ ወሌ ቤት ተመልሰው ወደ ግቢ ሲሔዱ በጣሊያን ቆንሱል ደጃፍ ቁመው በበቅሎ ላይ ሆነው “ኮንቴ ማላሳኒ አለ” ብለው ጠየቁኝ፤ እኔም “ንጉሥ ሆይ የሉም” ብዬ መለስሁላቸውና ሔዱ። ንጉሥ ሚካኤል ብርቱ፣ ባለ ግርማ፣ ጢማምና ቁመተ ረጅም፤ ሃያማኖተኛ የአጴ ዮሐንስ የክርስትና ልጅ፣ ትግሮቹን የወደዱና ያከበሩ እውነተኛው ሚካኤልም ነበሩ።” ገጽ 32

“ከዚያም ቀን በፊት የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት መሪ ልጃቸው ልጅ ኢያሱ ሚካኤል ደሴ መጥተው ሳሉ የጣሊያን መንግሥት በግፍ የያዛትን ኤርትራ አያቴ ደጃዝማች ይማም ከሠራዬ ስለሚወለዱበት በመጭው ፲፱፻፱ ዓ.ም. መስከረም ሐማሴንን ለማስለቀቅ ዘመቻ እንዘምታለን ብለው ከወራሴ መንግሥት ከልጃቸው ጋር ውሳኔ ወስነው ስለነበርበዚሁ ትልቁ የዓለም ጦርነት የኛን የቃል ኪዳን ጓደኝነት እምቢ ብለው የተሰወረ የጀርመንን ቄሣር ወዳጅነት አበጅተዋልና “ነገ ጡዋትም ኢትዮጵያ በኛው ላይ በባላጋራነት ጦርነት ያስነሱብናልና በፖለቲካ ባለ ትልቅ ዋጋ ሰው የሚሆኑ ደጃዝማች ተፈሪ በመርዳት ልጅ ኢያሱ የወደቁበት እውነተኛው ምክንያት በመጀመሪያ ጠብ ያነሳሱባቸው ፈረንሣዊዎችና እንግሊዞች ናቸው” ሲል ሔንሪ ደ ምንፍረድ ወደ ጠበኞች የሆኑት የኢትዮጵያ ሀገሮች በሚል መጽሐፍ መሰከረባቸው።” ገጽ 33

“በዚሁም መጸሐፍ በመቅደላ የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት አጼ ቴዎድሮስ እንደ ሞቱ፣ ቱርኮች የሐረርን አውራጃ ለቀው ለመሔድ ውሳኔ እንደወሰኑ፣ እንግሊዞች ወደ ሐረር ገዢ ጦራቸውን ላኩ ሞግዝትነቱን ይቀበለናል ብለው፤ መታያቸውን ተቀብሎ ባንዴራቸውን ባጥር ግቢው ብቻ ተከለና እንግሊዞች የመጡበትን ጉዳይ በመፈጸማችው በብዙ ደስ ብሎዋቸው ከሐረር ግቢም ገና እንደወጡ፣ ከእንግሊዞች የባሰው ተንኮለኛው የሐረር ገዢ ገና በደስታ ወደ ባህር እንደተነሱና የሐረርን በሮች እንደወጡ በሚያንፀባርቅ ጌትነቱ ሕዝቡን በበዓላዊ ጥሪ ሰብስቦ የእንግሊዝን ባንዴራ በትልቁ ገበያ አቃጠለው። የእንግሊዝን ባንዴራ በድፍረት ካቃጠለው በኋላ አንድ ጦር እንግሊዞችን የሚደርስ ላከ። እነሱም ዙሪያቸውን ተከበው ሌት በመታረድ ተገደሉ። ቆይቶም ከጣሊያን መንግሥት ጋር አንድ የወዳጅነት ውል ከተዋዋለ በኋላ በሶማል ሀገር ከገቡ በኮንት ፓሮ የሚመሩት ዶክቶር ሳታርዲና፣ ዶክቶስ ዛኒኒ፣ ፕሮፌሰር ሊካታ፣ ኮንት ካርሎ ኮካስተሊ ከነተከታዎቻቸው በ፲፰፻፸፱ ዓ.ም በኢሳዎች ፈጽመው በመገደል አለቁ። በእነዚህ ሁለት ጊዜ መግደል በቀል ለመበቀል እንግሊዝ በዘይላዕ ቢሰናዳ ንጉሥ ምኒልክ “እኔ ደምህን እመልስልህ አለሁ” ብለው ለወንድማቸው ፲፭ሺህ ጦር አዛዥ አድርገው ቢልኩበት የሐረር ገዥ ግን ፭ሺ ብቻ ሰው ነበረውና ጣሊያን በሰጠው መድፍ ቢተኩስበት ከጨርጨር በሽሽት ደንግጠው ቢመለሱ ንጉሥ ምኒልክ አሩሲ ነበሩና በመላላክና በሰላዎችም ውስጥ ለውስጥ ሰሩበት፤” ገጽ 34

“በወራሴ መንግሥት ለልጅ ኢያሱ ሚካኤልም እንደዚህ ተብሎ ዘፈን ተዘፈነላቸው፤ “ኣባ ጤና ኢያሱ ሰባቱ መሳይ፣ ከደሴ ገስግሶ ግሚራ ገዳይ”። ስለምን ከደሴ ሔደው በግሚራ ዝሆን ስለገደሉና ከዚያም ወደ ሰዩ አቢጋር ዞረው በእንግሊዝ ጦር ላይ ግጭት አንስተው ፬ት መኰንኖችና ወታደሮችም ገድለው፣ ራሳችውም ቆስለው አዲስ አበባ ግቢ አገባለሁ ቢሉ ዘበኞች አናስገባም ብለው ቢሉዋቸው በኃይል ተጋፍተው ገቡ። እኔም ወዲያው ከዶሮሲ ጋር ተጣላሁና “እዚህ እኮ ኣሥመራ አይምሰልህ፤ ሥራህንም አልፈልግም ብዬው ወጣሁ” ፪ኛ ጦቢት አቶ ይዕብዩ ዑቁባዝጊን እግዚአብሔር ከአሥምመራ ዕለቱን አመጣልኝና አንድላይ ተነስተን በአልቡኮ፣ ደብረ ብርሃን አድርገን አዲስ አበባ ገባን።” ገጽ 34

“የላዛሪስት ሚሲዮን አባ ተስፋሥላሴ ወልደ ገሪማ ወደ ካፑቺን ሚሲዮን ለማስገባት ይዘውኝ ሔደን ትምሕርት ቤት አግቡኝ ብዬ ብለምናቸው፣ “ከኤርትራ ለመጣ ልጅ ሁሉ ምንም እንዳናገባ የጣሊያን መንግሥት በጥብቅ ከልክሎናልና ተማሪ ቤት ልናገባህ አንችልም” ስለ መለሱልኝ በብዙ ኅዘን አዘንሁ። የኢትዮጵያ መንግሥትንም አማሁ፤ ኣማደርገውም ጠፋኝ። በዚሁ እድፋም፣ እጅግ አዳፋ በሆነው የኢትዮጵያን ሕዝብ ለያይተው እጅ ለማድረግ በሚደክሙበት የማያቋርጥ ፖለቲካቸው ተደነቅሁ።” ገጽ 34

“. . . እኔም በዚያን መጥፎ ሌት ከቀን የተኩስ ጊዜ አዲስ አበባ መቀመጥ የጠላሁበት ምክንያት የሀገሩን አቀማመጥና የጊዜውም ፖለቲካ መለዋወጡንና የሰውም ልጅ ሥራ ሠርቶ በሰላም ለመኖር አለመቻሉንና አስፈላጊውን መብት አጥቶ ፀጥታም ባለማግኘቱ ምክንያት የልብ እረፍት በማጣቴ ነው።” ገጽ 35

“የዛሬ ንጉሠ ነገሥት ደጃዝማች ተፈሪም ራስ ተብለው ሐረርን ለቀው ከፋ እንዲሾሙ ብሉዋቸው ሐረርን አልለቅም ብለው ፲፭ አሽከሮች ይዘው አዲስ አበባ ባባታቸው ቤት ተቀምጠው ወደ የባለቤታቸው እናት ወደ ወይዘሮ ሲሂን ሚካኤል ቢተወደድ ኃይለ ጊዮርጊስን አግብተው ነበርና እሳቸው ዘንድ ከመመላለሳቸው በቀር ግቢ ዓይዘልቁም ነበር። የልጅ ኢያሱ ጸሐፌ ትእዛዝ አቶ ግዛው ሹምዬ ጩፋ ሰሜናኛው ነበርና የሱን ኮሮጀ ያዥ፣ በ፲፱፻፳፷ ዓ.ም. ለጣሊያን ሆኖ የከዳቸው፣ ተክለ ማርቆስ የተባለ የውራጌ “ያሪባ” ሲላላካቸው ስለነበረ የዚሁን ውለታ ብለው ደጃዝማች ተፈሪ ልጅ ኢያሱ በሰገሌ ማግስት በአንኮበር ዘልቀው ባደረጉት ግጭት አቶ ግዛው ሹሚዬ ሲሞት ተክለማርቆስ ተይዞ በራስ ተፈሪ ዘንድ ዚቀርብ፣ በግዛው ሹምዬ ጊዜ ይረዳቸው ስለነበረ፣ በተሰወረ ርዳታው ምክንያት በ፲ ወር እሥራት ብቻ ፈተው ለቀቁት። ብዙ የደከሙ ያባታቸው አሽከሮች ሳሉ ከእሥራት የተፈታውን የዛሬው ተክለ ማርቆስ አንስተው በግላቸው ጸሐፊ አደረጉት፤ ሰውም አየባቸው፣ አዘነም።” ገጽ 35

“ሰው ቢያዝን ቢያይባቸውም ራስ ተፈሪ ለተክለ ማርቆስ እያከታተሉ ባላምባራስ፣ ቀኛዝማች ብለ የጽሕፈት ሚኒስቴር ዋና ዲረክተርና የፖስታ ሚኒስተርም ቢሾሙት ያለ ድካም የተሾመውን ሱመት ባልታወቀ ምክንያት ጌታውን በክህደት ሸጦ የጣሊያን መንግሥት ሠላይ ሆነ፤ እነፍቅረ ሥላሴ ከተማም፤ ወርቁ አስታጥቄም አስቀድመው በግልጽ ወደ ጣሊያን ዞሩ። ቀኛዝማች ገብረአብና ቀኛዝማች ተሰማ አቡኔ፣ ቀኛዝማች ተክለ ማርቆስ፣ ቀኛዝማች ከልክሌ ወርቁ፣ እነ ብላቴን ጌታ ኅሩይ፣ ሊጋባ ሀብተ ሚካኣኤል አጥብቀው ቢወዱዋቸውም ንጉሠ ነገሥት ጋር ተጣልተው ርዳታቸውና ፍቅራቸው ለጣሊያን ሆኑ ብላቴን ጌታ ኅሩይም ለእንግሊዝ።” ገጽ 36

“ደጃዝማች ተፈሪ መኰንን ራስ ተብለው ወደ ከፋ ይህዱ ቢሉዋቸው አልሔድም ብለው ሲከራከሩ የሸዋ ሰው መስተንግዶ ሲያዘንብላቸው፣ በሐረርም ለስሙ ፊተውራሪ ገብሬ ቢሆኑ ሥራዉን የሚያኬዱት ጨዋ የጨዋ ልጅ ቀኛዝማች እምሩ ኃይለ ሥላሴ አባይነህ የ፲፭ ደጃዝማጮች እንደራሴ( የዛሬው ራስ) ነበሩ። እኔም በዚህ ጊዜ ምክር አዋቂው የኢትዮጵያ ጦር ሚኒስተር ባለ ታሪክ ፊተውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስን ለማየት ምኞት ስለነበረኝ ፫ት ቀን በአጀባቸው መካከል ሆነው በበቅሎ ሲሔዱ አየሁዋቸውና መልካቸውና የፖለቲካቸውም ረቂቅ ሁናቴ ሳመዛዝነው ስለተራራቀብኝ ተገረምሁ። በዛሬም ኢትዮጵያ ባለሥልጣኖች ዘንድ ፊተውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ፣ ደጃዝማች ባልቻ የመንግሥት ጉዳይ አሳቢዎች፣ በእውነተኛው የሀገር ፍቅር ፈረንጅ የማይፈቅዱ ነበሩ።” ገጽ 36

"ደጃዝማች አብርሃ አርአያ ከዚያው ትምሕርታቸውና ወጣቱ ሰውነታችው፣ ወርቅ ከመሰለ ወደረኛ ከሌለው ቅላታቸው ጋር፣ ከኣኒያ እሳቶች የሆኑት የትግሬ አሽከሮቻቸው ሲሔዱ እንደመብረቅ፣ ዓይቻቸው ሳልጠግባቸው ከእውቀትና ከወንድነት ጋር ከፈ ያለ ድፍረትና ንቃትም ያላቸው ሰው ሆነው ታዩኝ። የልጅ ኢያሱ ወገን ነበሩና በሰገሌ ጊዜ ደጃዝማች አብርሃ አርአያና ደጃዝማች አመዴ ወሌ ብጡል ሁለቱ ትግሮች ባንድግዜ ሞቱ ማለትን ሰማን፤ በዚሁም ጊዜ አዲስ አበባ በጭቃ የተሞላች “ፊንፍኔ” የተባለች ዱርና ገደል ነበረች። ይህም ከተማ አጼ ምኒልክ በሌሉበት ከኣንጦጦ ፍልወኃ ለመታጠብ ወርደው ኮረብታይቱን ለከተማነት የመረጡዋት፣ የቆረቆሩዋት የሸዋን ቤተ መንግሥት በችሎታዊው ድፍረትና እውቀታቸው ብዛት ያቋቋሙት እቴጌ ጣይቱ ብጡል ናቸው። የሸዋ ንጉሥ ምኒልክ ግን ውራጌዎችንንና ኦሮሞዎችን ስለፈሩ ቆጥ በመሰለው የኣንቶቶ ገደል ሠፈሩ፤ ወድትዋ የሴቶች መመክያ እቴጌ ጣይቱ ግን በትግሮችና በሰሜነኞች አሽከሮቻቸውና በእውቀታቸው ብዛት ዘው አስጭነው ኢትዮጵያን አስገዙዋቸው።" ገጽ 36

"የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ጃንሆይ አጼ ዮሐንስ በምጽዋዕ ያለ ማቋረጥ ከቱርክ በጎዳጉድና በጕራዕ፣ ከጣሊያን በሰሐቲ እየተዋጕ ለንጉሥ ምኒልክ ሐረርና አሩሲ፣ ጂማና ከፋ፣ ለቀምት እንትይዝ ብለው ፫ ጊዘ የቁጣ ቃል ጻፉላቸው፤ ያልሰማና ያላየ ሰውም ምኒልክ አሥፋፋት ብሎ ያላል። ይህኑኑም ሀገር ሁሉ በጀግንነት ያቀኑት ደጃዝማች ጐበና ናቸው፤ እሳቸው በያዙት ሀገር ሱኡን ራስ ተባለበት። ጀግናው ደጃዝማች ጐበና ግን ጉዳታቸው ለአጼ ዮሐንስ እንኳ አቤቱታ ሳይልኩ የራስ ማዕረግ አልተሰጣቸው፤ ስለምን የጀግና ጠላቶች ቁጥር የላቸውም እና ከሽሽታዎቹ (ከሸሽዎቹ ከፈሪዎቹ) በኋላ በመቀበላችወ አስደነቀ። አጼ ዮሐንስ ለሸዋ ንጉሥ ምኒልክ ጣሊያኖች ፈጽመው ከሸዋ መሬት ለቀው በግዴታ እንዲወጡ፣ አንተም ገረርና አሩሲን ጂማና ከፋ ለቀምትና ምዕራብ ሀገሮች ሁሉ በፍጥነት እንድትይዛቸው ይሁን እያሉ ፫ት ጊዜ መጻፋቸው ለማንም ሰው የተሰወረ አለመሆኑን አስገነዝባለሁ። እውነተኛው ጽሑፍና ሐሰተኛው የኣፍ ታሪክ ለየራሱ ስለሆነ፣ እውነትን ወደ ሐሰት ለመለወጥ ስለማይቻል በከንቱ ለደከሙና ለሚደክሙ ሰዎች አዝንላቸው አለሁ እንጂ አላዝንባቸውም።" ገጽ 37

ባለታሪኩ “ከአዲስ አበባ በጂቡቲና በአደን መንገድ መቃድሾ ስለሜሔዳቸው” ትረካቸውን ይቀጥሉልናል!
Thank you a lot,I always wanted to know how and when dej.Abraha Araya,it is a historic book.

Re: ተስፋሚካኤል ትኩእ (1892 – 1964)] - ወለዶና ክነቦ ዝግባእ መኽዘን ታሪኽ

Posted: 11 Jun 2019, 09:56
by Degnet
Meleket wrote:
08 Jun 2019, 06:03
በያንዳንዱ አንቀጽ ውስጥ ያለውን ረቂቅ መልእኽት ከቻላችሁ ፈልፍላችሁ አግኙት! ሰውየው የዋዛ አይመስሉም! :mrgreen:

“በእብደቴ ከሔድሁበት የቼሬናይካ ጦርነት ተመልሼ የጣሊያንን ሀገር ሮማን ጎብኝቼ ከተመለስኩ በኋላ ሰው ያልሆኑ ልዩ የእግዚኣብሔር ፍጡሮች አድርገን ስናያቸው የነበሩትን ኢጣሊያኖች እንደ እኛ አንዳች ብልጫና ልዩነትም የሌላቸው ሰዎች የዓዳምና የሄዋን ልጆች መሆናቸውን በትክክል አውቀን ትንሽ በትንሽም አእምሮ ገዛን።” ገጽ 31

“በሥራዮ መመለሴም ከቁም ነገር ቆጠርሁት፣ ፈረንሣዊ ለመማርም አሰብሁና ፊደል ስቆጥር ኢጣሊያኖች እንዳይጣሉኝ ስለፈራሁ የጽሕፈት ቤቱ ደብዳቤዎች በጣሊያንኛ አጻጻፍ ከወዳጄ ከጴጥሮስ ኢዶ ስማር ወደ የአሥመራ ከተማ ዙሪያ ገዥ ጽሕፈት ቤት አዞሩኝ። የዚሁም አለቃ አንድ ጥዮ ቢኒፋስ የተባለ በጉቦ የታወረ የጣሊያን ጸሓፊ አጥብቆ ጠላኝ፤ እያሳደደም ክፉ ደብዳቤ ጻፈብኝ፤ በሐሰትም አጠቃኝ። ንቀት መናቁንና ኩራት መኩራቱም ከልኩ አልፎ የተረፈ ነበር፤ ቅጥፈቱ ታውቆ ከሥራ እስክያስወግዱት ድረስ እውነት በሌላቸው ራፖሮቹ እኔን ሽባ አደረገኝ።” ገጽ 31

“የአሥመራ ዙሪያ ሀገረ ገዢም ኮመንዳቶረ ካቫሊ የተባለ በጥየ ቦኒፋስ የሐሰት ስብቅ ምክንያት የኔን ስም ለማንሳት ከመጥላቱ ብዛት የተነሳ “ያን ኩራተኛውን ጥሩት” ሲለኝ ነበር። ስለምን ወደ ቢሮው ሲገባና ሲወጣም ጫማውን ለሚጠርጉለት ለነ ባሻይ ምሕረተአብ ጫማውን በመጥረጋቸው ስድብ ስለምሰድባቸውባ ጐንበስ ብዬ እጅ ሳልነሳው እየተጋፋሁት በመግባቴና በመውጣቴም ብቻ ሳይሆን ቦኒፋስ በሚሰጠው የዕለቱ ወሬ በብዙ ጠላኝ። ከሁሎቹም ጋር አውቆ አጣላኝ።” ገጽ 31

“ወደ ፈተናም ተጠርቼ ቀረብሁና “ፈተናውን ወጥተሃል” አሉኝ፤ በሁለተኛው ፈተና ግን ወድቀህ ስለቀረህ ከሥራም ወጥተሐል” ሲሉኝ ጊዜ ዕለቱን ከአቶ ተክለ የኃላይ ልጅ ጋር ካሥመራ ወጥተን ቅናፍና አደርን። ከዚያም በኣንጉያ አድርገን፣ በባለ ታሪክ በአባ ገሪማ አድርገን ዓድዋ ገባን፤ በዚያም ጊዜ ትግሬን የሚገዙ ልዑል ራስ ሥዩም ነበሩ፤ ደፋሩ ልጃቸው ደጃዝማች ካሣም ሸፍተው በእርቅ ፩ሺህ ያህል ሰው ይዘው በታህሣሥ ወር ፲፱፻፲ዓ. ም. ሲገቡ ዓየሁ። ከዚያም ጓደኛዬ ተክለ ዓድዋ ስለቀረ ብቻዬን ወደ መቀለ መንገድ ስቀጥል ገና ከዓድዋ ስወጣ አንድ ከአኵሱም መጣሁ የሚል ጐበዝ ገጠመኝና ለጦቢት የሸኘው ቅዱስ ሩፋኤል ለኔም መጣልኝ ብዬ ፈጣሪዬ አመሰገንሁ። ከሽፍቶቹም ድነን መቀለ ገባን፤ ከዚያም ደሴ።” ገጽ 32

“በዚሁም ጊዜ በእንድርታ የነበረውን ሀብትና ለምለም፣ ቄጠማና ወኃ፣ በበለጠም ከአምባ አላጄ እስከ አላማጣ የነበረው ቦታ ሁሉ የፊተኛውን ዓመት ክምር ሳይወቃ እንደገና የገብስና ስንዴ ክምር ሲከመርና ግማሹ አብቦና እሸት ሆኖ፣ ግማሹም በቡቃያ አጌጦ የደስደስ ያለበት ሀገር የምድር ገነት ማለት አምባ አላጄና ማይጨው ኮሮም ነበር። ጣሊያን በ፲፱፻፲፩ዓ.ም. ከረገጠው ወዲህ በ፲፱፻፵፩ ዓ.ም. ሳየው ግን ያ ሀብቱንና ወኃው አልቆ፣ ዛፉ ተቆርጦ፣ አበባው ረግፎ ግርማው ተገፎ ሳየው አስለቀሰኝ። በኃጢያቴም አዛንሁ፣ ከአሥመራ እስከ ደሴም እባካችሁ ኑ ብሉልን፤ ኑ ጠጡልን ኣየተባልን ጥቂት ብሮች ስንቅ ይዘን በሰላም ያለ አንዳች ችግር እንኳንስ ልንታመም የታመመውን ሰው ምንም ሳናይ ወሎ ገባን፤ በወሎም ብዙ ሹም ሺር ሲደረግ ደረሰን። ደሴም ከሠራዊት ብዛት ድንኳን መትከያ ቦታ አልነበረም።” ገጽ 32

“በደሴ እንደገባን የጣሊያ አነጋጋሪ ብላታ መሐመድ ፈረጅ፣ የባንዳ አለቃ ባሻይ ተፈሪ ሌሎቹም የአከለጕዛይ ሰዎች ከቆንሱሉ ከኮንተ ፊሊጶስ ማላሳኒ ጋር አገኘሁዋቸውና “አትሔድም ትጣፋለህ ብላችሁ ተከራከሩት” የተባሉ ይመስል ለመሔድ ከለከሉኝና ቁንስሉም ነግረውት ጠርቶ የጣሊያን ቋንቋ አስተማሪና ጸሐፊም ሆኑህ ሥራ አለኝ። እኔም እሽ ብዬ ሥሠራ ኮንተ ማላሳኒ ወደ ሀገሩ ለመሔድ ሲነሳ በለውጡ ካቫሊዬር ዶሮሲ መጥና የዚሁ ልጅ አደራህን ብሎ አለው፤ ለኔም አስጠነቀቀኝ ወድ አሥመራ ተነስቶ ሄደ። እማስተምራቸውም የነበሩት የመኳንንት ልጆች ዣንጥራር አስፋው ገብረ መድኅን፣ ሐሰን በላይ ተፈሪ፣ አምሳለ ሰሎሞንና ሴቶችም ልጆች ነበሩባቸው። የፈረንጂ እጅ ለመጨበጥ የሚጸየፉ ራስ አባተም በዚያን ሀገር እሥረኛ ሆነው፣ ነዋሪነታቸው በዓዲ አቡን የነበረ አቡነ ጴጥሮስም ከአጼ ዮሐንስ ዘር በአዅሱም እንዳያነግሱ ተብሎ በማስገደድ ከትግሬ ወሎ አምጥተው የንጉሥ ሚካኤል አቡን አድርገው በደሴ ተቀማጭ ስለነበሩ፤ ለምሣ ቁንሱል ጋብዞዋቸው አሳማ መብላታችውን ሲጠይቃቸው አነጋጋሪ ነበርሁና ”ና አም” አዎን ሲሉ መለሱለት። ቅዳሴም በዐረብኛ ሲቀድሱ እሠማቸው ነበር።” ገጽ 32

“በ፲፱፻፷ ዓ.ም ንጉሥ ሚካኤል በብዙ እጀብ ታጅበው ከቢተወደድ ወሌ ቤት ተመልሰው ወደ ግቢ ሲሔዱ በጣሊያን ቆንሱል ደጃፍ ቁመው በበቅሎ ላይ ሆነው “ኮንቴ ማላሳኒ አለ” ብለው ጠየቁኝ፤ እኔም “ንጉሥ ሆይ የሉም” ብዬ መለስሁላቸውና ሔዱ። ንጉሥ ሚካኤል ብርቱ፣ ባለ ግርማ፣ ጢማምና ቁመተ ረጅም፤ ሃያማኖተኛ የአጴ ዮሐንስ የክርስትና ልጅ፣ ትግሮቹን የወደዱና ያከበሩ እውነተኛው ሚካኤልም ነበሩ።” ገጽ 32

“ከዚያም ቀን በፊት የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት መሪ ልጃቸው ልጅ ኢያሱ ሚካኤል ደሴ መጥተው ሳሉ የጣሊያን መንግሥት በግፍ የያዛትን ኤርትራ አያቴ ደጃዝማች ይማም ከሠራዬ ስለሚወለዱበት በመጭው ፲፱፻፱ ዓ.ም. መስከረም ሐማሴንን ለማስለቀቅ ዘመቻ እንዘምታለን ብለው ከወራሴ መንግሥት ከልጃቸው ጋር ውሳኔ ወስነው ስለነበርበዚሁ ትልቁ የዓለም ጦርነት የኛን የቃል ኪዳን ጓደኝነት እምቢ ብለው የተሰወረ የጀርመንን ቄሣር ወዳጅነት አበጅተዋልና “ነገ ጡዋትም ኢትዮጵያ በኛው ላይ በባላጋራነት ጦርነት ያስነሱብናልና በፖለቲካ ባለ ትልቅ ዋጋ ሰው የሚሆኑ ደጃዝማች ተፈሪ በመርዳት ልጅ ኢያሱ የወደቁበት እውነተኛው ምክንያት በመጀመሪያ ጠብ ያነሳሱባቸው ፈረንሣዊዎችና እንግሊዞች ናቸው” ሲል ሔንሪ ደ ምንፍረድ ወደ ጠበኞች የሆኑት የኢትዮጵያ ሀገሮች በሚል መጽሐፍ መሰከረባቸው።” ገጽ 33

“በዚሁም መጸሐፍ በመቅደላ የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት አጼ ቴዎድሮስ እንደ ሞቱ፣ ቱርኮች የሐረርን አውራጃ ለቀው ለመሔድ ውሳኔ እንደወሰኑ፣ እንግሊዞች ወደ ሐረር ገዢ ጦራቸውን ላኩ ሞግዝትነቱን ይቀበለናል ብለው፤ መታያቸውን ተቀብሎ ባንዴራቸውን ባጥር ግቢው ብቻ ተከለና እንግሊዞች የመጡበትን ጉዳይ በመፈጸማችው በብዙ ደስ ብሎዋቸው ከሐረር ግቢም ገና እንደወጡ፣ ከእንግሊዞች የባሰው ተንኮለኛው የሐረር ገዢ ገና በደስታ ወደ ባህር እንደተነሱና የሐረርን በሮች እንደወጡ በሚያንፀባርቅ ጌትነቱ ሕዝቡን በበዓላዊ ጥሪ ሰብስቦ የእንግሊዝን ባንዴራ በትልቁ ገበያ አቃጠለው። የእንግሊዝን ባንዴራ በድፍረት ካቃጠለው በኋላ አንድ ጦር እንግሊዞችን የሚደርስ ላከ። እነሱም ዙሪያቸውን ተከበው ሌት በመታረድ ተገደሉ። ቆይቶም ከጣሊያን መንግሥት ጋር አንድ የወዳጅነት ውል ከተዋዋለ በኋላ በሶማል ሀገር ከገቡ በኮንት ፓሮ የሚመሩት ዶክቶር ሳታርዲና፣ ዶክቶስ ዛኒኒ፣ ፕሮፌሰር ሊካታ፣ ኮንት ካርሎ ኮካስተሊ ከነተከታዎቻቸው በ፲፰፻፸፱ ዓ.ም በኢሳዎች ፈጽመው በመገደል አለቁ። በእነዚህ ሁለት ጊዜ መግደል በቀል ለመበቀል እንግሊዝ በዘይላዕ ቢሰናዳ ንጉሥ ምኒልክ “እኔ ደምህን እመልስልህ አለሁ” ብለው ለወንድማቸው ፲፭ሺህ ጦር አዛዥ አድርገው ቢልኩበት የሐረር ገዥ ግን ፭ሺ ብቻ ሰው ነበረውና ጣሊያን በሰጠው መድፍ ቢተኩስበት ከጨርጨር በሽሽት ደንግጠው ቢመለሱ ንጉሥ ምኒልክ አሩሲ ነበሩና በመላላክና በሰላዎችም ውስጥ ለውስጥ ሰሩበት፤” ገጽ 34

“በወራሴ መንግሥት ለልጅ ኢያሱ ሚካኤልም እንደዚህ ተብሎ ዘፈን ተዘፈነላቸው፤ “ኣባ ጤና ኢያሱ ሰባቱ መሳይ፣ ከደሴ ገስግሶ ግሚራ ገዳይ”። ስለምን ከደሴ ሔደው በግሚራ ዝሆን ስለገደሉና ከዚያም ወደ ሰዩ አቢጋር ዞረው በእንግሊዝ ጦር ላይ ግጭት አንስተው ፬ት መኰንኖችና ወታደሮችም ገድለው፣ ራሳችውም ቆስለው አዲስ አበባ ግቢ አገባለሁ ቢሉ ዘበኞች አናስገባም ብለው ቢሉዋቸው በኃይል ተጋፍተው ገቡ። እኔም ወዲያው ከዶሮሲ ጋር ተጣላሁና “እዚህ እኮ ኣሥመራ አይምሰልህ፤ ሥራህንም አልፈልግም ብዬው ወጣሁ” ፪ኛ ጦቢት አቶ ይዕብዩ ዑቁባዝጊን እግዚአብሔር ከአሥምመራ ዕለቱን አመጣልኝና አንድላይ ተነስተን በአልቡኮ፣ ደብረ ብርሃን አድርገን አዲስ አበባ ገባን።” ገጽ 34

“የላዛሪስት ሚሲዮን አባ ተስፋሥላሴ ወልደ ገሪማ ወደ ካፑቺን ሚሲዮን ለማስገባት ይዘውኝ ሔደን ትምሕርት ቤት አግቡኝ ብዬ ብለምናቸው፣ “ከኤርትራ ለመጣ ልጅ ሁሉ ምንም እንዳናገባ የጣሊያን መንግሥት በጥብቅ ከልክሎናልና ተማሪ ቤት ልናገባህ አንችልም” ስለ መለሱልኝ በብዙ ኅዘን አዘንሁ። የኢትዮጵያ መንግሥትንም አማሁ፤ ኣማደርገውም ጠፋኝ። በዚሁ እድፋም፣ እጅግ አዳፋ በሆነው የኢትዮጵያን ሕዝብ ለያይተው እጅ ለማድረግ በሚደክሙበት የማያቋርጥ ፖለቲካቸው ተደነቅሁ።” ገጽ 34

“. . . እኔም በዚያን መጥፎ ሌት ከቀን የተኩስ ጊዜ አዲስ አበባ መቀመጥ የጠላሁበት ምክንያት የሀገሩን አቀማመጥና የጊዜውም ፖለቲካ መለዋወጡንና የሰውም ልጅ ሥራ ሠርቶ በሰላም ለመኖር አለመቻሉንና አስፈላጊውን መብት አጥቶ ፀጥታም ባለማግኘቱ ምክንያት የልብ እረፍት በማጣቴ ነው።” ገጽ 35

“የዛሬ ንጉሠ ነገሥት ደጃዝማች ተፈሪም ራስ ተብለው ሐረርን ለቀው ከፋ እንዲሾሙ ብሉዋቸው ሐረርን አልለቅም ብለው ፲፭ አሽከሮች ይዘው አዲስ አበባ ባባታቸው ቤት ተቀምጠው ወደ የባለቤታቸው እናት ወደ ወይዘሮ ሲሂን ሚካኤል ቢተወደድ ኃይለ ጊዮርጊስን አግብተው ነበርና እሳቸው ዘንድ ከመመላለሳቸው በቀር ግቢ ዓይዘልቁም ነበር። የልጅ ኢያሱ ጸሐፌ ትእዛዝ አቶ ግዛው ሹምዬ ጩፋ ሰሜናኛው ነበርና የሱን ኮሮጀ ያዥ፣ በ፲፱፻፳፷ ዓ.ም. ለጣሊያን ሆኖ የከዳቸው፣ ተክለ ማርቆስ የተባለ የውራጌ “ያሪባ” ሲላላካቸው ስለነበረ የዚሁን ውለታ ብለው ደጃዝማች ተፈሪ ልጅ ኢያሱ በሰገሌ ማግስት በአንኮበር ዘልቀው ባደረጉት ግጭት አቶ ግዛው ሹሚዬ ሲሞት ተክለማርቆስ ተይዞ በራስ ተፈሪ ዘንድ ዚቀርብ፣ በግዛው ሹምዬ ጊዜ ይረዳቸው ስለነበረ፣ በተሰወረ ርዳታው ምክንያት በ፲ ወር እሥራት ብቻ ፈተው ለቀቁት። ብዙ የደከሙ ያባታቸው አሽከሮች ሳሉ ከእሥራት የተፈታውን የዛሬው ተክለ ማርቆስ አንስተው በግላቸው ጸሐፊ አደረጉት፤ ሰውም አየባቸው፣ አዘነም።” ገጽ 35

“ሰው ቢያዝን ቢያይባቸውም ራስ ተፈሪ ለተክለ ማርቆስ እያከታተሉ ባላምባራስ፣ ቀኛዝማች ብለ የጽሕፈት ሚኒስቴር ዋና ዲረክተርና የፖስታ ሚኒስተርም ቢሾሙት ያለ ድካም የተሾመውን ሱመት ባልታወቀ ምክንያት ጌታውን በክህደት ሸጦ የጣሊያን መንግሥት ሠላይ ሆነ፤ እነፍቅረ ሥላሴ ከተማም፤ ወርቁ አስታጥቄም አስቀድመው በግልጽ ወደ ጣሊያን ዞሩ። ቀኛዝማች ገብረአብና ቀኛዝማች ተሰማ አቡኔ፣ ቀኛዝማች ተክለ ማርቆስ፣ ቀኛዝማች ከልክሌ ወርቁ፣ እነ ብላቴን ጌታ ኅሩይ፣ ሊጋባ ሀብተ ሚካኣኤል አጥብቀው ቢወዱዋቸውም ንጉሠ ነገሥት ጋር ተጣልተው ርዳታቸውና ፍቅራቸው ለጣሊያን ሆኑ ብላቴን ጌታ ኅሩይም ለእንግሊዝ።” ገጽ 36

“ደጃዝማች ተፈሪ መኰንን ራስ ተብለው ወደ ከፋ ይህዱ ቢሉዋቸው አልሔድም ብለው ሲከራከሩ የሸዋ ሰው መስተንግዶ ሲያዘንብላቸው፣ በሐረርም ለስሙ ፊተውራሪ ገብሬ ቢሆኑ ሥራዉን የሚያኬዱት ጨዋ የጨዋ ልጅ ቀኛዝማች እምሩ ኃይለ ሥላሴ አባይነህ የ፲፭ ደጃዝማጮች እንደራሴ( የዛሬው ራስ) ነበሩ። እኔም በዚህ ጊዜ ምክር አዋቂው የኢትዮጵያ ጦር ሚኒስተር ባለ ታሪክ ፊተውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስን ለማየት ምኞት ስለነበረኝ ፫ት ቀን በአጀባቸው መካከል ሆነው በበቅሎ ሲሔዱ አየሁዋቸውና መልካቸውና የፖለቲካቸውም ረቂቅ ሁናቴ ሳመዛዝነው ስለተራራቀብኝ ተገረምሁ። በዛሬም ኢትዮጵያ ባለሥልጣኖች ዘንድ ፊተውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ፣ ደጃዝማች ባልቻ የመንግሥት ጉዳይ አሳቢዎች፣ በእውነተኛው የሀገር ፍቅር ፈረንጅ የማይፈቅዱ ነበሩ።” ገጽ 36

"ደጃዝማች አብርሃ አርአያ ከዚያው ትምሕርታቸውና ወጣቱ ሰውነታችው፣ ወርቅ ከመሰለ ወደረኛ ከሌለው ቅላታቸው ጋር፣ ከኣኒያ እሳቶች የሆኑት የትግሬ አሽከሮቻቸው ሲሔዱ እንደመብረቅ፣ ዓይቻቸው ሳልጠግባቸው ከእውቀትና ከወንድነት ጋር ከፈ ያለ ድፍረትና ንቃትም ያላቸው ሰው ሆነው ታዩኝ። የልጅ ኢያሱ ወገን ነበሩና በሰገሌ ጊዜ ደጃዝማች አብርሃ አርአያና ደጃዝማች አመዴ ወሌ ብጡል ሁለቱ ትግሮች ባንድግዜ ሞቱ ማለትን ሰማን፤ በዚሁም ጊዜ አዲስ አበባ በጭቃ የተሞላች “ፊንፍኔ” የተባለች ዱርና ገደል ነበረች። ይህም ከተማ አጼ ምኒልክ በሌሉበት ከኣንጦጦ ፍልወኃ ለመታጠብ ወርደው ኮረብታይቱን ለከተማነት የመረጡዋት፣ የቆረቆሩዋት የሸዋን ቤተ መንግሥት በችሎታዊው ድፍረትና እውቀታቸው ብዛት ያቋቋሙት እቴጌ ጣይቱ ብጡል ናቸው። የሸዋ ንጉሥ ምኒልክ ግን ውራጌዎችንንና ኦሮሞዎችን ስለፈሩ ቆጥ በመሰለው የኣንቶቶ ገደል ሠፈሩ፤ ወድትዋ የሴቶች መመክያ እቴጌ ጣይቱ ግን በትግሮችና በሰሜነኞች አሽከሮቻቸውና በእውቀታቸው ብዛት ዘው አስጭነው ኢትዮጵያን አስገዙዋቸው።" ገጽ 36

"የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ጃንሆይ አጼ ዮሐንስ በምጽዋዕ ያለ ማቋረጥ ከቱርክ በጎዳጉድና በጕራዕ፣ ከጣሊያን በሰሐቲ እየተዋጕ ለንጉሥ ምኒልክ ሐረርና አሩሲ፣ ጂማና ከፋ፣ ለቀምት እንትይዝ ብለው ፫ ጊዘ የቁጣ ቃል ጻፉላቸው፤ ያልሰማና ያላየ ሰውም ምኒልክ አሥፋፋት ብሎ ያላል። ይህኑኑም ሀገር ሁሉ በጀግንነት ያቀኑት ደጃዝማች ጐበና ናቸው፤ እሳቸው በያዙት ሀገር ሱኡን ራስ ተባለበት። ጀግናው ደጃዝማች ጐበና ግን ጉዳታቸው ለአጼ ዮሐንስ እንኳ አቤቱታ ሳይልኩ የራስ ማዕረግ አልተሰጣቸው፤ ስለምን የጀግና ጠላቶች ቁጥር የላቸውም እና ከሽሽታዎቹ (ከሸሽዎቹ ከፈሪዎቹ) በኋላ በመቀበላችወ አስደነቀ። አጼ ዮሐንስ ለሸዋ ንጉሥ ምኒልክ ጣሊያኖች ፈጽመው ከሸዋ መሬት ለቀው በግዴታ እንዲወጡ፣ አንተም ገረርና አሩሲን ጂማና ከፋ ለቀምትና ምዕራብ ሀገሮች ሁሉ በፍጥነት እንድትይዛቸው ይሁን እያሉ ፫ት ጊዜ መጻፋቸው ለማንም ሰው የተሰወረ አለመሆኑን አስገነዝባለሁ። እውነተኛው ጽሑፍና ሐሰተኛው የኣፍ ታሪክ ለየራሱ ስለሆነ፣ እውነትን ወደ ሐሰት ለመለወጥ ስለማይቻል በከንቱ ለደከሙና ለሚደክሙ ሰዎች አዝንላቸው አለሁ እንጂ አላዝንባቸውም።" ገጽ 37

ባለታሪኩ “ከአዲስ አበባ በጂቡቲና በአደን መንገድ መቃድሾ ስለሜሔዳቸው” ትረካቸውን ይቀጥሉልናል!
Thank you a lot,I always wanted to know how and when dej.Abraha Araya died ,it is a historic book.I think I have said enough,I will go back to my reading now.

Re: ተስፋሚካኤል ትኩእ (1892 – 1964)] - ወለዶና ክነቦ ዝግባእ መኽዘን ታሪኽ

Posted: 11 Jun 2019, 11:06
by Meleket
Degnet wrote:
11 Jun 2019, 09:56
Meleket wrote:
08 Jun 2019, 06:03
በያንዳንዱ አንቀጽ ውስጥ ያለውን ረቂቅ መልእኽት ከቻላችሁ ፈልፍላችሁ አግኙት! ሰውየው የዋዛ አይመስሉም! :mrgreen:
...
Thank you a lot,I always wanted to know how and when dej.Abraha Araya died ,it is a historic book.I think I have said enough,I will go back to my reading now.
ደግነት ወንድሜ ግዜ ስታገኝ መጸሐፉን ከጫፍ እስከ ጫፍ ለማንበብ ሞክር፣ እኔ አለፍ አለፍ እያልኩ ስለሆነ ለማካፈል የሞከርኩት። አብርሃ አርአያ የሚል ስም እስካሁን ቢያንስ ቢያንስ ሁለት ጊዜ ተጠቅሰዋል፡
አንደኛው በገጽ 13 ልጅ አብርሃ አርአያ ተብሎ
Meleket wrote:
07 Jun 2019, 11:55

"አልጋ ፈላጊ ሆነው በአሳኦርታና በጠልጣል እያሉ በጽናት ሲቀመጡ የነበሩበትን የደጃዝማች ደበብ አራአያም የ፲፪ ዓመት ልጅ ወንድማቸው ልጅ አብርሃ አርአያን መያዣ ሰጥተው ፫፻ ወጨፎ ጠበንጃ ከነ ጥይቱ ከጣሊያን መቀበላቸውን ደጃዝማች ባህታን ለመግደል መሰናዳታቸውን ስለ ሰሙ የደጃዝማች ባህታም ከሀባብ ወደ ምፅዋዕ በመምጣት ለጣሊያን እጃቸውን ሰጡ።" ገጽ 13
ሁለተኛው በገጽ 36 ደጃዝማች አብርሃ አርአያ ተብለው
Meleket wrote:
08 Jun 2019, 06:03

"ደጃዝማች አብርሃ አርአያ ከዚያው ትምሕርታቸውና ወጣቱ ሰውነታችው፣ ወርቅ ከመሰለ ወደረኛ ከሌለው ቅላታቸው ጋር፣ ከኣኒያ እሳቶች የሆኑት የትግሬ አሽከሮቻቸው ሲሔዱ እንደመብረቅ፣ ዓይቻቸው ሳልጠግባቸው ከእውቀትና ከወንድነት ጋር ከፈ ያለ ድፍረትና ንቃትም ያላቸው ሰው ሆነው ታዩኝ። የልጅ ኢያሱ ወገን ነበሩና በሰገሌ ጊዜ ደጃዝማች አብርሃ አርአያና ደጃዝማች አመዴ ወሌ ብጡል ሁለቱ ትግሮች ባንድግዜ ሞቱ ማለትን ሰማን፤ በዚሁም ጊዜ አዲስ አበባ በጭቃ የተሞላች “ፊንፍኔ” የተባለች ዱርና ገደል ነበረች። ይህም ከተማ አጼ ምኒልክ በሌሉበት ከኣንጦጦ ፍልወኃ ለመታጠብ ወርደው ኮረብታይቱን ለከተማነት የመረጡዋት፣ የቆረቆሩዋት የሸዋን ቤተ መንግሥት በችሎታዊው ድፍረትና እውቀታቸው ብዛት ያቋቋሙት እቴጌ ጣይቱ ብጡል ናቸው። የሸዋ ንጉሥ ምኒልክ ግን ውራጌዎችንንና ኦሮሞዎችን ስለፈሩ ቆጥ በመሰለው የኣንቶቶ ገደል ሠፈሩ፤ ወድትዋ የሴቶች መመክያ እቴጌ ጣይቱ ግን በትግሮችና በሰሜነኞች አሽከሮቻቸውና በእውቀታቸው ብዛት ዘው አስጭነው ኢትዮጵያን አስገዙዋቸው።" ገጽ 36
እንግዲህ ተከታዪ አንባቢዎች እንዳይደናገሩ ወይም ግልጥ ለማድረግ መጸሐፉን እየጠቃቀስን ገጽ 49 አካባቢ ደርሰናል። ነገሩ ነው እንጂ መጸሐፉ መርጦ ለመጥቀስም አያመችም ምክንያቱም እያንዳንዷ ዓረፍተነገር ብርቕ ታሪክን ከዝናለችና፣ ቢሆንም ይዘቱን በከፊልም ቢሆን መካፈሉን እንቀጥላለን። መጨረሻ የደረስንበት ክፍል እዚህ ነው! መልካም ንባብ።
Meleket wrote:
11 Jun 2019, 03:32
እኒህ ቆፍጣና አርበኛ፡ ኤርትራ ተመልሰው በዳሎል የፖታሽ ሥራቸው ያጋጠማቸውን ሁኔታ፡ የዓዲ አቡኑ ሰላይ የተስፋሁነኝ ሸፍጥ፣ በወቅቱ ከፖታስ ይገኝ የነበረውን ትርፍ በኣኃዝ አስደግፈው ይተነትናሉ፣ አያይዘውም በኢትዮጵያ መንግሥት ስም ያለልክ እጅግ ከፍ ባለው ዋጋ ከፈረንሣይ ሀገር አጭር ውጅግራ ጠበንጃ የገዙ ደጃዝማች ጌታቸው አባተ በምጽዋዕ ስላጋጠማችወ ጉዳይ ተንትነው ጨው እንዴት እንደሚመረትም ሂደቱን ገልጸው የፋብሪካውንም ዲዛይን ማን እንደነደፈው ሳይቀር ዘርዝረው ይገልጹልናል። ከገለጡ አይቀር እንዲ አርጎ እውነቱን ቁልጭ አድርጎ መግለጥ ነው እንጂ! በርግጥ እንዲህ አድርገው እውነታን የሚገልጹ ኤርትራውያን አባቶች እና ቅድመ አያቶች መኖራቸው ያኮራናል! :lol: ይህን ጽሑፍና ትንታኔ እጅግ ብርቅ የሚያደርገው ዋነኛ ምክንያት፣ አሁን ያለው ትውልድ ገሚሱ ገና ሳይወለድ፣ ገሚሱም ገና ባንቀልባ ላይ ታዝሎ እያለ የነበረን ሁኔታን ፍንትው አድርጎ መግለጡ ነው!!! መልካም ንባብ። :mrgreen:

ባባቴ ቤት በሀገሬ በሠገነይቲ አንድ ወር ስቀመጥ ከዘመዶቼ ብዙ ስልቻ ማር ስጦታ መጣልኝ፤ በዚያም ፲፱፻፲ ዓ.ም. ወሰን የሌለው ማር ከየ ጫካውና ከየ ቤቱም ሲቆረጥ በብዙ አስደነቀ፤ ዘመኑም የቅቤ ፣ የእህል፣ የማር ዘበን ተባለ። ስለዚሁ መልካም ዘበን ሰው ሁሉ በፍቅር ተሳስሮ ተስማማ፤ መሬቲቱም ፍሬዋን ሰጠች፤ እኔም ያለ ኅሳብና ያለወጭ ገንዘብ ባባቴ ቤት ቶይቼ አሥመራ የገባሁኝ ቀን የተማሪ ቤት ጓደኛዬ አቶ ወልደማርያም ተወልደን አገኘሁና በብዙ ደስታ ተቀብሎ ጋበዘኝ። በዚሁም ግብጃ መካከል “እኔ መርሳ ፋጢማ ኤረሰለ የደሎል ፖታሳ ሥራ እሔዳለሁና መቃድሾ ከመመለስ ይልቅ በዋናው መሥሪያ ቤታችን የኔው የጸሐፊነቱ ቦታ አለና ነገ ጡዋትና” አለኝ። እኔም አባቴ መቃድሾ መመለሴን ስላልፈቀዱ ደስ ለማሰኘታቸው ብዬ ኅሳቡን ተቀበልሁት።” ገጽ 42

በማግሥቱም የፖታሳ(ማዕድን) ኩባንያ ዲረክሲዩ ወደ ኮመንዳቶረ ጆቫኒ ደል ኮርሶ ፊት በቅጽበት አቶ ወልደማርያም አቀረበኝ፤ ወዲያውም ጆቫኒ ደል ኮርሶ በመኪና ጽሕፈት ፈተና አደረገልኝና ስለወጣሁ ዕለቱን በ፻ ሊሬ የወር ደመወዝ ቆርጦ ስለተቀበለኝ። እኔም በመቃድሾ እማገኘው ደመወዝ ብልጫው ትንሽ ስለሆነ በሀገሬ መቅረቴን ፈቀድሁና በአሥመራ ቀረሁ። አቶ ወልደማርያም ሥራዉን አስረካክቦኝ ሔደና ከኮመንዳቶረ ጆቫኒ ደል ኮርሶ ጋር በደስታና ስምምነት ሥሠራ ሳለሁ፤ አንድ በኩራት የተሞላ፣ ክርስትያኖቹን የጠላ፣ በየሰዓቱ ልብሱን የሚለውጥ ጋንተስ የተባለ ግምጃ ቤት በክፉ ዓይን ተመለከተኝ፤ እኔም እኔን የሚጠላበትን ምክንያት ስላላወቅሁት በብዙ ደነቀኝ። ይህም ያለ ልክ በኩራት የተሞላው ከንቱ የሆነው ዮሴፍ ጋንተስ የግምጃ ቤቱን ሒሳብ አማትቶ ፴፭ሺህ ሊሬ አጥፍቶ በስንብት ወደ ጣሊያን ሀገር ተነስቶ ሔደ። ደል ኮርሶም ገቢን ወጭውን፣ በባንክ ያለውንም ገንዘብ ሲያመዛዝን ሳለ ፴፭ሺህ ሊሬ ጉድለት ስለተገኘበት አታላው ጋንተስ ናፓሊ እንደደረሰ ታሥሮ አሥመራ እንዲመለስ አስቀድሞ በቴሌግራም አስታውቆ አሥመጣው።” ገጽ 43

“የሠገነይቲ አቶ ወልደ ማርያም ተወልደ ጤና ስላጣ ወደ የኔው ሥራ አሥመራ ሲመጣ እኔም በሱ ሥራ የ፻፶፭ ሊሬ ደመወዝ ወደ እሳታዊው ፋጢማ ኤረ ተዛውሬ እንድሠራ ከደል ኮርሶ ታዝዤ ሔድሁ። ገና በዚህ ሀገር ስገባ የዓጋሜው ወጣት ፊታውራሪ ለበን ስብሐት መጡና ሰንብተው ሲሔዱ ፊታውራሪ ተድላ የሚባሉትም ሹም ከዓጋሜ በአሥመራ መንገድ መጡ። እንደመጡም ፈልገው ተገናኙኝና ስለ ፓታሳም ፈጥነው ጠየቁኝ፤ እኔም አላውቅም ስል መለስኩላቸው። በማግሥቱ እሁድ ቀን ነበርና ለማየታቸው ባረፉበት ቦታ ስሔድ ፊታውራሪ ተድላ በደስታ ፈጥነው ተቀበሉኝና ወዲያው ቁጭ ብለን ስንነጋገር “ባክዎ ይህንን የደሎል ማዕድን ወዴት ነው የሚወስዱት? ምንስ ጥቅም ያገኙበታል? ይንገሩኝ” ብለው አጥብቀው ጠየቁኝ። እኔም ጥያቄአቸው ደስ ስላለኝ “ከፍ ያለ ብዙ ጥቅም ባያገኙበት በከንቱ የሀገራችንን አፈር እየቆፈሩ የባቡር መንገድ እስከ ባህር ዘርግተው ባላጓዙት ነበር። የኢትዮጵያ መንግሥት እውቀት ቢኖረው ከባለ ብዙ ጥበብ እንደ ጀርመን መንግሥት ከመሰለው ጋር ውል ተዋውሎ ቢያሠራው ኑሮ ብዙ ጥቅም ባገኘበት ነበር”። ገጽ 43

“የዚሁም ኢትዮጵያው ደሎል አንድ ኩንታል አፈር፣ በአደን ፮፻ በኤውሮጳ ሺህ ፸ በአመሪካ ፪ ሺህ ሊሬ ይሸጣል፤ ባሩድ ይሠሩበታል፤ መድኃኒት ይቀምሙበታል፤ ጥቅማቸውም ወሰን የለውም ብዬ” ስላቸው ተከትሎዋቸው ከመጡት ከ፰ቱ ልብስ ከሌላቸው አሽከሮቻቸው ውስጥ የዓዲ አቡን ተስፋሁነኝ ከዚህ በላይ የተጻፈውን ቃል በቅጽበት ለቢያንኪ ነገረውና ፷ ብር ዋጋ ተቀበለብኝ። ለዚሁ ሥራ ዋና ሹም የሆነው ቢያንኪም “ተስፋሚካኤል ትኩእ የተባለው ጸሐፊ የተሰወረ የኢትዮጵያ መንግሥት ቈንስል ሆኖ ሲሠራ ስለተገኘ በፖሊስ ጥበቃ ወደ አሥመራ ልከነዋልና በቀጥታ ወደ አሰብ እሥር ቤት ተልኮ እንዲታሰር” ብሎ ለኮመንዳቶረ ጆቫኒ ደልኮርሶ በቀጥታ ጻፈለት። ለኔ” ወደ አሥመራ እንድትወጣ” አለኝ። “አልወጣም የደል ኮርሶ ትእዛዝ ካልደረሰኝ” ብዬ ፫ት ቀን በቤቴ ተቀምጨ ሳወጣ ሳወርድ ሰነብትሁና ወደ የኢትዮጵያዉን አፍቃሪ የሆነው የመድፈኞች ሻምበል የጨዋ ልጅ አምፕሪሮሪ በአሥመራ መሥያ ቤት ስለማውቀው እሱ ዘንድ ኼጄ “የላከኝ ደል ኮርሶ ነው፤ ያለ የደል ኮርሶ ትእዛዝም ቢያንኩ ወደ አሥመራ እንድትወጣ ብሎ አለኝ፤ እኔም የላከኝ ኮመንዳቶረ ደል ኮርሶ ስለሆነ ያለ የሱ ፌርማ አልሔድም አልሁት፤ ነገሩስ ምን ይመስልሃል” አልሁት። እምፐራቶሪም በብያንክ መጥፎ የስለላ መሠለልን ሥራ አዘነ፤ ነገሩንም ስለፈራ “ዝም ብለህ መሔድ ይሻላል” እያለ ካጽናናኝ በኋላ ለአሽከሩ፣ ቢያንኪ ተንኮል እንደሠራብኝ ነግሮት ኑሮ ተከተለኝ እና ዳርዳሩን ነገረኝ። እኔም ከመርሶ ፋቲማ ኤረ ወደ ዓጋሜ ለመውጣት አሰብሁ፤ ዳሩ ግን ዓጋሜ ሳልደርስ በወኃ ጥም ብሞት ወይም በመንገድ በማላውቀው ሀገር ሞያ ሳልሠራ በከንቱ ብያዝ፣ ለአባቴና ለዘመዶቼ ከማስወረሴ በላይ ማሳዘኔን አሰብሁና ወደ አሥመራ ወጥቼ የሚመጣብኝን አሥራትና መከራ መቀበል ይቻላል ብዬ ወደ ሠፈሬ ተመለስሁና ሻንጣየን አሸክሜ ወደ ጀልባይቱ ገባሁ።” ገጽ 43

" በዚህ ጊዜ እኔን የሚጠብቁ ሁለት ፖሊሶች በፍጥነት መጡና በቀኝና በግራ ሆነው ተሣፈሩ። . . . ምጽዋዕም እንደ ደረስን አንደኛው ቀረና ሁለተኛው ከኔ ጋር ከምፅዋዕ አሥመራ ድረስ ወጣ። እኔም በቀጥታ ወደ መሥሪያ ቤት ወደ ደጕ ኮመንዳቶሪ ጆቫኒ ደል ኮርሶ ዘንድ ኸጄ “አንተ ለሥራ ላከኝ፤ ግፈኛው ቢያንኪ ግን በፈቃዱ መለሰኝ፤ ምክንያቱስ ምንድር ነው” ብለው፣ እኔ ላኩህ እኔም አሥጠራሁህ፤ የሚያናግርህ ጉዳይ የለምና ፭ት ቀን አርፈህ ና” አለኝና ቢያንኪንና ለ፷ ብር የሸጠኝን ተስፋ ሁነኝን በፍጥነት በሥልክ ተጠሩና አሥመራ መጡ።" ገጽ 44

"ደል ኮርሶም በቁጣ ቃል ለቢያንኪና ለተስፋ ሁነኝ “አንተ አለ አገባብ የሰጠሀው ፷ ብር፣ አንተም በሐሰት የተቀበልካትን ለ፷ ብር መልሱ” ብሎ አስጨንቆ ሁለቱንም ያዛቸው። “የተሰወረ የኢትዮጵያ መንግሥት ቈንስል ሆኖ ተስፋሚካኤል ትኩእ ፖለቲካ ሲሠራ ስላገኘው ለተስፋሁነኝ የሰጠሁትን ፷ ብር ስለምን እከፍላለሁ? ተስፋሚካኤል ትኩእስ ይህን ያህል ከፍ ያለው ጉዳት በጣሊያን መንግሥት ላይ የሠራውን ሣይታሠር እንዴት ይቀራል” ብሎ መለሰ። “ተስፋሚካኤል ትኩእ ለክቡር ራስ ሥዩም መንገሻ ዮሐንስ ለልጃቸው ለደጃዝማች ካሣ ስዩም፣ ለደጃዝማች ተካም ጋር ደብዳቤዎች ስንጻጻፍ ሳስተረጕመው ተስፋሚካኤል ትኩእ ምንጊዜም ምስጢር ውጭ አውጥቶብኝ አያውቅም ነበር። እኔ መርጨ ያመጣኹትን ሥራተኛ አለማመንህ እሱን አይደለም እኔን ነው፤ ተስፋሚካኤልም አንተ እንደምትለው ክስ ዓይነት ዓይሠራም ቢሠራም እኛን የሚያገባን ጉዳይ ዓይደለም። ይህም ወጣት ልጅ በዚሁ ፖለቲካ አሰብ እሥር ቤት ቢታሠር እኛ ምን እንጠቀምበታል፤ አንተም በማያገባህ ሥራ አትግባ! የፖለቲካ ሠራተኛ ዓይደለህምና ተጠንቀቅ” ብሎ ደልኮርሶ በቁጣ በቢያንኪ ላይ በይፋ ተቆጣውና ተንቀጠቀጠ፤ በፍራትም ያለልክ ተሸበረ።" ገጽ 45

"ኮመንዳቶሪ ጆቫኒ ሰል ኮርሶም “ተስፋሁነኝ የሚባል ዘበኛ እኛንና እናንተን የሚያጣላን መጥፎ ሰው ስለሆነ ከደሎል ሥራ እንዲወገድ፣ ወደ ኤርትራም ኣንዳይመለስ እንድታደርጉልን አጥብቀን ለክቡርነትዎ እንለምናለን” የሚል ደብዳቤ ለክቡር ራስ ሥዩምና ለደጃዝማች ካሣ ጻፈና እጁንም በኤርትራ መንግሥት በኩል ወደ ዓድዋ ተልኮ በደጃዝማች ካሣ ዘንድ ውርደትና አለንጋም ተቀበለ። ተስፋሁነኝ ፷ብር እበላለሁ ሲል ተበላ፤ ተዋረደ። እግዚአብሔር ግን በሰፊ ቅን ትክክለኛው ፍርዱ ከቢያንኪና ተስፋሁነኝ ሰብቅና እሥራት ሰውሮ ስላተረፈኝ አመሰገንሁት፤ አመሰግነዋለሁም።" ገጽ 46

"ለኢትዮጵያ ሕዝብ እማኝና ጠበቃም የሆነው መልካሙ ደል ኮርሶ ይህን ጭቅጭቅ ከፈጸመ በኋላ እኔን ጠራኝ እና “የምጽዋዕ የጨው መስሪያ ቤት አለቃው እኔ ስለሆንኩ ለዛሬ በ፻፷ ሊሬ ለወደፊቱም ደመወዝ እንዲጨመርለት፣ ቤትም እንዲሠጠው” ብሎ ጽፎ ላከኝ፤ በጥር ወር ፲፱፻፲፱ ዓ.ም. በጸሐፊነት ፪፻ ሊሬ ደመወዝ ስሠራ ሳለሁ፣ በየቀኑ የሚመጡትን የእንግሊዝ መርከቦች የሚጭኑትን ጨው ዋጋ በወርቅ ለውጥ ብዙ ሚሊዮን የወር ገቢ ነበራቸው፤ የጨው ሀብትና ሥራም የምጽዋዕን የመሰለ የተከናወነ ሥራ በዓለም ዓይገኝም። የምጽዋዕ ጨውና ዓሳም ጣፋጭነቱና ማማሩም ልዩ በመሆኑ በብዙ ተመስግነዋል። ገጽ 46

በኢትዮጵያ መንግሥት ስም ያለልክ እጅግ ከፍ ባለው ዋጋ ከፈረንሣይ ሀገር አጭር ውጅግራ ጠበንጃ የገዙ ደጃዝማች ጌታቸው አባተ ከነጓደኞቻቸው ምጽዋዕ ወረዱና በታሪኩ የታወቀውን የግራርን ጨው አመጣጥና ካንድ ሽህ የበለጠውን ሠራተኛ ሲሠራ፣ ጨው ትልቅ ወሰን የሌለው ክምር ሲከመር፣ ከተከመረበትም በምድር ባቡር ተሞልቶ ወደ ባህር ዳር ባለው መጋዜን ውስጥ ገብቶ ሲያፈሰው፣ ከዚያም ጥበባዊው የእውቀት ሥራ ሽቅብ አውጥቶ ወደ ወፍጮ ራሱ እየወረወረ ፈጭቶ መልሶም ወደሌላው መጋዜን ያገባዋል፣ ከዚሁም መጋዜን አንስቶም ወደ ባህር ውስጥ ያሉትን መርከቦች በፍጥነት ሲሞላ በማየታቸው፤ የኢትዮጵያ መላክተኞች ይቅርና ሞላው የዓለም ሕዝብ አደነቀው፤ አመሰገነውም።" ገጽ 46

“በዚሁ ጊዜ የመንግሥት የምጽዋዕ ጕምሩክ ሹሞች የሆኑት በትምህርታቸውና በእውቀታቸው ከፍ ያሉት ግራዝማች ተድላ ጋብርና ፊተውራሪ ዘወልደማርያም ዘገርጊስ፣ ብላት ዘርኤ ግርሙ ዘጠና ሊሬ ደመወዝ ለየ አንዳንዳቸው ሲሠሩ እኔ “፪፻፶ ሊሬ ካልተሠጠኝ በ፪፻ ሊሬ ደመወዝ ምንም አልሠራም” ብየ በ፮ ወር ወደ አሥመራ እምቢ ብዬ ሥወጣ በማየታቸው በብዙ ተደነቁ። “የተስፋሚካኤል ትኩእ ዕድል ድንጋይ የሚፈልጥ ዕድል ነው” ሲሉ መሰከሩ።" ገጽ 46

"ይህንኑ የምጽዋዕን ጥበባዊ የጨው ፋብሪካ ሥራ የሠራ ዓይምነ የሚባል አዋቂ መሐንዲስ ብዙ ምስጋና ከኤርትራዊያን ይገባዋል።" ገጽ 46

አርበኛው ከምፅዋዕ አሥመራ ተቀይረው ስራ እንደጀመሩ፣ ኤርትራ ዉስጥም ድርቅ እንደገባ፣ እሳቸውም ከአስመራ ሞቃዲሾ በጂቡቲ በኩል እንደተመለሱ፣ ጂቡቲ ላይም ልጅ በየነ ህብትዝጊን እንዳገኙ፣ ኃይለሥላሴም ልጅ በየነን በአ/አ ስራ ሊቀጥሯቸው እንዳሰቡ፣ ልጅ በየነ ግን ወደ ሮማ መመለስና ቀጥሎም የትሪፓሊ የእርሻ ዋና ዲራክተ ሆኖ ከእንደነበር ይገልጻሉ። መብራህቱ (ሎሬንሶ) ታእዛዝም በአደን ሥራ እንደጀመረና የኢትዮጵያን አልጋወራሽ በብዙ ዓይነት ፓለቲካ እንደረዳቸው፣ በኤደን እንዳገኛቸው፣ አ/አ መጥቶ ሥራ እንዲዝ ቢጠይቁት ፈረንሣይ ሄዶ መማር እንደሚሻ እንደገለጠላቸው፣ እሳቸውም እንደፈቀዱት፣ እሱም ፓሪስ ሂዶ በየዓመቱ አንደኛ እየሆነ በሕግ ሊቅነት ምስክር እንደተቀበለ ይገልጻሉ

መቃድሾ ከተመለሱ በኋላ ያጋጠማቸውን ሁሉ በሶማልያ የነበሩ ኤርትራዉያን ለኢትዮጵያ መንግሥት በመስራታቸው ያጋጠማቸውን እንግልትና ሞትም ስም እየጠቀሱ እንዲሁም ስለ ልጅ ኢያሱ በቀጥዩ ክፍል ይዘከዝኩልናል! ይህ ሁሉ ደግሞ ያሁኑ ትውልድ ማለትም አዳሜ ገና ሳይወለድ በአንቀልባም እንኳ ገና ሳይታዘል የተፈጸመ ነው!!! :mrgreen:

Re: ተስፋሚካኤል ትኩእ (1892 – 1964)] - ወለዶና ክነቦ ዝግባእ መኽዘን ታሪኽ

Posted: 11 Jun 2019, 11:33
by Degnet
Meleket wrote:
06 Jun 2019, 10:02
ናይ ኑረነቢ ማህደር ዚብል ርእስ ዘለዎ ታሪክ ዝኸዘነት መጸሐፍ መሳጢ ብዝዀነ አገባብ ብቋንቋ አምሓርኛን ትግርኛን ብ2017 ተጻሒፉስ ነቢብና አሎና። ዓሰርተ ዓመታት አቐዲሙ፡ ብኣርታኢ ደረጄ ገብሬ ብ2006 ናይ ኣርትዖት ስራሕ ዝተገብረላ “ሀገሬ የህይወቴ ጥሪ” ዚብል ርእስ ዘለዋ መጸሓፍ ናይ ሓደ አቶ ተስፋሚካኤል ትኩእ ዝተባህለ ብመንነቱ ሕቡን ኤርትራዊ ተጋዳላይ ንናጽነትን ሓርነትን፣ ንመግዛእቲ ጥልያን ንምስዓር ብብረት ጥራሕ ዘይዀነ በተሓሳስባን ብብርዒን ዝተቓለሰ ኣቦ “ግለ ታሪክ” ብቋንቋ አምሓርኛ ተጻሒፋስ ነቢብናያ። ሓርበኛ አቶ ተስፋሚካኤል ትኹእ ንዝነበሩሉ ዘመን ብግቡእ መርሚሮምን ተንቲኖምን፡ ንእከይ አተሓሳስባታት እቱይ ዘመን፣ ንሽጣራታት ጥልያንን ኃይለሥላሴን እንግሊዝን ብዉህልነት ዝመልኦ ልቦናን ፖለቲካዊ ብስለትን ዝተንተኑ፣ ኣብ መንጎ ደቂ ኢጦብያ ንዝነበረ ሕድሕዳዊ ምጉርፋጥን ሳዕቤናቱን፡ ኣብ ሞንጎ መራሕቲ ጦብያ ዝነበረ ናይ ስልጣን ሕርፋንን ርኡይ አድልዎታትን ብጭብጢ ብምምጓትን ብምትንታንን፡ ንዝኣመኑሉ ኩሉ ብዘይቀለዓለም ብምትግባር፡ ድንቂ ብዝዀነ ግሉጽነትን ምቕሉል አገባብን ውልቃዊ ታሪኾም “ግለ ታሪኾም” ጽሒፍምልና፡ ንስለ ትግሃቶምን ተወፋይነቶምን ነመስግኖም አሎና። እዞም ሓርበይናዊ ምቕሉል ኣቦ ኣብ ሃገሮም አብ ኤርትራ፣ አብ ዓዲ ጥልያን፣ አብ ሊቢያ፣ አብ ሶማል፣ አብ ሱዳን፣ ኣብ ኢትዮጵያዉን ወዘተ ብጅግንነትን ነቱይ ዝኣመኑሉ መትከል አብ ግብሪ ንምትግባር ዝተቃለስዎ ኩሉ ታሪኾም ብ፲፱፻፵፰ (1948 ኣቆጻጽራ ግእዝ) ጽሒፎም ገዲፎምልናስ ደቆም ብ2006 ንሓንቲ ካብተን 9 መጻሕፍቶም አሕቲመን ንነበብቲ ቀሪበንኣ ኣለዋ። እንተክኢልኩም ሃሰስ ኢልኩም ደሊኹም ንበብዎ። ቅድሚ ሚእቲ ዓመታት ብስለትን ፖለቲካዊ ንቕሓት ኤርትራዉያን አቦታት ማዕረ ክንደይ ልዑል ምንባሩ ክትግንዘቡ ኢኹም።

ገሊኦም ንፉዓት፡ ንትሕዝቶ እዙይ መጸሓፍ ናብ ትግርኛ ክሳብ ዝትርጉምዎ እቶም አምሓርይና ዝርድኣኹም ኣሕዋትን ኣሓትን ቅድሚ 100 ዓመታት ዝነበረ ታሪክን ፖለቲካዊ ሃዋህው ከባቢና ክትፈልጡ እንተደኣ ደሊኹም አብዙይ አለኹም ብዘይቃል ዓለም ዝተጻሕፈ ታሪኽ!!! ነዙይ መጽሐፍ አብ ሕትመት ንዘብቕዓ ደቆም ድማ ነመስግን። ንፉዓት ቢልናዉን ነተን ተሪፈን ዘለዋ ጽሑፋቶምዉን ከሕትማ እሞ ብፍልጠቶምን ብስለቶምን ጥበቦምን ትብዓቶምን “ርእሰ መዃንንት” ናይዝዀኑ ናይ ክቡር አቦና ኣቶ ተስፋሚካኤል ትኹእ ፍልጠትን ልቦናን ጥበብን ትብዓትን ክንካፈል ክተክእሉና ንላቦ።


http://www.mereb.shop/rs/?prodet=true&p ... 283&vid=88



ታሪኽ እሞ ድማ ብኤርትራዉያን ቀዳሞት ኣቦታት ዝተጻሕፈ ታሪኽ ኽንነብቦ ይግባእ እቱይ ምንታይ ንፍተዎ አይንፍተዎ ኣካል ታሪኽናን ታሪኽ ኅብረተሰብናን ስለዝዀነ!ብርግጽ ንታሪኽ እዞም እሙንን መትከላዊን ኣቦ ግን ክንፈትዎ ኢና፣ ብዙሕ ድማ ክንመሃረሉ ኢና! ምስ ነበብናዮን ምስ ኣዀማሳዕናዮን! :mrgreen:
Neweshteysi fewsi koynuni,I have seen some of the people in my life.

Re: ተስፋሚካኤል ትኩእ (1892 – 1964)] - ወለዶና ክነቦ ዝግባእ መኽዘን ታሪኽ

Posted: 12 Jun 2019, 04:48
by Meleket
እኒህ ኩሩ የነጻነት አርበኛ ተስፋሚካኤል ትኩእ ለዛሬ ኤርትራዉያን በሱማሌ ውስጥ ሆነው በምስጢር ኢትዮጵያን በማገዛቸው ስላጋጠማቸው ድርብ ገድል ይገልጡልናል። “የትግሬው የረቀቀ የዲፕሎማሲ ጥበብ” ያሉትን የደጃዝማች ገብረሥላሴ ባርያጋብርን የመከፋፈል ስልትም ይገልጹልናል፣ የልጅ ኢያሱን ድንቅ አባባሎችና፣ የእንግሊዝ መንግስት ስጋትን ቁልጭ አድርገው ይተርኩልናል። ኢትዮጵያ አንዳንድ የድንበር ባላባቶቿ በውጭ ኃይሎች ሲደመሰሱ “ነግ በኔ አለማለቷ” እጅግ እንዳሳዘናቸው ይተርኩልናል፣ ብልህ የተባሉት የጦር ሚኒስተር ፊታውራሪ ሀብተጊዮርጊስ “ለዜጎቻቸው የነበራቸውን ልዑል አክብሮትም" ይገልጹልናል። የጣልያን መንግሥትም ኢትዮጵያን ሊወር እንደሚችል አስቀድመው ማወቃቸውንም አልሸሸጉንም። መልካም ንባብ። :lol:

“በሰላም መቃድሾ ገባሁ፤ የመቃድሾም መንግሥት ለኤርትራ ጸሐፊዎችና አነጋጋሪዎች ካንዱ ደረጃ ወደ ሁለተኛው ደረጃ እንዲተላለፉ ልዩ ደንብ ወስኖ በአዋጅ አቁሞ ስለነበርና እኔም በሕመምና በመርከብም ችግር አሥመራ የቆየሁበትን ፮ወር ደመወዝ ፭፻፷፬ ሩቢያ በ፮ ሊሬ ከ፶ ሣንቲም ሂሳብ ፫ ሺህ ፮፻፷፮ ሊሬ ዕለቱን ተቀብየ ፫ሺህ ባንክ በማስቀመጤ ሰው ሁሉ ቀናብኝ። . . . የትርፍ ሰዓት ሥራም በየወሩ ፳፭ ሩቢያ ለቀለቤ ስለማገኝ ፻፪ ሩቢያ ያለማቋረጥ በየወሩ ፯፻፷፭ ሊሬ ባንክ ሳስቀምጥ እንኳንስ ጓደኞቼ ፈረንጆች አላመኑም” ገጽ 50

“ልክ ባመቱም ወደ ፩ኛ ማዕረግ ወደ ፻፴፪ ሩቢያ ወጣሁና ፳፮ ሩቢያ የሰዓት ኣላፊ በድምሩ የ፶፰ ሩቢያ፣ ያንዱም ሩቢያ ለውጥ ከ፱ ሊሬ በላይ ሲሆን ፩ሺ ፬፻፳፪ ሊሬ ደመወዝ የኤርትራ ጸሐፊዎችና አነጋጋሪዎች ስንቀበል ጣሊያኖች ራሳቸውና ሶማሎችም “በደመወዝ በለጡን፣ እኩል አድርጉን” ብለው አመለከቱ። ዳሩ ግን በአዋጅ ለኤርትራዊያን ብቻ የወጣውን ደንብ ለማፍረስ ስላስቸገራቸውና ያለ ኤርትራዊያንም ሥራ ለሠሩ ባለመቻላቸው ስለተረዱት ካንድ ጣሊያን አብልጠውም ቢይዙን ተደስተን ስላላደርን የጣሊያን ኢትዮጵያን የመውረር ኅሳብ በመረዳታችን በየ በኩላችን ወደ ኢትዮጵያ መዞርና መርዳት፣ መጻጻፍም አዘወተርን። በየመንገዱና በአዲስ አበባም ደርሰው፣ በነገ እሽ ነገ ተቃጥለውና በኅሳብ ተከበው፣ የመጡበትን የጀግናነት ኅሳብ ሳይፈጽም፣ ተስፋ ቆርጠው የሞቱ ኤርትራዊያን ቁጥር የላቸው።” ገጽ 50

ልጅ ገብርኤል ኤድሞንዶ ከመቃድሾ ለኢትዮጵያ መንግሥት ርዳታ የጣሊያን ሁናቴና ፖለቲካ የሚያስረዳ የምስጢር ራፓር ቢልክ በዚያን ጊዜ የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ የነበረ ወደ ጣሊያን መንግሥት አስተላልፎት በ፲፱፻፳፰ ዓ.ም. በመቃድሾ ተይዞ ወሰን የሌላው እሥራትና ስቃይ አልሰቀዩትምን? የሞት ፍርድ አልፈረዱበትምን? ፲፪ ጓደኞቹም የጠበቀ እሥራት ሲታሠሩ፣ በዚሁ እሥር ምክንያት መዝገበ መኩንን አልሞተምን? የተቀሩት ኤርትራዊያን ታሥረው ከመቃድሾ ወደ አሥመራ በግዴታ አልተወሰዱዋቸውምን? እንደዚሁም በሕግ ወጥ በሆነው እሥራትና ስቃይ ተሰቀይቶ አቶ ተክለ አጐስቲኖ አልሞተምን?" ገጽ 51

“ይህ ሁሉ የኤርትራዊያን የሀገር ፍቅርና ታሪካዊ ባለ ዋጋ ሥራ የኢትዮጵያ መንግሥት በሚያዝያ ፳፯ ቀን ፲፱፻፴፫ ዓ.ም. እንደተመለሰ እነዚህ ባለውለታ ሰዎች ወለታቸውን ተቀብለዋልን?" ገጽ 51

“ወደ ሥር ነገራችን ተመልሰን እንግባ። እኔም ምንም እንኳንና መቃድሾ ከመግባቴ በቅጽበት ከደረጃ ወደ ደረጃ የመተላለፍ መልካም ዕድል ቢገጥመኝም የልብ ደስታና እረፍት ምንም አልነበረኝም። ስለምን? የጣሊያን የጠላት መንግሥት ኢትዮጵያን ለመውረር ያለውን የጋለ ብዙ ምኞት መመኘቱን በመረዳቴ፣ መንፈሴ ታውኮ የልብ እረፍት በማጣቴ ስቃይ ተሰቃይቼ ነበር። ጣሊያኖቹም የተጨበጠ ኃጢያት አግኝተው ለማሠር በብዙ ንቃትና ትጋት ቢከታተሉኝም በእጃቸው ባለ መውደቄ አምላኬን አመሰገንሁ፤ አመሰግናለሁም።” ገጽ 51

“በ፲፱፻፲ ዓ.ም. የኢትዮጵያ መንግሥት አልጋ ወራሽ ልዑል ልጅ ኢያሱ ሚካኤል ከሰገሌ ጦርነት በኋላ ሐውሣ ወርደው ስለ ነበሩ የእንግሊዝ ብርቱ መንግሥት መልእክተኛ ካሉበት ሐውሣ በረሐ ወርዶ እንዲህ አላቸው።” የጀርመን መንግሥት ቄሣር በኤውሮጳና በአመሪካ መንግሥታት ላይ ጦርነት ስላነሳብን ፈቃድዎ ሆኖ ኢትዮጵያም የኛ የቃል ኪዳን ጓደኛችን ከሆኑና መሆንዎንም ከፈረሙልን እንደገና መልሰን ወደ አልጋ እንመልሰዎት አለን” ብሎ ቢላቸው። “አልጋን የያዘ ወንድሜ ተፈሪ ነው፤ እኔም የኢትዮጵያን ሕዝብ ደም በከንቱ ለማፍሰስ የናንተ የጦርነት ጓደኛ ለመሆን አልፈቅድም” ብለው ስላሉት በብዙ አዘነ። የልጅ ኢያሱም መልስ እጅግ አስደነቀ። ገጽ 51

የእንግሊዞቹም ስጋትና ፍራት እኛ ከጀርመን ጋር ስንዋጋ በኢትዮጵያና በአፍሪካ፣ በግብፅና በእስያ፣ በህንድም ዛሬ የለቀቁትን የቅኝ ሀገር ሁሉ ኢትዮጵያ ጦርነት ካስነሳችብን ሌሎቹም ሁሉ ያስለቅቁናል በማለት ተጨነቁ። በሰገሌ ጦርነት ለሐዲሱ የንግሥት ዘውዲቱ መንግሥት የረዳው፣ መልሶ ኢትዮጵያን እርስበርስዋ ለማፋጀት ድል ሆነው በሐውሣ በረሀ በተቀመጡበት ሔዶ በብዙ ማባባል ልጅ ኢያሱን መለመኑ ከመደምሰስ ጥፋት ለመዳን ያደረገወ የሰፊ እውቀት ዘዴ ነው። እውነትም በትልቁ የዓለም ጦርነት ጊዜ ኢትዮጵያ ጦርነት ብታነሳ በኤውሮጶች የተያዙባትን ሀገሮች ባስመለሰች ለህንድና ለግብፆችም የተስማማ የጋራቸው ጥቅም ቀረባቸው። ገጽ 52

“ልዑል ልጅ ኢያሱም ከሐውሣ ትግሬ ወደ ራስ ሥዩም መንገሻ ዮሐንስ ዘንድ መጥተው በስውር በክብር አስቀምጠዋቸው ሳሉ ፪ት ሰዎች ሸዋ መጥተው ልጅ ኢያሱ በራስ ሥዩም ሀገር መኖራቸውን ነገሩባቸውጣሊያንም ትግሬንና ሸዋን ለማዋጋት ሌት ተቀን ያለ ማቋረጥ ከፍ ያለውን ድካም ደከመ፤ ይህም የተሰወረ የራስ ሥዩምና የልጅ ኢያሱ ስምምነት በመንግሥት ዘንድ ስለታወቀ ልጅ ኢያሱ ማይጨው ሔደው በፈቃዳቸው እጃቸውን ለራስ ጉግሣ አርአያ በመስጠታቸው ለጣሊያንና ለእንግሊዝ ለፈረንሣይም መንግሥታት ኅዘን ከበባቸው ገጽ 52

“የኢትዮጵያ መንግሥት አልጋ ወራሽ ራስ ተፈሪ መኰንን ልጅ ኢያሱን በእጃቸው ለማግባት በአዋቂው ደጃዝማች ገብረሥላሴ በኩል ጥበባዊ የዲፕሎማሲ ረቂቅ ሥራ ለመስራት ቻሉ። ስለምን ደጃዝማች ገብረሥላሴ በሚኒስትርነታቸው ምክንያት ልጅ ኢያሱንም ወደ አልጋ እንዲመለሱ ስለማይፈቅዱ። ደጃዝማች ገብረሥላሴ ለራስ ሥዩምና ለራስ ጕግሣ ድፍን ትግሬ ተሰጥተዋታል የሚል የንግሥትና የአልጋ ወራሽ፣ የራሳቸውም ማህተም እየላኩ በኅሳብ ለያዩዋቸው እንጂ ራስ ጕግሣም ቢሆኑ እጃቸውን አሳልፈው አይሰጡም ነበር። ገጽ 52

“በዚህ ጊዜ ልዑል አልጋ ወራሽ ትግሬ ዘመቻ ዘምተው በጦርነት ልጅ ኢያሱን እጅ ለማድረግ አለመቻላቸው፣ ቢችሉም ራያና ወሎም አለማሳለፉን በመረዳታቸው ምክንያት መሳይ የሌለው ጭንቅ መጨነቅና ከፍ ያለውን ችግር ዙሪያቸውን ከበባቸው፤ ሸዋና ዳር ሀገር፣ ጎንደርና ጐጃምም ኅሳቡ ተከፋፈለ። ስለዚህ ጦራቸውን አስከትተው ልዑል አልጋ ወራሽ ተፈሪና የጦር ሚኒስተር ፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ ደሴ ሆነው በብዙ ስጋት ወደ ትግሬ ዘመቻ ለመዝመት ሲጠበቡ ሳለ በትግሬው ዲፕሎማሲ በደጃዝማች ገብረሥላሴ ባርያጋብር የረቀቀ ዘዴ ራስ ጕግሣ ከራስ ሥዩም ተለይተው የልጅ ኢያሱን እጅ ይዘው በመብረቃዊ ያልታሰበ ግስጋሴ ደሴ ገቡ። አልጋ ወራሽም ወሰን በሌለው ደስታ ከልጅ ኢያሱ ጋር አሽከሮቻቸውን አቆራኙመደሰታቸውንም በመድፍ ተኩስ ገለጹ። ገጽ 53

“በንግሥት ዘውዲቱ ትእዛዝ ልጅ ኢያሱ በራስ ካሣ ኃይሉ እጅ በኮላሽና በስላሴ እንዲታሠሩ ተደረገ። እነዚያ ኢትዮጵያን ለ፫ት መንግሥታት እንካፈላታለን ብለው ከንቱ በሆነው ተስፋ በተዋዋሉት ውል መሠረት ኢትዮጵያን ከመደምሰሳቸው በፊት በዙሪያዋ ያሉትን ባላባቶች ለመግደል ተስማሙባት። በበርበራና በሙጂርተን በወጋዴን ብዙ ጊዜ እንግሊዝ ድል ይመታ የነበረውን ሸክ መሐመድ አብደላ ሁሰን “ሙላህን” ለማጥፋት ስለተስማሙ የጣሊያን መንግሥት ከኤርትራ ፭ኛ በጦሌኒ በግስገሳ በዲናር አምጥቶ በመሐደይና በበልድ ወንዝ ሲያስከብበው እንግሊዝም ቁርሔይ ላይ በአረዩጵላን ቦምብ ደብድቦ ደመሰሰው። ከሞት የቀሩትም ልጆች ወደ የኢትዮጵያ መንግሥት ባሌ ገቡ። እንግሊዝም እጃቸውን ይዛችሁ ስጡኝ ብሎ በቁጣ ቃል ስለጠየቀ ብልሁ የጦር ሚኒስተር ፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ እምቢ ዜጎቼን አልሰጥም ብለው ከለከሉት የኬንያ ጠረፍ የሆነው ቦሮና በኢትዮጵያዊ ጦር ሠራዊት አለበሱት፤ አስከበሩት። እንግሊዝም አስፈራርቶ ዝም አለ። ገጽ 53

ስለዚህ ግፈኛው፣ የፈረንጅ ተንኮለኛው አገዛዝ፤ በመቃድሾ የምንኖር አነጋጋሪዎችና ጸሐፊዎች በሸክ መሐመድ ግፈኛው አገዳደል ምክንያት ኅዘን ማዘናችንም ከፈረንጆቹ የተሰወረ አልነበረም። ቀጥሎም በ፲፱፻፲፯ ዓ.ም. የመቃድሾ ሀገረ ገዥ ማርያ ደ በኪ በሙጂርተን ሶልጣን ኦስማን ማህሙድና በሱልጣን አሊ የሱፍ ላይ ጦርነት ሲያነሳ ኢትዮጵያ ነገ በኔ ብላ ርዳታ ሳትሰጣቸው ዝም በማለትዋ ይበልጥ ተናደድን፤ አለቀስን፤ አስረዳን። ሰሚ ግን አልተገኘም እኔም የልብ እረፍት አጣሁና ስንብት ጠይቄ ከመቃድሾ ወደ አሥመራ ወጣሁ። ወደ ሸዋ ኸጄ እንደ ሙሴ ኅሳብ ወገኔ ከሆነው ጀግና የኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር አብሬ ለመሞት ብዬ ነው እንጂ ከብዙ ጊዜ በፊት ኢትዮጵያ በጠላቶችዋ ተከባ መያዝዋን ተረድቸው ነበር። ገጽ 53

እኒህ ታሪከኛ ኤርትራዊ አርበኛ ከመቃድሾ ተመልሰው ወደ ኤርትራ ከዚያም ወዲ ኢትዮጵያ እንዴት እንደሄዱ እንዲህ ይተርኩታል፣ ከቄስ ገብረመድህን ወደ ሀገረ ገዢው ባሻይ ጎበና እንደተላለፉ፣ ባሻይ ጎበናም ዲል ባለ ድግስ እንደተቀበሏቸው እሳቸው ግን ከነመሳሪያቸውና ሽጉጣቸው ለጣሊያን ተላልፈው እንዳይሰጡ እንደሰጉ፣ የጣልያን ሰራዊት በነበረበት እምባ ስያስ በኩል ባብ ድሐን በተባለ መንደር እንደገቡ፣ ከዚያም በገለባ በኩል በአዲግራት አልፈው ስንቃጣ ከበረኛው ቤት እንዳደሩ፣ በረኛውም ከሽፍቶች እንዲጠነቀቁ እንደመከራቸው፣ ከትሪፓሊ የመጡ ፫ የወሎ ልጆች ከሽፍቶች ሲሸሹ እንዳጋጠሟቸው፣ ከነሱም ጋር ባንድላይ ከሽፍቶች እየተጠነቀቁ በበቅሎ መቀሌ እንደገቡ ይገልጻሉ። መቀሌ ደሴና አዲስኣበባ ምን ጠበቃቸው፣ ከጣሊያን ቈንስሎች ጋርስ ምን አይነት ሁኔታ አጋጠማቸው በቀጣይ ክፍል እንኮመኩማለን።

ይህን ታሪክ ብርቅ የሚያደርገው አሁን ያለው አዛውንት ትውልድ ንፍጡ ባፍንጫው ይዝረከረክበት በነበረ ወቅት ለነጻነቱ ሲል ብርቱ ገድልን ባከናወነ ኤርትራዊ አባት አርበኛ የዓይን እማኝነት የተጻፈ መሆኑ ነው።
:mrgreen:

Re: ተስፋሚካኤል ትኩእ (1892 – 1964)] - ወለዶና ክነቦ ዝግባእ መኽዘን ታሪኽ

Posted: 12 Jun 2019, 13:35
by Degnet
Meleket wrote:
11 Jun 2019, 11:06
Degnet wrote:
11 Jun 2019, 09:56
Meleket wrote:
08 Jun 2019, 06:03
በያንዳንዱ አንቀጽ ውስጥ ያለውን ረቂቅ መልእኽት ከቻላችሁ ፈልፍላችሁ አግኙት! ሰውየው የዋዛ አይመስሉም! :mrgreen:
...
Thank you a lot,I always wanted to know how and when dej.Abraha Araya died ,it is a historic book.I think I have said enough,I will go back to my reading now.
ደግነት ወንድሜ ግዜ ስታገኝ መጸሐፉን ከጫፍ እስከ ጫፍ ለማንበብ ሞክር፣ እኔ አለፍ አለፍ እያልኩ ስለሆነ ለማካፈል የሞከርኩት። አብርሃ አርአያ የሚል ስም እስካሁን ቢያንስ ቢያንስ ሁለት ጊዜ ተጠቅሰዋል፡
አንደኛው በገጽ 13 ልጅ አብርሃ አርአያ ተብሎ
Meleket wrote:
07 Jun 2019, 11:55

"አልጋ ፈላጊ ሆነው በአሳኦርታና በጠልጣል እያሉ በጽናት ሲቀመጡ የነበሩበትን የደጃዝማች ደበብ አራአያም የ፲፪ ዓመት ልጅ ወንድማቸው ልጅ አብርሃ አርአያን መያዣ ሰጥተው ፫፻ ወጨፎ ጠበንጃ ከነ ጥይቱ ከጣሊያን መቀበላቸውን ደጃዝማች ባህታን ለመግደል መሰናዳታቸውን ስለ ሰሙ የደጃዝማች ባህታም ከሀባብ ወደ ምፅዋዕ በመምጣት ለጣሊያን እጃቸውን ሰጡ።" ገጽ 13
ሁለተኛው በገጽ 36 ደጃዝማች አብርሃ አርአያ ተብለው
Meleket wrote:
08 Jun 2019, 06:03

"ደጃዝማች አብርሃ አርአያ ከዚያው ትምሕርታቸውና ወጣቱ ሰውነታችው፣ ወርቅ ከመሰለ ወደረኛ ከሌለው ቅላታቸው ጋር፣ ከኣኒያ እሳቶች የሆኑት የትግሬ አሽከሮቻቸው ሲሔዱ እንደመብረቅ፣ ዓይቻቸው ሳልጠግባቸው ከእውቀትና ከወንድነት ጋር ከፈ ያለ ድፍረትና ንቃትም ያላቸው ሰው ሆነው ታዩኝ። የልጅ ኢያሱ ወገን ነበሩና በሰገሌ ጊዜ ደጃዝማች አብርሃ አርአያና ደጃዝማች አመዴ ወሌ ብጡል ሁለቱ ትግሮች ባንድግዜ ሞቱ ማለትን ሰማን፤ በዚሁም ጊዜ አዲስ አበባ በጭቃ የተሞላች “ፊንፍኔ” የተባለች ዱርና ገደል ነበረች። ይህም ከተማ አጼ ምኒልክ በሌሉበት ከኣንጦጦ ፍልወኃ ለመታጠብ ወርደው ኮረብታይቱን ለከተማነት የመረጡዋት፣ የቆረቆሩዋት የሸዋን ቤተ መንግሥት በችሎታዊው ድፍረትና እውቀታቸው ብዛት ያቋቋሙት እቴጌ ጣይቱ ብጡል ናቸው። የሸዋ ንጉሥ ምኒልክ ግን ውራጌዎችንንና ኦሮሞዎችን ስለፈሩ ቆጥ በመሰለው የኣንቶቶ ገደል ሠፈሩ፤ ወድትዋ የሴቶች መመክያ እቴጌ ጣይቱ ግን በትግሮችና በሰሜነኞች አሽከሮቻቸውና በእውቀታቸው ብዛት ዘው አስጭነው ኢትዮጵያን አስገዙዋቸው።" ገጽ 36
እንግዲህ ተከታዪ አንባቢዎች እንዳይደናገሩ ወይም ግልጥ ለማድረግ መጸሐፉን እየጠቃቀስን ገጽ 49 አካባቢ ደርሰናል። ነገሩ ነው እንጂ መጸሐፉ መርጦ ለመጥቀስም አያመችም ምክንያቱም እያንዳንዷ ዓረፍተነገር ብርቕ ታሪክን ከዝናለችና፣ ቢሆንም ይዘቱን በከፊልም ቢሆን መካፈሉን እንቀጥላለን። መጨረሻ የደረስንበት ክፍል እዚህ ነው! መልካም ንባብ።
Meleket wrote:
11 Jun 2019, 03:32
እኒህ ቆፍጣና አርበኛ፡ ኤርትራ ተመልሰው በዳሎል የፖታሽ ሥራቸው ያጋጠማቸውን ሁኔታ፡ የዓዲ አቡኑ ሰላይ የተስፋሁነኝ ሸፍጥ፣ በወቅቱ ከፖታስ ይገኝ የነበረውን ትርፍ በኣኃዝ አስደግፈው ይተነትናሉ፣ አያይዘውም በኢትዮጵያ መንግሥት ስም ያለልክ እጅግ ከፍ ባለው ዋጋ ከፈረንሣይ ሀገር አጭር ውጅግራ ጠበንጃ የገዙ ደጃዝማች ጌታቸው አባተ በምጽዋዕ ስላጋጠማችወ ጉዳይ ተንትነው ጨው እንዴት እንደሚመረትም ሂደቱን ገልጸው የፋብሪካውንም ዲዛይን ማን እንደነደፈው ሳይቀር ዘርዝረው ይገልጹልናል። ከገለጡ አይቀር እንዲ አርጎ እውነቱን ቁልጭ አድርጎ መግለጥ ነው እንጂ! በርግጥ እንዲህ አድርገው እውነታን የሚገልጹ ኤርትራውያን አባቶች እና ቅድመ አያቶች መኖራቸው ያኮራናል! :lol: ይህን ጽሑፍና ትንታኔ እጅግ ብርቅ የሚያደርገው ዋነኛ ምክንያት፣ አሁን ያለው ትውልድ ገሚሱ ገና ሳይወለድ፣ ገሚሱም ገና ባንቀልባ ላይ ታዝሎ እያለ የነበረን ሁኔታን ፍንትው አድርጎ መግለጡ ነው!!! መልካም ንባብ። :mrgreen:

ባባቴ ቤት በሀገሬ በሠገነይቲ አንድ ወር ስቀመጥ ከዘመዶቼ ብዙ ስልቻ ማር ስጦታ መጣልኝ፤ በዚያም ፲፱፻፲ ዓ.ም. ወሰን የሌለው ማር ከየ ጫካውና ከየ ቤቱም ሲቆረጥ በብዙ አስደነቀ፤ ዘመኑም የቅቤ ፣ የእህል፣ የማር ዘበን ተባለ። ስለዚሁ መልካም ዘበን ሰው ሁሉ በፍቅር ተሳስሮ ተስማማ፤ መሬቲቱም ፍሬዋን ሰጠች፤ እኔም ያለ ኅሳብና ያለወጭ ገንዘብ ባባቴ ቤት ቶይቼ አሥመራ የገባሁኝ ቀን የተማሪ ቤት ጓደኛዬ አቶ ወልደማርያም ተወልደን አገኘሁና በብዙ ደስታ ተቀብሎ ጋበዘኝ። በዚሁም ግብጃ መካከል “እኔ መርሳ ፋጢማ ኤረሰለ የደሎል ፖታሳ ሥራ እሔዳለሁና መቃድሾ ከመመለስ ይልቅ በዋናው መሥሪያ ቤታችን የኔው የጸሐፊነቱ ቦታ አለና ነገ ጡዋትና” አለኝ። እኔም አባቴ መቃድሾ መመለሴን ስላልፈቀዱ ደስ ለማሰኘታቸው ብዬ ኅሳቡን ተቀበልሁት።” ገጽ 42

በማግሥቱም የፖታሳ(ማዕድን) ኩባንያ ዲረክሲዩ ወደ ኮመንዳቶረ ጆቫኒ ደል ኮርሶ ፊት በቅጽበት አቶ ወልደማርያም አቀረበኝ፤ ወዲያውም ጆቫኒ ደል ኮርሶ በመኪና ጽሕፈት ፈተና አደረገልኝና ስለወጣሁ ዕለቱን በ፻ ሊሬ የወር ደመወዝ ቆርጦ ስለተቀበለኝ። እኔም በመቃድሾ እማገኘው ደመወዝ ብልጫው ትንሽ ስለሆነ በሀገሬ መቅረቴን ፈቀድሁና በአሥመራ ቀረሁ። አቶ ወልደማርያም ሥራዉን አስረካክቦኝ ሔደና ከኮመንዳቶረ ጆቫኒ ደል ኮርሶ ጋር በደስታና ስምምነት ሥሠራ ሳለሁ፤ አንድ በኩራት የተሞላ፣ ክርስትያኖቹን የጠላ፣ በየሰዓቱ ልብሱን የሚለውጥ ጋንተስ የተባለ ግምጃ ቤት በክፉ ዓይን ተመለከተኝ፤ እኔም እኔን የሚጠላበትን ምክንያት ስላላወቅሁት በብዙ ደነቀኝ። ይህም ያለ ልክ በኩራት የተሞላው ከንቱ የሆነው ዮሴፍ ጋንተስ የግምጃ ቤቱን ሒሳብ አማትቶ ፴፭ሺህ ሊሬ አጥፍቶ በስንብት ወደ ጣሊያን ሀገር ተነስቶ ሔደ። ደል ኮርሶም ገቢን ወጭውን፣ በባንክ ያለውንም ገንዘብ ሲያመዛዝን ሳለ ፴፭ሺህ ሊሬ ጉድለት ስለተገኘበት አታላው ጋንተስ ናፓሊ እንደደረሰ ታሥሮ አሥመራ እንዲመለስ አስቀድሞ በቴሌግራም አስታውቆ አሥመጣው።” ገጽ 43

“የሠገነይቲ አቶ ወልደ ማርያም ተወልደ ጤና ስላጣ ወደ የኔው ሥራ አሥመራ ሲመጣ እኔም በሱ ሥራ የ፻፶፭ ሊሬ ደመወዝ ወደ እሳታዊው ፋጢማ ኤረ ተዛውሬ እንድሠራ ከደል ኮርሶ ታዝዤ ሔድሁ። ገና በዚህ ሀገር ስገባ የዓጋሜው ወጣት ፊታውራሪ ለበን ስብሐት መጡና ሰንብተው ሲሔዱ ፊታውራሪ ተድላ የሚባሉትም ሹም ከዓጋሜ በአሥመራ መንገድ መጡ። እንደመጡም ፈልገው ተገናኙኝና ስለ ፓታሳም ፈጥነው ጠየቁኝ፤ እኔም አላውቅም ስል መለስኩላቸው። በማግሥቱ እሁድ ቀን ነበርና ለማየታቸው ባረፉበት ቦታ ስሔድ ፊታውራሪ ተድላ በደስታ ፈጥነው ተቀበሉኝና ወዲያው ቁጭ ብለን ስንነጋገር “ባክዎ ይህንን የደሎል ማዕድን ወዴት ነው የሚወስዱት? ምንስ ጥቅም ያገኙበታል? ይንገሩኝ” ብለው አጥብቀው ጠየቁኝ። እኔም ጥያቄአቸው ደስ ስላለኝ “ከፍ ያለ ብዙ ጥቅም ባያገኙበት በከንቱ የሀገራችንን አፈር እየቆፈሩ የባቡር መንገድ እስከ ባህር ዘርግተው ባላጓዙት ነበር። የኢትዮጵያ መንግሥት እውቀት ቢኖረው ከባለ ብዙ ጥበብ እንደ ጀርመን መንግሥት ከመሰለው ጋር ውል ተዋውሎ ቢያሠራው ኑሮ ብዙ ጥቅም ባገኘበት ነበር”። ገጽ 43

“የዚሁም ኢትዮጵያው ደሎል አንድ ኩንታል አፈር፣ በአደን ፮፻ በኤውሮጳ ሺህ ፸ በአመሪካ ፪ ሺህ ሊሬ ይሸጣል፤ ባሩድ ይሠሩበታል፤ መድኃኒት ይቀምሙበታል፤ ጥቅማቸውም ወሰን የለውም ብዬ” ስላቸው ተከትሎዋቸው ከመጡት ከ፰ቱ ልብስ ከሌላቸው አሽከሮቻቸው ውስጥ የዓዲ አቡን ተስፋሁነኝ ከዚህ በላይ የተጻፈውን ቃል በቅጽበት ለቢያንኪ ነገረውና ፷ ብር ዋጋ ተቀበለብኝ። ለዚሁ ሥራ ዋና ሹም የሆነው ቢያንኪም “ተስፋሚካኤል ትኩእ የተባለው ጸሐፊ የተሰወረ የኢትዮጵያ መንግሥት ቈንስል ሆኖ ሲሠራ ስለተገኘ በፖሊስ ጥበቃ ወደ አሥመራ ልከነዋልና በቀጥታ ወደ አሰብ እሥር ቤት ተልኮ እንዲታሰር” ብሎ ለኮመንዳቶረ ጆቫኒ ደልኮርሶ በቀጥታ ጻፈለት። ለኔ” ወደ አሥመራ እንድትወጣ” አለኝ። “አልወጣም የደል ኮርሶ ትእዛዝ ካልደረሰኝ” ብዬ ፫ት ቀን በቤቴ ተቀምጨ ሳወጣ ሳወርድ ሰነብትሁና ወደ የኢትዮጵያዉን አፍቃሪ የሆነው የመድፈኞች ሻምበል የጨዋ ልጅ አምፕሪሮሪ በአሥመራ መሥያ ቤት ስለማውቀው እሱ ዘንድ ኼጄ “የላከኝ ደል ኮርሶ ነው፤ ያለ የደል ኮርሶ ትእዛዝም ቢያንኩ ወደ አሥመራ እንድትወጣ ብሎ አለኝ፤ እኔም የላከኝ ኮመንዳቶረ ደል ኮርሶ ስለሆነ ያለ የሱ ፌርማ አልሔድም አልሁት፤ ነገሩስ ምን ይመስልሃል” አልሁት። እምፐራቶሪም በብያንክ መጥፎ የስለላ መሠለልን ሥራ አዘነ፤ ነገሩንም ስለፈራ “ዝም ብለህ መሔድ ይሻላል” እያለ ካጽናናኝ በኋላ ለአሽከሩ፣ ቢያንኪ ተንኮል እንደሠራብኝ ነግሮት ኑሮ ተከተለኝ እና ዳርዳሩን ነገረኝ። እኔም ከመርሶ ፋቲማ ኤረ ወደ ዓጋሜ ለመውጣት አሰብሁ፤ ዳሩ ግን ዓጋሜ ሳልደርስ በወኃ ጥም ብሞት ወይም በመንገድ በማላውቀው ሀገር ሞያ ሳልሠራ በከንቱ ብያዝ፣ ለአባቴና ለዘመዶቼ ከማስወረሴ በላይ ማሳዘኔን አሰብሁና ወደ አሥመራ ወጥቼ የሚመጣብኝን አሥራትና መከራ መቀበል ይቻላል ብዬ ወደ ሠፈሬ ተመለስሁና ሻንጣየን አሸክሜ ወደ ጀልባይቱ ገባሁ።” ገጽ 43

" በዚህ ጊዜ እኔን የሚጠብቁ ሁለት ፖሊሶች በፍጥነት መጡና በቀኝና በግራ ሆነው ተሣፈሩ። . . . ምጽዋዕም እንደ ደረስን አንደኛው ቀረና ሁለተኛው ከኔ ጋር ከምፅዋዕ አሥመራ ድረስ ወጣ። እኔም በቀጥታ ወደ መሥሪያ ቤት ወደ ደጕ ኮመንዳቶሪ ጆቫኒ ደል ኮርሶ ዘንድ ኸጄ “አንተ ለሥራ ላከኝ፤ ግፈኛው ቢያንኪ ግን በፈቃዱ መለሰኝ፤ ምክንያቱስ ምንድር ነው” ብለው፣ እኔ ላኩህ እኔም አሥጠራሁህ፤ የሚያናግርህ ጉዳይ የለምና ፭ት ቀን አርፈህ ና” አለኝና ቢያንኪንና ለ፷ ብር የሸጠኝን ተስፋ ሁነኝን በፍጥነት በሥልክ ተጠሩና አሥመራ መጡ።" ገጽ 44

"ደል ኮርሶም በቁጣ ቃል ለቢያንኪና ለተስፋ ሁነኝ “አንተ አለ አገባብ የሰጠሀው ፷ ብር፣ አንተም በሐሰት የተቀበልካትን ለ፷ ብር መልሱ” ብሎ አስጨንቆ ሁለቱንም ያዛቸው። “የተሰወረ የኢትዮጵያ መንግሥት ቈንስል ሆኖ ተስፋሚካኤል ትኩእ ፖለቲካ ሲሠራ ስላገኘው ለተስፋሁነኝ የሰጠሁትን ፷ ብር ስለምን እከፍላለሁ? ተስፋሚካኤል ትኩእስ ይህን ያህል ከፍ ያለው ጉዳት በጣሊያን መንግሥት ላይ የሠራውን ሣይታሠር እንዴት ይቀራል” ብሎ መለሰ። “ተስፋሚካኤል ትኩእ ለክቡር ራስ ሥዩም መንገሻ ዮሐንስ ለልጃቸው ለደጃዝማች ካሣ ስዩም፣ ለደጃዝማች ተካም ጋር ደብዳቤዎች ስንጻጻፍ ሳስተረጕመው ተስፋሚካኤል ትኩእ ምንጊዜም ምስጢር ውጭ አውጥቶብኝ አያውቅም ነበር። እኔ መርጨ ያመጣኹትን ሥራተኛ አለማመንህ እሱን አይደለም እኔን ነው፤ ተስፋሚካኤልም አንተ እንደምትለው ክስ ዓይነት ዓይሠራም ቢሠራም እኛን የሚያገባን ጉዳይ ዓይደለም። ይህም ወጣት ልጅ በዚሁ ፖለቲካ አሰብ እሥር ቤት ቢታሠር እኛ ምን እንጠቀምበታል፤ አንተም በማያገባህ ሥራ አትግባ! የፖለቲካ ሠራተኛ ዓይደለህምና ተጠንቀቅ” ብሎ ደልኮርሶ በቁጣ በቢያንኪ ላይ በይፋ ተቆጣውና ተንቀጠቀጠ፤ በፍራትም ያለልክ ተሸበረ።" ገጽ 45

"ኮመንዳቶሪ ጆቫኒ ሰል ኮርሶም “ተስፋሁነኝ የሚባል ዘበኛ እኛንና እናንተን የሚያጣላን መጥፎ ሰው ስለሆነ ከደሎል ሥራ እንዲወገድ፣ ወደ ኤርትራም ኣንዳይመለስ እንድታደርጉልን አጥብቀን ለክቡርነትዎ እንለምናለን” የሚል ደብዳቤ ለክቡር ራስ ሥዩምና ለደጃዝማች ካሣ ጻፈና እጁንም በኤርትራ መንግሥት በኩል ወደ ዓድዋ ተልኮ በደጃዝማች ካሣ ዘንድ ውርደትና አለንጋም ተቀበለ። ተስፋሁነኝ ፷ብር እበላለሁ ሲል ተበላ፤ ተዋረደ። እግዚአብሔር ግን በሰፊ ቅን ትክክለኛው ፍርዱ ከቢያንኪና ተስፋሁነኝ ሰብቅና እሥራት ሰውሮ ስላተረፈኝ አመሰገንሁት፤ አመሰግነዋለሁም።" ገጽ 46

"ለኢትዮጵያ ሕዝብ እማኝና ጠበቃም የሆነው መልካሙ ደል ኮርሶ ይህን ጭቅጭቅ ከፈጸመ በኋላ እኔን ጠራኝ እና “የምጽዋዕ የጨው መስሪያ ቤት አለቃው እኔ ስለሆንኩ ለዛሬ በ፻፷ ሊሬ ለወደፊቱም ደመወዝ እንዲጨመርለት፣ ቤትም እንዲሠጠው” ብሎ ጽፎ ላከኝ፤ በጥር ወር ፲፱፻፲፱ ዓ.ም. በጸሐፊነት ፪፻ ሊሬ ደመወዝ ስሠራ ሳለሁ፣ በየቀኑ የሚመጡትን የእንግሊዝ መርከቦች የሚጭኑትን ጨው ዋጋ በወርቅ ለውጥ ብዙ ሚሊዮን የወር ገቢ ነበራቸው፤ የጨው ሀብትና ሥራም የምጽዋዕን የመሰለ የተከናወነ ሥራ በዓለም ዓይገኝም። የምጽዋዕ ጨውና ዓሳም ጣፋጭነቱና ማማሩም ልዩ በመሆኑ በብዙ ተመስግነዋል። ገጽ 46

በኢትዮጵያ መንግሥት ስም ያለልክ እጅግ ከፍ ባለው ዋጋ ከፈረንሣይ ሀገር አጭር ውጅግራ ጠበንጃ የገዙ ደጃዝማች ጌታቸው አባተ ከነጓደኞቻቸው ምጽዋዕ ወረዱና በታሪኩ የታወቀውን የግራርን ጨው አመጣጥና ካንድ ሽህ የበለጠውን ሠራተኛ ሲሠራ፣ ጨው ትልቅ ወሰን የሌለው ክምር ሲከመር፣ ከተከመረበትም በምድር ባቡር ተሞልቶ ወደ ባህር ዳር ባለው መጋዜን ውስጥ ገብቶ ሲያፈሰው፣ ከዚያም ጥበባዊው የእውቀት ሥራ ሽቅብ አውጥቶ ወደ ወፍጮ ራሱ እየወረወረ ፈጭቶ መልሶም ወደሌላው መጋዜን ያገባዋል፣ ከዚሁም መጋዜን አንስቶም ወደ ባህር ውስጥ ያሉትን መርከቦች በፍጥነት ሲሞላ በማየታቸው፤ የኢትዮጵያ መላክተኞች ይቅርና ሞላው የዓለም ሕዝብ አደነቀው፤ አመሰገነውም።" ገጽ 46

“በዚሁ ጊዜ የመንግሥት የምጽዋዕ ጕምሩክ ሹሞች የሆኑት በትምህርታቸውና በእውቀታቸው ከፍ ያሉት ግራዝማች ተድላ ጋብርና ፊተውራሪ ዘወልደማርያም ዘገርጊስ፣ ብላት ዘርኤ ግርሙ ዘጠና ሊሬ ደመወዝ ለየ አንዳንዳቸው ሲሠሩ እኔ “፪፻፶ ሊሬ ካልተሠጠኝ በ፪፻ ሊሬ ደመወዝ ምንም አልሠራም” ብየ በ፮ ወር ወደ አሥመራ እምቢ ብዬ ሥወጣ በማየታቸው በብዙ ተደነቁ። “የተስፋሚካኤል ትኩእ ዕድል ድንጋይ የሚፈልጥ ዕድል ነው” ሲሉ መሰከሩ።" ገጽ 46

"ይህንኑ የምጽዋዕን ጥበባዊ የጨው ፋብሪካ ሥራ የሠራ ዓይምነ የሚባል አዋቂ መሐንዲስ ብዙ ምስጋና ከኤርትራዊያን ይገባዋል።" ገጽ 46

አርበኛው ከምፅዋዕ አሥመራ ተቀይረው ስራ እንደጀመሩ፣ ኤርትራ ዉስጥም ድርቅ እንደገባ፣ እሳቸውም ከአስመራ ሞቃዲሾ በጂቡቲ በኩል እንደተመለሱ፣ ጂቡቲ ላይም ልጅ በየነ ህብትዝጊን እንዳገኙ፣ ኃይለሥላሴም ልጅ በየነን በአ/አ ስራ ሊቀጥሯቸው እንዳሰቡ፣ ልጅ በየነ ግን ወደ ሮማ መመለስና ቀጥሎም የትሪፓሊ የእርሻ ዋና ዲራክተ ሆኖ ከእንደነበር ይገልጻሉ። መብራህቱ (ሎሬንሶ) ታእዛዝም በአደን ሥራ እንደጀመረና የኢትዮጵያን አልጋወራሽ በብዙ ዓይነት ፓለቲካ እንደረዳቸው፣ በኤደን እንዳገኛቸው፣ አ/አ መጥቶ ሥራ እንዲዝ ቢጠይቁት ፈረንሣይ ሄዶ መማር እንደሚሻ እንደገለጠላቸው፣ እሳቸውም እንደፈቀዱት፣ እሱም ፓሪስ ሂዶ በየዓመቱ አንደኛ እየሆነ በሕግ ሊቅነት ምስክር እንደተቀበለ ይገልጻሉ

መቃድሾ ከተመለሱ በኋላ ያጋጠማቸውን ሁሉ በሶማልያ የነበሩ ኤርትራዉያን ለኢትዮጵያ መንግሥት በመስራታቸው ያጋጠማቸውን እንግልትና ሞትም ስም እየጠቀሱ እንዲሁም ስለ ልጅ ኢያሱ በቀጥዩ ክፍል ይዘከዝኩልናል! ይህ ሁሉ ደግሞ ያሁኑ ትውልድ ማለትም አዳሜ ገና ሳይወለድ በአንቀልባም እንኳ ገና ሳይታዘል የተፈጸመ ነው!!! :mrgreen:
1.Amesegen alehugn
2.degmo men emarebet alehugn.

Re: ተስፋሚካኤል ትኩእ (1892 – 1964)] - ወለዶና ክነቦ ዝግባእ መኽዘን ታሪኽ

Posted: 12 Jun 2019, 13:35
by Degnet
Meleket wrote:
11 Jun 2019, 11:06
Degnet wrote:
11 Jun 2019, 09:56
Meleket wrote:
08 Jun 2019, 06:03
በያንዳንዱ አንቀጽ ውስጥ ያለውን ረቂቅ መልእኽት ከቻላችሁ ፈልፍላችሁ አግኙት! ሰውየው የዋዛ አይመስሉም! :mrgreen:
...
Thank you a lot,I always wanted to know how and when dej.Abraha Araya died ,it is a historic book.I think I have said enough,I will go back to my reading now.
ደግነት ወንድሜ ግዜ ስታገኝ መጸሐፉን ከጫፍ እስከ ጫፍ ለማንበብ ሞክር፣ እኔ አለፍ አለፍ እያልኩ ስለሆነ ለማካፈል የሞከርኩት። አብርሃ አርአያ የሚል ስም እስካሁን ቢያንስ ቢያንስ ሁለት ጊዜ ተጠቅሰዋል፡
አንደኛው በገጽ 13 ልጅ አብርሃ አርአያ ተብሎ
Meleket wrote:
07 Jun 2019, 11:55

"አልጋ ፈላጊ ሆነው በአሳኦርታና በጠልጣል እያሉ በጽናት ሲቀመጡ የነበሩበትን የደጃዝማች ደበብ አራአያም የ፲፪ ዓመት ልጅ ወንድማቸው ልጅ አብርሃ አርአያን መያዣ ሰጥተው ፫፻ ወጨፎ ጠበንጃ ከነ ጥይቱ ከጣሊያን መቀበላቸውን ደጃዝማች ባህታን ለመግደል መሰናዳታቸውን ስለ ሰሙ የደጃዝማች ባህታም ከሀባብ ወደ ምፅዋዕ በመምጣት ለጣሊያን እጃቸውን ሰጡ።" ገጽ 13
ሁለተኛው በገጽ 36 ደጃዝማች አብርሃ አርአያ ተብለው
Meleket wrote:
08 Jun 2019, 06:03

"ደጃዝማች አብርሃ አርአያ ከዚያው ትምሕርታቸውና ወጣቱ ሰውነታችው፣ ወርቅ ከመሰለ ወደረኛ ከሌለው ቅላታቸው ጋር፣ ከኣኒያ እሳቶች የሆኑት የትግሬ አሽከሮቻቸው ሲሔዱ እንደመብረቅ፣ ዓይቻቸው ሳልጠግባቸው ከእውቀትና ከወንድነት ጋር ከፈ ያለ ድፍረትና ንቃትም ያላቸው ሰው ሆነው ታዩኝ። የልጅ ኢያሱ ወገን ነበሩና በሰገሌ ጊዜ ደጃዝማች አብርሃ አርአያና ደጃዝማች አመዴ ወሌ ብጡል ሁለቱ ትግሮች ባንድግዜ ሞቱ ማለትን ሰማን፤ በዚሁም ጊዜ አዲስ አበባ በጭቃ የተሞላች “ፊንፍኔ” የተባለች ዱርና ገደል ነበረች። ይህም ከተማ አጼ ምኒልክ በሌሉበት ከኣንጦጦ ፍልወኃ ለመታጠብ ወርደው ኮረብታይቱን ለከተማነት የመረጡዋት፣ የቆረቆሩዋት የሸዋን ቤተ መንግሥት በችሎታዊው ድፍረትና እውቀታቸው ብዛት ያቋቋሙት እቴጌ ጣይቱ ብጡል ናቸው። የሸዋ ንጉሥ ምኒልክ ግን ውራጌዎችንንና ኦሮሞዎችን ስለፈሩ ቆጥ በመሰለው የኣንቶቶ ገደል ሠፈሩ፤ ወድትዋ የሴቶች መመክያ እቴጌ ጣይቱ ግን በትግሮችና በሰሜነኞች አሽከሮቻቸውና በእውቀታቸው ብዛት ዘው አስጭነው ኢትዮጵያን አስገዙዋቸው።" ገጽ 36
እንግዲህ ተከታዪ አንባቢዎች እንዳይደናገሩ ወይም ግልጥ ለማድረግ መጸሐፉን እየጠቃቀስን ገጽ 49 አካባቢ ደርሰናል። ነገሩ ነው እንጂ መጸሐፉ መርጦ ለመጥቀስም አያመችም ምክንያቱም እያንዳንዷ ዓረፍተነገር ብርቕ ታሪክን ከዝናለችና፣ ቢሆንም ይዘቱን በከፊልም ቢሆን መካፈሉን እንቀጥላለን። መጨረሻ የደረስንበት ክፍል እዚህ ነው! መልካም ንባብ።
Meleket wrote:
11 Jun 2019, 03:32
እኒህ ቆፍጣና አርበኛ፡ ኤርትራ ተመልሰው በዳሎል የፖታሽ ሥራቸው ያጋጠማቸውን ሁኔታ፡ የዓዲ አቡኑ ሰላይ የተስፋሁነኝ ሸፍጥ፣ በወቅቱ ከፖታስ ይገኝ የነበረውን ትርፍ በኣኃዝ አስደግፈው ይተነትናሉ፣ አያይዘውም በኢትዮጵያ መንግሥት ስም ያለልክ እጅግ ከፍ ባለው ዋጋ ከፈረንሣይ ሀገር አጭር ውጅግራ ጠበንጃ የገዙ ደጃዝማች ጌታቸው አባተ በምጽዋዕ ስላጋጠማችወ ጉዳይ ተንትነው ጨው እንዴት እንደሚመረትም ሂደቱን ገልጸው የፋብሪካውንም ዲዛይን ማን እንደነደፈው ሳይቀር ዘርዝረው ይገልጹልናል። ከገለጡ አይቀር እንዲ አርጎ እውነቱን ቁልጭ አድርጎ መግለጥ ነው እንጂ! በርግጥ እንዲህ አድርገው እውነታን የሚገልጹ ኤርትራውያን አባቶች እና ቅድመ አያቶች መኖራቸው ያኮራናል! :lol: ይህን ጽሑፍና ትንታኔ እጅግ ብርቅ የሚያደርገው ዋነኛ ምክንያት፣ አሁን ያለው ትውልድ ገሚሱ ገና ሳይወለድ፣ ገሚሱም ገና ባንቀልባ ላይ ታዝሎ እያለ የነበረን ሁኔታን ፍንትው አድርጎ መግለጡ ነው!!! መልካም ንባብ። :mrgreen:

ባባቴ ቤት በሀገሬ በሠገነይቲ አንድ ወር ስቀመጥ ከዘመዶቼ ብዙ ስልቻ ማር ስጦታ መጣልኝ፤ በዚያም ፲፱፻፲ ዓ.ም. ወሰን የሌለው ማር ከየ ጫካውና ከየ ቤቱም ሲቆረጥ በብዙ አስደነቀ፤ ዘመኑም የቅቤ ፣ የእህል፣ የማር ዘበን ተባለ። ስለዚሁ መልካም ዘበን ሰው ሁሉ በፍቅር ተሳስሮ ተስማማ፤ መሬቲቱም ፍሬዋን ሰጠች፤ እኔም ያለ ኅሳብና ያለወጭ ገንዘብ ባባቴ ቤት ቶይቼ አሥመራ የገባሁኝ ቀን የተማሪ ቤት ጓደኛዬ አቶ ወልደማርያም ተወልደን አገኘሁና በብዙ ደስታ ተቀብሎ ጋበዘኝ። በዚሁም ግብጃ መካከል “እኔ መርሳ ፋጢማ ኤረሰለ የደሎል ፖታሳ ሥራ እሔዳለሁና መቃድሾ ከመመለስ ይልቅ በዋናው መሥሪያ ቤታችን የኔው የጸሐፊነቱ ቦታ አለና ነገ ጡዋትና” አለኝ። እኔም አባቴ መቃድሾ መመለሴን ስላልፈቀዱ ደስ ለማሰኘታቸው ብዬ ኅሳቡን ተቀበልሁት።” ገጽ 42

በማግሥቱም የፖታሳ(ማዕድን) ኩባንያ ዲረክሲዩ ወደ ኮመንዳቶረ ጆቫኒ ደል ኮርሶ ፊት በቅጽበት አቶ ወልደማርያም አቀረበኝ፤ ወዲያውም ጆቫኒ ደል ኮርሶ በመኪና ጽሕፈት ፈተና አደረገልኝና ስለወጣሁ ዕለቱን በ፻ ሊሬ የወር ደመወዝ ቆርጦ ስለተቀበለኝ። እኔም በመቃድሾ እማገኘው ደመወዝ ብልጫው ትንሽ ስለሆነ በሀገሬ መቅረቴን ፈቀድሁና በአሥመራ ቀረሁ። አቶ ወልደማርያም ሥራዉን አስረካክቦኝ ሔደና ከኮመንዳቶረ ጆቫኒ ደል ኮርሶ ጋር በደስታና ስምምነት ሥሠራ ሳለሁ፤ አንድ በኩራት የተሞላ፣ ክርስትያኖቹን የጠላ፣ በየሰዓቱ ልብሱን የሚለውጥ ጋንተስ የተባለ ግምጃ ቤት በክፉ ዓይን ተመለከተኝ፤ እኔም እኔን የሚጠላበትን ምክንያት ስላላወቅሁት በብዙ ደነቀኝ። ይህም ያለ ልክ በኩራት የተሞላው ከንቱ የሆነው ዮሴፍ ጋንተስ የግምጃ ቤቱን ሒሳብ አማትቶ ፴፭ሺህ ሊሬ አጥፍቶ በስንብት ወደ ጣሊያን ሀገር ተነስቶ ሔደ። ደል ኮርሶም ገቢን ወጭውን፣ በባንክ ያለውንም ገንዘብ ሲያመዛዝን ሳለ ፴፭ሺህ ሊሬ ጉድለት ስለተገኘበት አታላው ጋንተስ ናፓሊ እንደደረሰ ታሥሮ አሥመራ እንዲመለስ አስቀድሞ በቴሌግራም አስታውቆ አሥመጣው።” ገጽ 43

“የሠገነይቲ አቶ ወልደ ማርያም ተወልደ ጤና ስላጣ ወደ የኔው ሥራ አሥመራ ሲመጣ እኔም በሱ ሥራ የ፻፶፭ ሊሬ ደመወዝ ወደ እሳታዊው ፋጢማ ኤረ ተዛውሬ እንድሠራ ከደል ኮርሶ ታዝዤ ሔድሁ። ገና በዚህ ሀገር ስገባ የዓጋሜው ወጣት ፊታውራሪ ለበን ስብሐት መጡና ሰንብተው ሲሔዱ ፊታውራሪ ተድላ የሚባሉትም ሹም ከዓጋሜ በአሥመራ መንገድ መጡ። እንደመጡም ፈልገው ተገናኙኝና ስለ ፓታሳም ፈጥነው ጠየቁኝ፤ እኔም አላውቅም ስል መለስኩላቸው። በማግሥቱ እሁድ ቀን ነበርና ለማየታቸው ባረፉበት ቦታ ስሔድ ፊታውራሪ ተድላ በደስታ ፈጥነው ተቀበሉኝና ወዲያው ቁጭ ብለን ስንነጋገር “ባክዎ ይህንን የደሎል ማዕድን ወዴት ነው የሚወስዱት? ምንስ ጥቅም ያገኙበታል? ይንገሩኝ” ብለው አጥብቀው ጠየቁኝ። እኔም ጥያቄአቸው ደስ ስላለኝ “ከፍ ያለ ብዙ ጥቅም ባያገኙበት በከንቱ የሀገራችንን አፈር እየቆፈሩ የባቡር መንገድ እስከ ባህር ዘርግተው ባላጓዙት ነበር። የኢትዮጵያ መንግሥት እውቀት ቢኖረው ከባለ ብዙ ጥበብ እንደ ጀርመን መንግሥት ከመሰለው ጋር ውል ተዋውሎ ቢያሠራው ኑሮ ብዙ ጥቅም ባገኘበት ነበር”። ገጽ 43

“የዚሁም ኢትዮጵያው ደሎል አንድ ኩንታል አፈር፣ በአደን ፮፻ በኤውሮጳ ሺህ ፸ በአመሪካ ፪ ሺህ ሊሬ ይሸጣል፤ ባሩድ ይሠሩበታል፤ መድኃኒት ይቀምሙበታል፤ ጥቅማቸውም ወሰን የለውም ብዬ” ስላቸው ተከትሎዋቸው ከመጡት ከ፰ቱ ልብስ ከሌላቸው አሽከሮቻቸው ውስጥ የዓዲ አቡን ተስፋሁነኝ ከዚህ በላይ የተጻፈውን ቃል በቅጽበት ለቢያንኪ ነገረውና ፷ ብር ዋጋ ተቀበለብኝ። ለዚሁ ሥራ ዋና ሹም የሆነው ቢያንኪም “ተስፋሚካኤል ትኩእ የተባለው ጸሐፊ የተሰወረ የኢትዮጵያ መንግሥት ቈንስል ሆኖ ሲሠራ ስለተገኘ በፖሊስ ጥበቃ ወደ አሥመራ ልከነዋልና በቀጥታ ወደ አሰብ እሥር ቤት ተልኮ እንዲታሰር” ብሎ ለኮመንዳቶረ ጆቫኒ ደልኮርሶ በቀጥታ ጻፈለት። ለኔ” ወደ አሥመራ እንድትወጣ” አለኝ። “አልወጣም የደል ኮርሶ ትእዛዝ ካልደረሰኝ” ብዬ ፫ት ቀን በቤቴ ተቀምጨ ሳወጣ ሳወርድ ሰነብትሁና ወደ የኢትዮጵያዉን አፍቃሪ የሆነው የመድፈኞች ሻምበል የጨዋ ልጅ አምፕሪሮሪ በአሥመራ መሥያ ቤት ስለማውቀው እሱ ዘንድ ኼጄ “የላከኝ ደል ኮርሶ ነው፤ ያለ የደል ኮርሶ ትእዛዝም ቢያንኩ ወደ አሥመራ እንድትወጣ ብሎ አለኝ፤ እኔም የላከኝ ኮመንዳቶረ ደል ኮርሶ ስለሆነ ያለ የሱ ፌርማ አልሔድም አልሁት፤ ነገሩስ ምን ይመስልሃል” አልሁት። እምፐራቶሪም በብያንክ መጥፎ የስለላ መሠለልን ሥራ አዘነ፤ ነገሩንም ስለፈራ “ዝም ብለህ መሔድ ይሻላል” እያለ ካጽናናኝ በኋላ ለአሽከሩ፣ ቢያንኪ ተንኮል እንደሠራብኝ ነግሮት ኑሮ ተከተለኝ እና ዳርዳሩን ነገረኝ። እኔም ከመርሶ ፋቲማ ኤረ ወደ ዓጋሜ ለመውጣት አሰብሁ፤ ዳሩ ግን ዓጋሜ ሳልደርስ በወኃ ጥም ብሞት ወይም በመንገድ በማላውቀው ሀገር ሞያ ሳልሠራ በከንቱ ብያዝ፣ ለአባቴና ለዘመዶቼ ከማስወረሴ በላይ ማሳዘኔን አሰብሁና ወደ አሥመራ ወጥቼ የሚመጣብኝን አሥራትና መከራ መቀበል ይቻላል ብዬ ወደ ሠፈሬ ተመለስሁና ሻንጣየን አሸክሜ ወደ ጀልባይቱ ገባሁ።” ገጽ 43

" በዚህ ጊዜ እኔን የሚጠብቁ ሁለት ፖሊሶች በፍጥነት መጡና በቀኝና በግራ ሆነው ተሣፈሩ። . . . ምጽዋዕም እንደ ደረስን አንደኛው ቀረና ሁለተኛው ከኔ ጋር ከምፅዋዕ አሥመራ ድረስ ወጣ። እኔም በቀጥታ ወደ መሥሪያ ቤት ወደ ደጕ ኮመንዳቶሪ ጆቫኒ ደል ኮርሶ ዘንድ ኸጄ “አንተ ለሥራ ላከኝ፤ ግፈኛው ቢያንኪ ግን በፈቃዱ መለሰኝ፤ ምክንያቱስ ምንድር ነው” ብለው፣ እኔ ላኩህ እኔም አሥጠራሁህ፤ የሚያናግርህ ጉዳይ የለምና ፭ት ቀን አርፈህ ና” አለኝና ቢያንኪንና ለ፷ ብር የሸጠኝን ተስፋ ሁነኝን በፍጥነት በሥልክ ተጠሩና አሥመራ መጡ።" ገጽ 44

"ደል ኮርሶም በቁጣ ቃል ለቢያንኪና ለተስፋ ሁነኝ “አንተ አለ አገባብ የሰጠሀው ፷ ብር፣ አንተም በሐሰት የተቀበልካትን ለ፷ ብር መልሱ” ብሎ አስጨንቆ ሁለቱንም ያዛቸው። “የተሰወረ የኢትዮጵያ መንግሥት ቈንስል ሆኖ ተስፋሚካኤል ትኩእ ፖለቲካ ሲሠራ ስላገኘው ለተስፋሁነኝ የሰጠሁትን ፷ ብር ስለምን እከፍላለሁ? ተስፋሚካኤል ትኩእስ ይህን ያህል ከፍ ያለው ጉዳት በጣሊያን መንግሥት ላይ የሠራውን ሣይታሠር እንዴት ይቀራል” ብሎ መለሰ። “ተስፋሚካኤል ትኩእ ለክቡር ራስ ሥዩም መንገሻ ዮሐንስ ለልጃቸው ለደጃዝማች ካሣ ስዩም፣ ለደጃዝማች ተካም ጋር ደብዳቤዎች ስንጻጻፍ ሳስተረጕመው ተስፋሚካኤል ትኩእ ምንጊዜም ምስጢር ውጭ አውጥቶብኝ አያውቅም ነበር። እኔ መርጨ ያመጣኹትን ሥራተኛ አለማመንህ እሱን አይደለም እኔን ነው፤ ተስፋሚካኤልም አንተ እንደምትለው ክስ ዓይነት ዓይሠራም ቢሠራም እኛን የሚያገባን ጉዳይ ዓይደለም። ይህም ወጣት ልጅ በዚሁ ፖለቲካ አሰብ እሥር ቤት ቢታሠር እኛ ምን እንጠቀምበታል፤ አንተም በማያገባህ ሥራ አትግባ! የፖለቲካ ሠራተኛ ዓይደለህምና ተጠንቀቅ” ብሎ ደልኮርሶ በቁጣ በቢያንኪ ላይ በይፋ ተቆጣውና ተንቀጠቀጠ፤ በፍራትም ያለልክ ተሸበረ።" ገጽ 45

"ኮመንዳቶሪ ጆቫኒ ሰል ኮርሶም “ተስፋሁነኝ የሚባል ዘበኛ እኛንና እናንተን የሚያጣላን መጥፎ ሰው ስለሆነ ከደሎል ሥራ እንዲወገድ፣ ወደ ኤርትራም ኣንዳይመለስ እንድታደርጉልን አጥብቀን ለክቡርነትዎ እንለምናለን” የሚል ደብዳቤ ለክቡር ራስ ሥዩምና ለደጃዝማች ካሣ ጻፈና እጁንም በኤርትራ መንግሥት በኩል ወደ ዓድዋ ተልኮ በደጃዝማች ካሣ ዘንድ ውርደትና አለንጋም ተቀበለ። ተስፋሁነኝ ፷ብር እበላለሁ ሲል ተበላ፤ ተዋረደ። እግዚአብሔር ግን በሰፊ ቅን ትክክለኛው ፍርዱ ከቢያንኪና ተስፋሁነኝ ሰብቅና እሥራት ሰውሮ ስላተረፈኝ አመሰገንሁት፤ አመሰግነዋለሁም።" ገጽ 46

"ለኢትዮጵያ ሕዝብ እማኝና ጠበቃም የሆነው መልካሙ ደል ኮርሶ ይህን ጭቅጭቅ ከፈጸመ በኋላ እኔን ጠራኝ እና “የምጽዋዕ የጨው መስሪያ ቤት አለቃው እኔ ስለሆንኩ ለዛሬ በ፻፷ ሊሬ ለወደፊቱም ደመወዝ እንዲጨመርለት፣ ቤትም እንዲሠጠው” ብሎ ጽፎ ላከኝ፤ በጥር ወር ፲፱፻፲፱ ዓ.ም. በጸሐፊነት ፪፻ ሊሬ ደመወዝ ስሠራ ሳለሁ፣ በየቀኑ የሚመጡትን የእንግሊዝ መርከቦች የሚጭኑትን ጨው ዋጋ በወርቅ ለውጥ ብዙ ሚሊዮን የወር ገቢ ነበራቸው፤ የጨው ሀብትና ሥራም የምጽዋዕን የመሰለ የተከናወነ ሥራ በዓለም ዓይገኝም። የምጽዋዕ ጨውና ዓሳም ጣፋጭነቱና ማማሩም ልዩ በመሆኑ በብዙ ተመስግነዋል። ገጽ 46

በኢትዮጵያ መንግሥት ስም ያለልክ እጅግ ከፍ ባለው ዋጋ ከፈረንሣይ ሀገር አጭር ውጅግራ ጠበንጃ የገዙ ደጃዝማች ጌታቸው አባተ ከነጓደኞቻቸው ምጽዋዕ ወረዱና በታሪኩ የታወቀውን የግራርን ጨው አመጣጥና ካንድ ሽህ የበለጠውን ሠራተኛ ሲሠራ፣ ጨው ትልቅ ወሰን የሌለው ክምር ሲከመር፣ ከተከመረበትም በምድር ባቡር ተሞልቶ ወደ ባህር ዳር ባለው መጋዜን ውስጥ ገብቶ ሲያፈሰው፣ ከዚያም ጥበባዊው የእውቀት ሥራ ሽቅብ አውጥቶ ወደ ወፍጮ ራሱ እየወረወረ ፈጭቶ መልሶም ወደሌላው መጋዜን ያገባዋል፣ ከዚሁም መጋዜን አንስቶም ወደ ባህር ውስጥ ያሉትን መርከቦች በፍጥነት ሲሞላ በማየታቸው፤ የኢትዮጵያ መላክተኞች ይቅርና ሞላው የዓለም ሕዝብ አደነቀው፤ አመሰገነውም።" ገጽ 46

“በዚሁ ጊዜ የመንግሥት የምጽዋዕ ጕምሩክ ሹሞች የሆኑት በትምህርታቸውና በእውቀታቸው ከፍ ያሉት ግራዝማች ተድላ ጋብርና ፊተውራሪ ዘወልደማርያም ዘገርጊስ፣ ብላት ዘርኤ ግርሙ ዘጠና ሊሬ ደመወዝ ለየ አንዳንዳቸው ሲሠሩ እኔ “፪፻፶ ሊሬ ካልተሠጠኝ በ፪፻ ሊሬ ደመወዝ ምንም አልሠራም” ብየ በ፮ ወር ወደ አሥመራ እምቢ ብዬ ሥወጣ በማየታቸው በብዙ ተደነቁ። “የተስፋሚካኤል ትኩእ ዕድል ድንጋይ የሚፈልጥ ዕድል ነው” ሲሉ መሰከሩ።" ገጽ 46

"ይህንኑ የምጽዋዕን ጥበባዊ የጨው ፋብሪካ ሥራ የሠራ ዓይምነ የሚባል አዋቂ መሐንዲስ ብዙ ምስጋና ከኤርትራዊያን ይገባዋል።" ገጽ 46

አርበኛው ከምፅዋዕ አሥመራ ተቀይረው ስራ እንደጀመሩ፣ ኤርትራ ዉስጥም ድርቅ እንደገባ፣ እሳቸውም ከአስመራ ሞቃዲሾ በጂቡቲ በኩል እንደተመለሱ፣ ጂቡቲ ላይም ልጅ በየነ ህብትዝጊን እንዳገኙ፣ ኃይለሥላሴም ልጅ በየነን በአ/አ ስራ ሊቀጥሯቸው እንዳሰቡ፣ ልጅ በየነ ግን ወደ ሮማ መመለስና ቀጥሎም የትሪፓሊ የእርሻ ዋና ዲራክተ ሆኖ ከእንደነበር ይገልጻሉ። መብራህቱ (ሎሬንሶ) ታእዛዝም በአደን ሥራ እንደጀመረና የኢትዮጵያን አልጋወራሽ በብዙ ዓይነት ፓለቲካ እንደረዳቸው፣ በኤደን እንዳገኛቸው፣ አ/አ መጥቶ ሥራ እንዲዝ ቢጠይቁት ፈረንሣይ ሄዶ መማር እንደሚሻ እንደገለጠላቸው፣ እሳቸውም እንደፈቀዱት፣ እሱም ፓሪስ ሂዶ በየዓመቱ አንደኛ እየሆነ በሕግ ሊቅነት ምስክር እንደተቀበለ ይገልጻሉ

መቃድሾ ከተመለሱ በኋላ ያጋጠማቸውን ሁሉ በሶማልያ የነበሩ ኤርትራዉያን ለኢትዮጵያ መንግሥት በመስራታቸው ያጋጠማቸውን እንግልትና ሞትም ስም እየጠቀሱ እንዲሁም ስለ ልጅ ኢያሱ በቀጥዩ ክፍል ይዘከዝኩልናል! ይህ ሁሉ ደግሞ ያሁኑ ትውልድ ማለትም አዳሜ ገና ሳይወለድ በአንቀልባም እንኳ ገና ሳይታዘል የተፈጸመ ነው!!! :mrgreen:
1.Amesegen alehugn
2.degmo men emarebet alehugn.

Re: ተስፋሚካኤል ትኩእ (1892 – 1964)] - ወለዶና ክነቦ ዝግባእ መኽዘን ታሪኽ

Posted: 12 Jun 2019, 13:35
by Degnet
Meleket wrote:
11 Jun 2019, 11:06
Degnet wrote:
11 Jun 2019, 09:56
Meleket wrote:
08 Jun 2019, 06:03
በያንዳንዱ አንቀጽ ውስጥ ያለውን ረቂቅ መልእኽት ከቻላችሁ ፈልፍላችሁ አግኙት! ሰውየው የዋዛ አይመስሉም! :mrgreen:
...
Thank you a lot,I always wanted to know how and when dej.Abraha Araya died ,it is a historic book.I think I have said enough,I will go back to my reading now.
ደግነት ወንድሜ ግዜ ስታገኝ መጸሐፉን ከጫፍ እስከ ጫፍ ለማንበብ ሞክር፣ እኔ አለፍ አለፍ እያልኩ ስለሆነ ለማካፈል የሞከርኩት። አብርሃ አርአያ የሚል ስም እስካሁን ቢያንስ ቢያንስ ሁለት ጊዜ ተጠቅሰዋል፡
አንደኛው በገጽ 13 ልጅ አብርሃ አርአያ ተብሎ
Meleket wrote:
07 Jun 2019, 11:55

"አልጋ ፈላጊ ሆነው በአሳኦርታና በጠልጣል እያሉ በጽናት ሲቀመጡ የነበሩበትን የደጃዝማች ደበብ አራአያም የ፲፪ ዓመት ልጅ ወንድማቸው ልጅ አብርሃ አርአያን መያዣ ሰጥተው ፫፻ ወጨፎ ጠበንጃ ከነ ጥይቱ ከጣሊያን መቀበላቸውን ደጃዝማች ባህታን ለመግደል መሰናዳታቸውን ስለ ሰሙ የደጃዝማች ባህታም ከሀባብ ወደ ምፅዋዕ በመምጣት ለጣሊያን እጃቸውን ሰጡ።" ገጽ 13
ሁለተኛው በገጽ 36 ደጃዝማች አብርሃ አርአያ ተብለው
Meleket wrote:
08 Jun 2019, 06:03

"ደጃዝማች አብርሃ አርአያ ከዚያው ትምሕርታቸውና ወጣቱ ሰውነታችው፣ ወርቅ ከመሰለ ወደረኛ ከሌለው ቅላታቸው ጋር፣ ከኣኒያ እሳቶች የሆኑት የትግሬ አሽከሮቻቸው ሲሔዱ እንደመብረቅ፣ ዓይቻቸው ሳልጠግባቸው ከእውቀትና ከወንድነት ጋር ከፈ ያለ ድፍረትና ንቃትም ያላቸው ሰው ሆነው ታዩኝ። የልጅ ኢያሱ ወገን ነበሩና በሰገሌ ጊዜ ደጃዝማች አብርሃ አርአያና ደጃዝማች አመዴ ወሌ ብጡል ሁለቱ ትግሮች ባንድግዜ ሞቱ ማለትን ሰማን፤ በዚሁም ጊዜ አዲስ አበባ በጭቃ የተሞላች “ፊንፍኔ” የተባለች ዱርና ገደል ነበረች። ይህም ከተማ አጼ ምኒልክ በሌሉበት ከኣንጦጦ ፍልወኃ ለመታጠብ ወርደው ኮረብታይቱን ለከተማነት የመረጡዋት፣ የቆረቆሩዋት የሸዋን ቤተ መንግሥት በችሎታዊው ድፍረትና እውቀታቸው ብዛት ያቋቋሙት እቴጌ ጣይቱ ብጡል ናቸው። የሸዋ ንጉሥ ምኒልክ ግን ውራጌዎችንንና ኦሮሞዎችን ስለፈሩ ቆጥ በመሰለው የኣንቶቶ ገደል ሠፈሩ፤ ወድትዋ የሴቶች መመክያ እቴጌ ጣይቱ ግን በትግሮችና በሰሜነኞች አሽከሮቻቸውና በእውቀታቸው ብዛት ዘው አስጭነው ኢትዮጵያን አስገዙዋቸው።" ገጽ 36
እንግዲህ ተከታዪ አንባቢዎች እንዳይደናገሩ ወይም ግልጥ ለማድረግ መጸሐፉን እየጠቃቀስን ገጽ 49 አካባቢ ደርሰናል። ነገሩ ነው እንጂ መጸሐፉ መርጦ ለመጥቀስም አያመችም ምክንያቱም እያንዳንዷ ዓረፍተነገር ብርቕ ታሪክን ከዝናለችና፣ ቢሆንም ይዘቱን በከፊልም ቢሆን መካፈሉን እንቀጥላለን። መጨረሻ የደረስንበት ክፍል እዚህ ነው! መልካም ንባብ።
Meleket wrote:
11 Jun 2019, 03:32
እኒህ ቆፍጣና አርበኛ፡ ኤርትራ ተመልሰው በዳሎል የፖታሽ ሥራቸው ያጋጠማቸውን ሁኔታ፡ የዓዲ አቡኑ ሰላይ የተስፋሁነኝ ሸፍጥ፣ በወቅቱ ከፖታስ ይገኝ የነበረውን ትርፍ በኣኃዝ አስደግፈው ይተነትናሉ፣ አያይዘውም በኢትዮጵያ መንግሥት ስም ያለልክ እጅግ ከፍ ባለው ዋጋ ከፈረንሣይ ሀገር አጭር ውጅግራ ጠበንጃ የገዙ ደጃዝማች ጌታቸው አባተ በምጽዋዕ ስላጋጠማችወ ጉዳይ ተንትነው ጨው እንዴት እንደሚመረትም ሂደቱን ገልጸው የፋብሪካውንም ዲዛይን ማን እንደነደፈው ሳይቀር ዘርዝረው ይገልጹልናል። ከገለጡ አይቀር እንዲ አርጎ እውነቱን ቁልጭ አድርጎ መግለጥ ነው እንጂ! በርግጥ እንዲህ አድርገው እውነታን የሚገልጹ ኤርትራውያን አባቶች እና ቅድመ አያቶች መኖራቸው ያኮራናል! :lol: ይህን ጽሑፍና ትንታኔ እጅግ ብርቅ የሚያደርገው ዋነኛ ምክንያት፣ አሁን ያለው ትውልድ ገሚሱ ገና ሳይወለድ፣ ገሚሱም ገና ባንቀልባ ላይ ታዝሎ እያለ የነበረን ሁኔታን ፍንትው አድርጎ መግለጡ ነው!!! መልካም ንባብ። :mrgreen:

ባባቴ ቤት በሀገሬ በሠገነይቲ አንድ ወር ስቀመጥ ከዘመዶቼ ብዙ ስልቻ ማር ስጦታ መጣልኝ፤ በዚያም ፲፱፻፲ ዓ.ም. ወሰን የሌለው ማር ከየ ጫካውና ከየ ቤቱም ሲቆረጥ በብዙ አስደነቀ፤ ዘመኑም የቅቤ ፣ የእህል፣ የማር ዘበን ተባለ። ስለዚሁ መልካም ዘበን ሰው ሁሉ በፍቅር ተሳስሮ ተስማማ፤ መሬቲቱም ፍሬዋን ሰጠች፤ እኔም ያለ ኅሳብና ያለወጭ ገንዘብ ባባቴ ቤት ቶይቼ አሥመራ የገባሁኝ ቀን የተማሪ ቤት ጓደኛዬ አቶ ወልደማርያም ተወልደን አገኘሁና በብዙ ደስታ ተቀብሎ ጋበዘኝ። በዚሁም ግብጃ መካከል “እኔ መርሳ ፋጢማ ኤረሰለ የደሎል ፖታሳ ሥራ እሔዳለሁና መቃድሾ ከመመለስ ይልቅ በዋናው መሥሪያ ቤታችን የኔው የጸሐፊነቱ ቦታ አለና ነገ ጡዋትና” አለኝ። እኔም አባቴ መቃድሾ መመለሴን ስላልፈቀዱ ደስ ለማሰኘታቸው ብዬ ኅሳቡን ተቀበልሁት።” ገጽ 42

በማግሥቱም የፖታሳ(ማዕድን) ኩባንያ ዲረክሲዩ ወደ ኮመንዳቶረ ጆቫኒ ደል ኮርሶ ፊት በቅጽበት አቶ ወልደማርያም አቀረበኝ፤ ወዲያውም ጆቫኒ ደል ኮርሶ በመኪና ጽሕፈት ፈተና አደረገልኝና ስለወጣሁ ዕለቱን በ፻ ሊሬ የወር ደመወዝ ቆርጦ ስለተቀበለኝ። እኔም በመቃድሾ እማገኘው ደመወዝ ብልጫው ትንሽ ስለሆነ በሀገሬ መቅረቴን ፈቀድሁና በአሥመራ ቀረሁ። አቶ ወልደማርያም ሥራዉን አስረካክቦኝ ሔደና ከኮመንዳቶረ ጆቫኒ ደል ኮርሶ ጋር በደስታና ስምምነት ሥሠራ ሳለሁ፤ አንድ በኩራት የተሞላ፣ ክርስትያኖቹን የጠላ፣ በየሰዓቱ ልብሱን የሚለውጥ ጋንተስ የተባለ ግምጃ ቤት በክፉ ዓይን ተመለከተኝ፤ እኔም እኔን የሚጠላበትን ምክንያት ስላላወቅሁት በብዙ ደነቀኝ። ይህም ያለ ልክ በኩራት የተሞላው ከንቱ የሆነው ዮሴፍ ጋንተስ የግምጃ ቤቱን ሒሳብ አማትቶ ፴፭ሺህ ሊሬ አጥፍቶ በስንብት ወደ ጣሊያን ሀገር ተነስቶ ሔደ። ደል ኮርሶም ገቢን ወጭውን፣ በባንክ ያለውንም ገንዘብ ሲያመዛዝን ሳለ ፴፭ሺህ ሊሬ ጉድለት ስለተገኘበት አታላው ጋንተስ ናፓሊ እንደደረሰ ታሥሮ አሥመራ እንዲመለስ አስቀድሞ በቴሌግራም አስታውቆ አሥመጣው።” ገጽ 43

“የሠገነይቲ አቶ ወልደ ማርያም ተወልደ ጤና ስላጣ ወደ የኔው ሥራ አሥመራ ሲመጣ እኔም በሱ ሥራ የ፻፶፭ ሊሬ ደመወዝ ወደ እሳታዊው ፋጢማ ኤረ ተዛውሬ እንድሠራ ከደል ኮርሶ ታዝዤ ሔድሁ። ገና በዚህ ሀገር ስገባ የዓጋሜው ወጣት ፊታውራሪ ለበን ስብሐት መጡና ሰንብተው ሲሔዱ ፊታውራሪ ተድላ የሚባሉትም ሹም ከዓጋሜ በአሥመራ መንገድ መጡ። እንደመጡም ፈልገው ተገናኙኝና ስለ ፓታሳም ፈጥነው ጠየቁኝ፤ እኔም አላውቅም ስል መለስኩላቸው። በማግሥቱ እሁድ ቀን ነበርና ለማየታቸው ባረፉበት ቦታ ስሔድ ፊታውራሪ ተድላ በደስታ ፈጥነው ተቀበሉኝና ወዲያው ቁጭ ብለን ስንነጋገር “ባክዎ ይህንን የደሎል ማዕድን ወዴት ነው የሚወስዱት? ምንስ ጥቅም ያገኙበታል? ይንገሩኝ” ብለው አጥብቀው ጠየቁኝ። እኔም ጥያቄአቸው ደስ ስላለኝ “ከፍ ያለ ብዙ ጥቅም ባያገኙበት በከንቱ የሀገራችንን አፈር እየቆፈሩ የባቡር መንገድ እስከ ባህር ዘርግተው ባላጓዙት ነበር። የኢትዮጵያ መንግሥት እውቀት ቢኖረው ከባለ ብዙ ጥበብ እንደ ጀርመን መንግሥት ከመሰለው ጋር ውል ተዋውሎ ቢያሠራው ኑሮ ብዙ ጥቅም ባገኘበት ነበር”። ገጽ 43

“የዚሁም ኢትዮጵያው ደሎል አንድ ኩንታል አፈር፣ በአደን ፮፻ በኤውሮጳ ሺህ ፸ በአመሪካ ፪ ሺህ ሊሬ ይሸጣል፤ ባሩድ ይሠሩበታል፤ መድኃኒት ይቀምሙበታል፤ ጥቅማቸውም ወሰን የለውም ብዬ” ስላቸው ተከትሎዋቸው ከመጡት ከ፰ቱ ልብስ ከሌላቸው አሽከሮቻቸው ውስጥ የዓዲ አቡን ተስፋሁነኝ ከዚህ በላይ የተጻፈውን ቃል በቅጽበት ለቢያንኪ ነገረውና ፷ ብር ዋጋ ተቀበለብኝ። ለዚሁ ሥራ ዋና ሹም የሆነው ቢያንኪም “ተስፋሚካኤል ትኩእ የተባለው ጸሐፊ የተሰወረ የኢትዮጵያ መንግሥት ቈንስል ሆኖ ሲሠራ ስለተገኘ በፖሊስ ጥበቃ ወደ አሥመራ ልከነዋልና በቀጥታ ወደ አሰብ እሥር ቤት ተልኮ እንዲታሰር” ብሎ ለኮመንዳቶረ ጆቫኒ ደልኮርሶ በቀጥታ ጻፈለት። ለኔ” ወደ አሥመራ እንድትወጣ” አለኝ። “አልወጣም የደል ኮርሶ ትእዛዝ ካልደረሰኝ” ብዬ ፫ት ቀን በቤቴ ተቀምጨ ሳወጣ ሳወርድ ሰነብትሁና ወደ የኢትዮጵያዉን አፍቃሪ የሆነው የመድፈኞች ሻምበል የጨዋ ልጅ አምፕሪሮሪ በአሥመራ መሥያ ቤት ስለማውቀው እሱ ዘንድ ኼጄ “የላከኝ ደል ኮርሶ ነው፤ ያለ የደል ኮርሶ ትእዛዝም ቢያንኩ ወደ አሥመራ እንድትወጣ ብሎ አለኝ፤ እኔም የላከኝ ኮመንዳቶረ ደል ኮርሶ ስለሆነ ያለ የሱ ፌርማ አልሔድም አልሁት፤ ነገሩስ ምን ይመስልሃል” አልሁት። እምፐራቶሪም በብያንክ መጥፎ የስለላ መሠለልን ሥራ አዘነ፤ ነገሩንም ስለፈራ “ዝም ብለህ መሔድ ይሻላል” እያለ ካጽናናኝ በኋላ ለአሽከሩ፣ ቢያንኪ ተንኮል እንደሠራብኝ ነግሮት ኑሮ ተከተለኝ እና ዳርዳሩን ነገረኝ። እኔም ከመርሶ ፋቲማ ኤረ ወደ ዓጋሜ ለመውጣት አሰብሁ፤ ዳሩ ግን ዓጋሜ ሳልደርስ በወኃ ጥም ብሞት ወይም በመንገድ በማላውቀው ሀገር ሞያ ሳልሠራ በከንቱ ብያዝ፣ ለአባቴና ለዘመዶቼ ከማስወረሴ በላይ ማሳዘኔን አሰብሁና ወደ አሥመራ ወጥቼ የሚመጣብኝን አሥራትና መከራ መቀበል ይቻላል ብዬ ወደ ሠፈሬ ተመለስሁና ሻንጣየን አሸክሜ ወደ ጀልባይቱ ገባሁ።” ገጽ 43

" በዚህ ጊዜ እኔን የሚጠብቁ ሁለት ፖሊሶች በፍጥነት መጡና በቀኝና በግራ ሆነው ተሣፈሩ። . . . ምጽዋዕም እንደ ደረስን አንደኛው ቀረና ሁለተኛው ከኔ ጋር ከምፅዋዕ አሥመራ ድረስ ወጣ። እኔም በቀጥታ ወደ መሥሪያ ቤት ወደ ደጕ ኮመንዳቶሪ ጆቫኒ ደል ኮርሶ ዘንድ ኸጄ “አንተ ለሥራ ላከኝ፤ ግፈኛው ቢያንኪ ግን በፈቃዱ መለሰኝ፤ ምክንያቱስ ምንድር ነው” ብለው፣ እኔ ላኩህ እኔም አሥጠራሁህ፤ የሚያናግርህ ጉዳይ የለምና ፭ት ቀን አርፈህ ና” አለኝና ቢያንኪንና ለ፷ ብር የሸጠኝን ተስፋ ሁነኝን በፍጥነት በሥልክ ተጠሩና አሥመራ መጡ።" ገጽ 44

"ደል ኮርሶም በቁጣ ቃል ለቢያንኪና ለተስፋ ሁነኝ “አንተ አለ አገባብ የሰጠሀው ፷ ብር፣ አንተም በሐሰት የተቀበልካትን ለ፷ ብር መልሱ” ብሎ አስጨንቆ ሁለቱንም ያዛቸው። “የተሰወረ የኢትዮጵያ መንግሥት ቈንስል ሆኖ ተስፋሚካኤል ትኩእ ፖለቲካ ሲሠራ ስላገኘው ለተስፋሁነኝ የሰጠሁትን ፷ ብር ስለምን እከፍላለሁ? ተስፋሚካኤል ትኩእስ ይህን ያህል ከፍ ያለው ጉዳት በጣሊያን መንግሥት ላይ የሠራውን ሣይታሠር እንዴት ይቀራል” ብሎ መለሰ። “ተስፋሚካኤል ትኩእ ለክቡር ራስ ሥዩም መንገሻ ዮሐንስ ለልጃቸው ለደጃዝማች ካሣ ስዩም፣ ለደጃዝማች ተካም ጋር ደብዳቤዎች ስንጻጻፍ ሳስተረጕመው ተስፋሚካኤል ትኩእ ምንጊዜም ምስጢር ውጭ አውጥቶብኝ አያውቅም ነበር። እኔ መርጨ ያመጣኹትን ሥራተኛ አለማመንህ እሱን አይደለም እኔን ነው፤ ተስፋሚካኤልም አንተ እንደምትለው ክስ ዓይነት ዓይሠራም ቢሠራም እኛን የሚያገባን ጉዳይ ዓይደለም። ይህም ወጣት ልጅ በዚሁ ፖለቲካ አሰብ እሥር ቤት ቢታሠር እኛ ምን እንጠቀምበታል፤ አንተም በማያገባህ ሥራ አትግባ! የፖለቲካ ሠራተኛ ዓይደለህምና ተጠንቀቅ” ብሎ ደልኮርሶ በቁጣ በቢያንኪ ላይ በይፋ ተቆጣውና ተንቀጠቀጠ፤ በፍራትም ያለልክ ተሸበረ።" ገጽ 45

"ኮመንዳቶሪ ጆቫኒ ሰል ኮርሶም “ተስፋሁነኝ የሚባል ዘበኛ እኛንና እናንተን የሚያጣላን መጥፎ ሰው ስለሆነ ከደሎል ሥራ እንዲወገድ፣ ወደ ኤርትራም ኣንዳይመለስ እንድታደርጉልን አጥብቀን ለክቡርነትዎ እንለምናለን” የሚል ደብዳቤ ለክቡር ራስ ሥዩምና ለደጃዝማች ካሣ ጻፈና እጁንም በኤርትራ መንግሥት በኩል ወደ ዓድዋ ተልኮ በደጃዝማች ካሣ ዘንድ ውርደትና አለንጋም ተቀበለ። ተስፋሁነኝ ፷ብር እበላለሁ ሲል ተበላ፤ ተዋረደ። እግዚአብሔር ግን በሰፊ ቅን ትክክለኛው ፍርዱ ከቢያንኪና ተስፋሁነኝ ሰብቅና እሥራት ሰውሮ ስላተረፈኝ አመሰገንሁት፤ አመሰግነዋለሁም።" ገጽ 46

"ለኢትዮጵያ ሕዝብ እማኝና ጠበቃም የሆነው መልካሙ ደል ኮርሶ ይህን ጭቅጭቅ ከፈጸመ በኋላ እኔን ጠራኝ እና “የምጽዋዕ የጨው መስሪያ ቤት አለቃው እኔ ስለሆንኩ ለዛሬ በ፻፷ ሊሬ ለወደፊቱም ደመወዝ እንዲጨመርለት፣ ቤትም እንዲሠጠው” ብሎ ጽፎ ላከኝ፤ በጥር ወር ፲፱፻፲፱ ዓ.ም. በጸሐፊነት ፪፻ ሊሬ ደመወዝ ስሠራ ሳለሁ፣ በየቀኑ የሚመጡትን የእንግሊዝ መርከቦች የሚጭኑትን ጨው ዋጋ በወርቅ ለውጥ ብዙ ሚሊዮን የወር ገቢ ነበራቸው፤ የጨው ሀብትና ሥራም የምጽዋዕን የመሰለ የተከናወነ ሥራ በዓለም ዓይገኝም። የምጽዋዕ ጨውና ዓሳም ጣፋጭነቱና ማማሩም ልዩ በመሆኑ በብዙ ተመስግነዋል። ገጽ 46

በኢትዮጵያ መንግሥት ስም ያለልክ እጅግ ከፍ ባለው ዋጋ ከፈረንሣይ ሀገር አጭር ውጅግራ ጠበንጃ የገዙ ደጃዝማች ጌታቸው አባተ ከነጓደኞቻቸው ምጽዋዕ ወረዱና በታሪኩ የታወቀውን የግራርን ጨው አመጣጥና ካንድ ሽህ የበለጠውን ሠራተኛ ሲሠራ፣ ጨው ትልቅ ወሰን የሌለው ክምር ሲከመር፣ ከተከመረበትም በምድር ባቡር ተሞልቶ ወደ ባህር ዳር ባለው መጋዜን ውስጥ ገብቶ ሲያፈሰው፣ ከዚያም ጥበባዊው የእውቀት ሥራ ሽቅብ አውጥቶ ወደ ወፍጮ ራሱ እየወረወረ ፈጭቶ መልሶም ወደሌላው መጋዜን ያገባዋል፣ ከዚሁም መጋዜን አንስቶም ወደ ባህር ውስጥ ያሉትን መርከቦች በፍጥነት ሲሞላ በማየታቸው፤ የኢትዮጵያ መላክተኞች ይቅርና ሞላው የዓለም ሕዝብ አደነቀው፤ አመሰገነውም።" ገጽ 46

“በዚሁ ጊዜ የመንግሥት የምጽዋዕ ጕምሩክ ሹሞች የሆኑት በትምህርታቸውና በእውቀታቸው ከፍ ያሉት ግራዝማች ተድላ ጋብርና ፊተውራሪ ዘወልደማርያም ዘገርጊስ፣ ብላት ዘርኤ ግርሙ ዘጠና ሊሬ ደመወዝ ለየ አንዳንዳቸው ሲሠሩ እኔ “፪፻፶ ሊሬ ካልተሠጠኝ በ፪፻ ሊሬ ደመወዝ ምንም አልሠራም” ብየ በ፮ ወር ወደ አሥመራ እምቢ ብዬ ሥወጣ በማየታቸው በብዙ ተደነቁ። “የተስፋሚካኤል ትኩእ ዕድል ድንጋይ የሚፈልጥ ዕድል ነው” ሲሉ መሰከሩ።" ገጽ 46

"ይህንኑ የምጽዋዕን ጥበባዊ የጨው ፋብሪካ ሥራ የሠራ ዓይምነ የሚባል አዋቂ መሐንዲስ ብዙ ምስጋና ከኤርትራዊያን ይገባዋል።" ገጽ 46

አርበኛው ከምፅዋዕ አሥመራ ተቀይረው ስራ እንደጀመሩ፣ ኤርትራ ዉስጥም ድርቅ እንደገባ፣ እሳቸውም ከአስመራ ሞቃዲሾ በጂቡቲ በኩል እንደተመለሱ፣ ጂቡቲ ላይም ልጅ በየነ ህብትዝጊን እንዳገኙ፣ ኃይለሥላሴም ልጅ በየነን በአ/አ ስራ ሊቀጥሯቸው እንዳሰቡ፣ ልጅ በየነ ግን ወደ ሮማ መመለስና ቀጥሎም የትሪፓሊ የእርሻ ዋና ዲራክተ ሆኖ ከእንደነበር ይገልጻሉ። መብራህቱ (ሎሬንሶ) ታእዛዝም በአደን ሥራ እንደጀመረና የኢትዮጵያን አልጋወራሽ በብዙ ዓይነት ፓለቲካ እንደረዳቸው፣ በኤደን እንዳገኛቸው፣ አ/አ መጥቶ ሥራ እንዲዝ ቢጠይቁት ፈረንሣይ ሄዶ መማር እንደሚሻ እንደገለጠላቸው፣ እሳቸውም እንደፈቀዱት፣ እሱም ፓሪስ ሂዶ በየዓመቱ አንደኛ እየሆነ በሕግ ሊቅነት ምስክር እንደተቀበለ ይገልጻሉ

መቃድሾ ከተመለሱ በኋላ ያጋጠማቸውን ሁሉ በሶማልያ የነበሩ ኤርትራዉያን ለኢትዮጵያ መንግሥት በመስራታቸው ያጋጠማቸውን እንግልትና ሞትም ስም እየጠቀሱ እንዲሁም ስለ ልጅ ኢያሱ በቀጥዩ ክፍል ይዘከዝኩልናል! ይህ ሁሉ ደግሞ ያሁኑ ትውልድ ማለትም አዳሜ ገና ሳይወለድ በአንቀልባም እንኳ ገና ሳይታዘል የተፈጸመ ነው!!! :mrgreen:
1.Amesegen alehugn
2.degmo men emarebet alehugn.

Re: ተስፋሚካኤል ትኩእ (1892 – 1964)] - ወለዶና ክነቦ ዝግባእ መኽዘን ታሪኽ

Posted: 13 Jun 2019, 02:31
by Meleket
እኒህ የግዚያቸውን ፖለቲካ ኅሊናቸውን ሳይሸጡ የኖሩትና ያነበቡት አባት አርበኛ እኛም እንድናነበው ከሳቸውና ከግዚያቸው ፖለቲካም እንድንማር በማለም ነው ይህን ታሪክ ጥፈው የተውሉን። ከዚህ ታሪክ የሚማር ሰውም አሁን በግዚያችን የሚደረጉ የጥቁር ይሁን የነጭን የፖለቲካ የመከፋፈል ደባና ተንኰልን፣ ሆድ አደሮችና ለባዕድ ጉርሻ ኅሊናቸውንና ህዝባቸውን ሀገራቸውንም የሸጡ አንዳንድ “ሰው መሳይ በሸንጎዎች”ን በጥቅምና በሹመት አሞኝቶ አዳሜን እርስበርስ ለማባላት የሚጎነጎኑና የሚፈጸሙ መሰሪ ፖለቲካዊ አካሄዶችን ወዘተ ሕዝቡ በንቃት ጠንቅቆ በማንበብ ፈውሳቸውን ለማግኘትም መላ ለመፍጠር ያስችለዋል ተብሎ ይጠበቃል! :mrgreen:

“በዚያን ጊዜ የመቀሌ ጠቅላይ ገዥ ልዑል ራስ ጉግሣ አርአያ ዮሐንስ ነበሩና የመስቀልን ሠልፍ አየን፤ ስለ የሀገሩ አስተዳደርና የፖለቲካው አካሔድ አስደነቀን፤ ለሁለት በመከፈሉና ጣሊያንም እንደፈቀደው በኢትዮጵያም ለመሥራት በመቻሉ ሓዘን ያለልክ አሳዘነን። የጣሊያን መንግሥት በኢትዮጵያ ግዛት ውስጥ ገብቶ በዓድዋና በጎንደር፣ በደሴና በሐረር፣ በባሌ ቆንሱሎቹን ከማስቀመጡና የፈቀደውንም ሥራ ከመሥራቱ፣ ከማሠራቱም በላይ የሰላዎች አለቃ አድርጎ ‘ረ’ የተባለውን ካፒቴን ሳይቀር በመቀሌ አስቀምጦ ስለነበረ እኔ ከጣሊያን መንግሥት ከነመሣሪያየ ከድቼ መምጣቴ ተነገረውና አስጠራኝ። ገጽ 56

“እኔም ጥሪውን ጠላሁት፤ እምቢ ብዬ ከመቅረትም የሚለኝን ቃል መስማት የተሻለ መሆኑን መርጨ ኸጄ ተገናኘሁ፤ ካፒቴን ‘ረ’ም “ስለምን ከኤርትራ መንግሥት ከድተህ መጣህ” አለኝ። እኔም “የጣልያን መንግሥት ያለ ፍርድ ዕምናላዬ የተባለው የአዲሹም ተወልዳይን መሬት ከነሰብሉ ለደግራ ስለተሰጠብኝና እናንተም እውነተኛ ሠራተኛ ሰው ስለማትወዱ፣ በበለጠም ዋሾና አልጋ አንጣፊውን ብቻ ስለምታፈቅሩ ዕድል ፍለጋ ሠርቼ ለመብላት መጣሁ” ብዬ መለስሁለት። ገጽ 56

“አንተ አዲስ አበባ ካሉት ዘመዶችህ ተጻጽፈህ መምጣትክን ሰምተናል፤ መጐዳትክም እውነት ነውና ሁሉም እንዲሻሻልልህ፣ በቅሎና ወታደር፣ ስንቅም እሰጠለሁና ዓድዋ ሔደህ ከኮመንዳቶረ ፖለራ ጋር ስለ የዕርቁ ውል እንድትዋዋል እለምንሀአለሁና ምክርዬን ስማ” ብሎ በረጅሙ ከተናገረ በኋላ የጣሊያን መውጫ የሌለበት ወጥመድ እንዳበጀብኝ አስቀድሜ ስለተረዳሁት፤ “ከጣሊያን መንግሥት ጋር ምንጊዜም ቢሆን እርቅ የለንም፤ ዓድዋ መኸዴንና አለመኽዴን ግን መክሬ እስከ ፫ት ቀን መልሱን እሰጥህአለሁ” ስለው በብዙ አዘነ። የሚያደርገውም ነገር ጠፋው። እኔም ሰው እኔን ለማስገደል ገዝቶ ወይም ሌላ ዘዴ እንዳያመጣ ስላሰብሁ የቀጠሮው ቀን ሳይደርስ አምባ አላጄ ገባሁ።” ገጽ 56

“ከዚያም ደሴ፤ በደሴም የጣሊያን ቆንሱል ዶክቶር ብሪዪሊ መክዳቴን ሰምቶ ኑሮ ከመንግሥቱ በተቀበለው ፕሮግራም መሠረት የፈቀድከውን ሥራ በደሴ እንድትሠራ ተፈቅዶልካልና ሥራ ጀምር አለኝ። እኔም “ንግድ ዕነግዳለሁ እንጂ የጣሊያን ሠራተኛ መሆኔን በቃኝ” አልሁትና በብዙ ሲለምነኝ እምቢ ብዬ ወደ አዲስ አበባ ተነሳሁና ባ፭ት ቀን በፈረስ ግልብያ ገባሁ። ጣሊያኖች ግን በኔ ስም ሥልክ ማስተላለፋቸውን ምንም አላቋረጡም ነበር።” ገጽ 57

“እኔ አስቀድሜ አሥመራ ካለው የኢትዮጵያ ቆንሱል ጋር ወደ አዲስ አበባ መሄዴን በስውር ተነጋግረን ያለ ደረሰኝም ፭ሺህ ሊሬ አደራ ሰጥቼ ነበር የመጣሁና ወዲያው አዲስ አበባ ከመግባቴም የአሥመራ የኢትዮጵያ ቆንሱል ልጅ ሰይፉ ሚካኤል ገቡና ከልዑል ራስተፈሪ መኰንን ጋር አነጋግረው፣ አንድ በቅሎ ከነ መሣሪያውና መቶ ብር ሸልመው በደሴ የሚቋቋመው የጕምሩክ ዲረክተርነት ሾሙኝ። ከ፮ ወር በኋላም የጉምሩክ ዲሬክተርነት ሾሙኝ።” ገጽ 57

“እንደዚሁም ፊታውራሪ አረጋይ ለወሎ እንደራሴና ቀኝ ወንበር፣ አቶ ኃይለ ሹምዬ ነጋድራስነቱኑ፣ ኣዛዥ ፍቅረ ማርያም፣ ግራዝማች ከልክሌ ወርቁ ደጅ አጋፋሪ፣ ልጅ ክብረት ባንትይርጕ ግምጃ ቤት አድርገው ብዙ ሰው ሾሙና ራስ ከበደ መንገሻ አቲከም እንደተሻሩ በመጋቢት ወር ፲፱፻፲፰ ዓ.ም. ደሴ ተሹመን ስንገባ ዶክተር ብሪዪለ ዲመኑኮ፣ “ሥራ መሥራት አልፈቅድም፤ ገንዘብም አለኝ እና ንግድ ዕነግዳለሁ ብለዉኝ ነበር። መልካም ንግድ ነግደዋል”፤ ሲል ከፍ ያለ የመንግሥቱንና የራሱንም ኅዘን ገለጸልኝ።” ገጽ 57

ብርና ገበያም በኔ ሥልጣን ሥር ስለገባ የጣሊያን ቆንሱል ነፃነቱን ተገፈፈ። ዕቃው ተፈተሸ፤ ክብሩም በብዙ ተቀነሰ። ደፋሮቹ የኤርትራ ልጆችም በየቀኑ ፮ት ፰ት አሥርም እየሆኑ ከአሥመራ መምጣታቸውን አዘወተሩ፤ አልጋ ወራሽም የ፶ብር ስንቅ ላኩላቸው፤ ልጅ ክብረትም የተስፋሚካኤል ትኩእ ወገኖች መጡ ብለው ከመንግሥት አዛዥ ብዙ መስተንግዶ አዘው ድንኳን ተክለው በመቀበላቸው የጣሊያን ስብከት ፖለቲካ ፈረሰ፤ እነሱም ተጨነቁ፤ ከአሥመራ ከድተው ከመጡትም ሰዎች ውስጥ ልጅ አምባዬ ወንዳፍራሽን ቤቴ ደረስ አነጋጋሪውን አቶ ወደሚካኤልን ልኮ “የጣሊያን ቆንሱል ይፈልገዎታል” ሲል ላከ፤ በዚህም ጥሪው እኔ በብዙ ተናደድሁና አብረን ሔደን፤ ቆንሱሉም ተቀበለንና ልጅ አምባዬን እንዲህ አለው። “ከማረሻሎ ሮሲ የተበደሩት ፹ሺህ ሊሬ ዕዳ ይክፈሉት፤ አለዚያም አሥመራ ተመልሰው ይተሳሰቡ፤ የታሊያንም መንግሥት ስለ ረጅሙ፣ የብዙ ዓመታት መልካም አገልግለትዎ ርዳታ ያደግለዎታል” ብሎ ሲያቆላምጠው መልሱን እምሰጠው እኔ ነኝ እና ዝም በል አልሁት። “ለማረሻሎ ሮሲ ዕለቱን ፹ሺህ ክፈለው፣ ባትከፍለው አሰብ ትታሠራለህ፤ ያንተ ገንዘብ የ፶ ሺህ ሊሬ የተበደሩህ ግን በ፳ እና በ፶ ሊሬ ይክፈሉህ ብሎ የመንደፈራ ሀገረ ገዥ ዶክቶር ጋምባ የአድልዎ ግፈኛው ፍርድ ስለፈረደበት ተመልሶ ኤርትራ ለመታሠር አይሔድም” ብዬ ብመለስለት፣ “ልጅ እምባዬ መልስ ስጡኝ እርስዎ ስለምን ይከራከራሉ” አለኝ፤ እኔም “ታምዋልና እኔ ነኝ መልስ እምሰጥህ” አልኩና በብዙ ተከራከርን፤ “የትም ሀገር ቢሔዱ መከሰስዎን ይወቁት” ቢል እኛም “በየትም ክስህን ለመስማት ዝግጁ ነን” ብለነው በቁጣ ተለያየን። ልጅ እምባዬን ከልጅ ሰይፉ ጋር ወደ አዲስ አበባ ላኩትና ሥራ ጀመረ፥፡ ጣሊያንም ፎክሮ ቀረ።” ገጽ 58

“አልጋ ወራሽም በመላክም አቀባበል እየተቀበሉ፣ ሥራም እየሰጡ፣ ኤርትራዊያንን በክብር ሲያስተዳድሩ ሳለ፣ ያልሆኑትን ባልደረባ ስለሰጡዋቸው ብዙ መጉላላትንና ችግር ደረሰባቸው። ብዙዎቹም መካከል አቶ ጐፋር የሚባል ወጣት ቢሞት ዶክተር ሐነር በንዴት ተቃጥሎ መሞቱን መሰከረ። አዘነም። ይህም ክፉ ሥራ የሚሠሩ ሰዎች አንጐልና የሀገርም ፍቅር የሌላቸው፣ እነ ሆዱ አምላኩ የተባሉ በሁለት ካራ የሚበሉ፣ የጣሊያን ሰላዮችና ወገኖች የሆኑት ሰዎች የኤርትራውያን ባልደረቦች በመሆናቸው፣ ጣሊያን አደራ ስላላቸው ወገኖቻቸውንና ሀገራቸውን አሳልፈው ለጠላት ለመስጠት አላፈሩበትም ነበር።” ገጽ 58

የኤርትራ ሀገረ ገዥ ኮመንዳቶር ዶክቶር አይሁዳዊ ያዕቆብ ጋስፓሪኑ የረቀቀ የዲፕሎማሲ ፓለቲካ አንስቶ መኳንንት ሲለያይ፣ የማይጠፋውን እሳት ጫረ፤ ደሆችን መላክ ነጋዴ እያለ፣ ሽጉጥና ጠበንጃም እየሸለመ አታለለ። ንግሥት ዘውዲቱና ትግሬው ራስ ጉግሣ ወሌ ብጡል እንደገና እንዲጋቡ አሰበከ፤ ብዙ ተቀባዮችም አገኘ። ልዑል ራስ ጉግሣ አርአያ ዮሐንስና ልዑል ራስ ኃይሉ ተክለሃይማኖት ከራስ ጉግሣ ወሌ ጋር በክደቱ ተስማምተው ውሳኔም ወስነው ነበርና ራስ ጉግሣ ወሌ በ፲፱፻፳፪ በመጋቢት ወር በአንቺ ጦርነት ከየኢትዮጵያ አልጋ ወራሽ ከንጉሥ ተፈሪ ጋር ተዋግተው ሲሞቱ፣ ንግሥት ዘውዲቱ በተሰወረ መንገድ የራስ ጕግሣ ወሌ ለመሆናቸው ማህተማቸው ተገኝቶዋል።” ገጽ 58

"እኔም በዚህ ጊዜ ጣሊያንን በመጥላት የንጉሥ ወገን ሁኘ ከአዋቂው ዘመዳቸው ከክቡር ደጃዝማች እምሩ ጋር ሆነን ብዙ ሥራ ሠራን። ደጃዝማች እምሩም ደሴ ባይገኙ የንጕሥ ተፈሪ መኰንን ጦር በጡዋቱ ድል በሆነ ነበር። የትግሬና የጐጃም መሳፍንቶች ልዑል ራስ ጕግሣ አርአያና ልዑል ራስ ኃይሉ ተክለሃያምኖትም ራስ ጉግሣ ወሌ ሲሞቱ በአድማው ውስጥ ያልነበሩ መሰሉ።" ገጽ 58

"እኔም ከወሎ ጕምሩክ ዲረክተርነተ በ፲፱፻፳፫ ዓ.ም. በነሐሴ ወር በሽረት ወደ አዲስ አበባ ተጠራሁና በአቶ ገብረ እግዚአብሄር ደስታ ከንግድ ሚንስተር ዋና ዲረክተር መሻር ምክንያት መጕላላትና ከፍ ያለው ኅዘንም በሐዲሱ ዲረክተር ባቶ መኰንን ሀብተወልድ ደረሰብኝ።" ገጽ 58

“የበጌምድርና ጎንደር ገዥ ራስ ጕግሣ ወሌ ንግሥት ዘውዲቱ ሚኒልክ ዘንድ በብዙ የተወደዱ ስለነበሩ “ተራርቃችሁ እንደገና ብትጋቡ ወሰንና መሳይ የሌለው መንግሥት አቋቁማችሁ በደስታ ትኖራላችሁ” የሚል ሐሰተኛ የጠላቶች ስብከት ስለሰሙ ሁለቱም መታረቅን ፈቀዱ፤ ያለማቁረጥም ደብዳቤዎች መጻጻፍ አዘወተሩ። ስለዚህ ንግሥት ዘውዲቱ ምኒልክ ወረይሉ ያሉትን ዘመዶቼና የተወለድኩበትን ቤተ አያለሁና ድግስ ደግሱ ተብሎ የወረይሉ ሕዝብ በ፲፱፻፳፩ ዓ.ም. ታዘዘ። ራስ ጕግሣ ወሌም በሰው ከበጌምድር በፈረስ ጋልበው ወራይሉ እንዲመጡና ተገናኝተው ምክራቸውን ለመፈጸም፣ ሠራዊታቸውን ለመሰብሰብ፣ አልጋ ወራሽንም ለመጣል ቢያስቡም እግዚአብሄር ስላልፈቀደ ንግሥት ወረይሉ እንዳይሄዱ ተከለከሉ።” ገጽ 58

“ቢከለከሉም ጦር ሚኒስተር ፊታውራሪ ሙሉጌታም በራስ ጉግሣ ወሌ እንዲማረኩ፣ ጦር ሚኒስተር ከተማረኩ ልዑል የኢትዮጵያ መንግሥት አልጋ ወራሽ ጕግሣ ወሌም በሌላ የተሠወረ መንገድ አዲስ አበባ ገብተው ከንግሥት ዘውዲቱ ምኒልክ ጋር ሲነግሡ፣ የኢትዮጵያ መንግሥት አልጋ ወራሽ እንደ የልዑል ልጅ ኢያሱ አወጣጥ ወጥተው ይቀራሉ ብለውም ቢመክሩባቸው ይህንንም ብልሁ አልጋ ወራሽ አወቁትና ዘዴ አበጁ። በጌምድርን ለራስ ካሣ ኃይሉና ለደጃዝማች አያሌው ብሩ ሰጥቼዎታለሁ የሚል ቃል ስለነበራቸው ሁለቱም ንግሥትን ትተው፣ ከልብ ራስ ጕግሣ ወሌን “እኔ እሾማለሁ፣ እኔ እሾማለሁ” ሲሉ ወጕና ሲሞቱ በጌምድር ለራስ ካሣ ተሰጠ፤ ስለምን ራስ ተብዬ በጌምድር ሳይሰጡኝ ቀረ ብለው ደጃዝማች አያሌው ኅዘናችውን ገለጹልኝና ኅሳባቸውን ለወጡ።” ገጽ 59

“በዚህ የራስ ጕግሣ ወሌም ክዳት ራስ ጕግሣ አርአያም ስለነበሩበት፣ ከመቀሌ ወደ ራያ አልዘምትም ስላሉ እንዲዘምቱ ለማድረጋቸው አጐታቸው ደጃዝማች ወልደሥላሴ ወልደ ሚካኤልና ጸሐፌ ትእዛዝ አፈወርቅ ደጃዝማች ዓምዴን በ፫ት አርዮፕላኖች አድርገው ላኩዋቸውና ደሴ አረፉ። ለስምምነት የተላኩትም መልእክተኞች ጕም አላስኬድም አለን ብለው ምክንያት በማድረግ ሳይሄዱ ሰነበቱ፤ ይህን መንገድ ለማሰናከል ተንኮለኛው የጣሊያን ቆንሱል ጄኔራል ካርሎ እናራቶን ለይቱ(ለይቶ) ጀርመኖች ብቻ ወዳጅ መስሎ ግብዣ በያይነቱ አእምሮዋቸው እስክጠፋ ድረስ ጋበዛቸውና ውለው አደሩበት። በዚህ ጊዜ ማዬ የተባለው ከኢትዮጵያ ብዙ የገንዘብ ርዳታና ሽልማትም የተቀበለ የፈረንሣይ አረዮፕላን ነጂ የነሱን ያስናቀ የጀርመንን ትልቅ አርዮፕላን እንዲሠባበር ቦሎኑን ሲያወልቀው ዋለ፤ ከጄኔራል አናራቶኦን ጋራ በተመካከረው ተንኮለኛው መጥፎ ምክር መሠረት አድርጎ በኢትዮጵያ ሕዝብ የተመሰገነውን ጀርመናዊ አርዮፕላንን ቀን ሙሉ ብቻዉን ገብቶ ምስማሩን አወለቀው።” ገጽ 60

በማግሥቱ ወደ ራስ ጕግሣ መቀለ ለመሄድ እንግዶቹን ለመሸኘት ተሰበሰብን፤ ሁለቱ የፈረንሣዊ ተነስተው ሲበሩ የጀርመን አረዮፕላን ገና ከምድር ሳይነሳ እኔ ምንም ጥርጣሬ ሳይኖረኝ በወሎ የደጃዝማች እምሩ እንደራሴ በቀኛዝማች ፍቅረማርያምና ባቶ ኃይለ ሱሚዬ፣ ባቶ ስለሺ አባይነህ ፊት ቆሜ፣ “ይህ አረዮፕላን ድምጹን ለወጠ፤ አልነሳም አለ” ብዬ ስል፣ ከኛ ርቆ ያለው የጣሊያን መርዘኛው ቆንሱል አናራቶን ያለ አንዳች ፍራት “ምንም አልተበላሸም ደህና ነው” ብሎ መለሰ። ብልሁ አቶ ኃይለ ሹሚዮም በመጥፎ ሥራው ካርሎ አናራቶንን ፈጽመው ንግግሩን ስለማይቀበሉት ትኩር ብለው በክፉ ዓይን አዩት። ደጃዝማች ወልደሥላሴን ብቻ የያዘ የጀርመን አረዮጵላን ለጊዜው ተነሳና ፓርከና (ቦርከና ወንዝ) የንጕሥ ሚካኤል ድልድይ እልፍ ብሎ ወደቀ። ሰውም ሁሉ እንግዳ ነገር ሆኖበት ደነገጠ፤ በአረዮፕላን በግድ የተሳፈሩት ደጃዝማች ወልደሥላሴ ሳይታሠሩ (ያደጋ መከላከያ ቀበቶ ሳይታሠሩ) ስለነበረ ራሳቸው ተመተው ዐረፉ። ይበሩ የነበሩትም ሁለት አረዩፕላኖች ተመልሰው አረፉ። በማግስቱም የደጃዝማች ወልደሥላሴን ሬሳ ወደ አዲስ አበባ እንዲላክ በሥልክ ስለታዘዘና ጓደኞቻቸውም “በበቅሎ ነው እንጂ በአረዮፕላን አንመለስም” ስላሉ እኔ ከሬሳው ጋር አብሬ ለመሄድ ለጓደኞቼ ለነ አቶ ስለሺ በላይነህ ብነግራቸው “አርፈህ ተቀመጥ፤ የልጆች አባት ነህ” አሉኝ። በዚሁም በአረዮፕላን ከደሴ አዲስ አበባ አንመለስም ብለው በዶባ በበቅሎ በተመለሱት ደጃዝማች አምዴና ጸሐፊ ትእዛዝ አፈወርቅ ምክንያት፣ አቶ ወልደ ጻድቅ ጋሻን ሕይወት ያሳጣ ክርክርና ጠብ በጋዜጣም ተጽፎ ስነበረ በሰፊው መሰከረ፤ ይመሰክራልም።” ገጽ 60

"የመሰከረባቸውም ወደ መቀለ ወደ የትግሬ መስፍን አንሔድም በማለታቸው ብቻ ሳይሆን የደጃዝማች ወደሥላሴን ሬሣ በአረዮፕላን ይዘን አንመለስም በማለታቸው ጭምር በመሆኑም ነው የተሰደቡ። አዋቂው አቶ ወልደ ጻድቅ ጋሼም በኢትዮጵያ ፓለቲካ ስለተቆረቆሩ በቅጽበት ሕይወታቸውን ገበሩ። በራስ ጕግሣ ወሌም መሞት ጣሊያን በብዙ ኅዘን አዘነ። ኢትዮጵያን እርስ በእርስዋ አዋግቶ ሕዝብዋ ከተላለቀ በኋላ ወራሽ ሆኖ ለመግባት አይሁዳዊ ባሮነ ፍራንከትን ከኢትዮጵያ መኳንንት ጋር የማታለል ሐሰተኛውን ፖለቲካ ለመነጋገር ባለሙሉ ሥልጣን አድርጎ ላከ፤ ያለ ድካም ራስ ኃይሉ ተክለሃይማኖትን ገዝቶ ልጅ ኢያሱ ሚካኤልን በራስ ካሣ ኃይሉ እጅ ከታሠሩበት ፍቼ ለማስወጣት እንኳ ቻለ፤ ተመሰገነበትም።" ገጽ 61

በቀጣዩ ትረካቸው ከደሴ አዲስ አበባ ጕምሩክ ስለመዛወራቸው፣ ልዑል ልጅ ኢያሱ ሚካኤል ከፍቼ እሥር ቤት ስለመውጣቸው እየተረኩ አያይዘውም የግዜውን ቦለቲካ እንደልማዳቸው ያለምንም ይሉኝታና ማጎብደድ ይዘከዝኩታል። እኛም ይህን ታሪክ በቅጡ እያነበብን የዘመናችንን ፖለቲካም እናጤንበታለን!
:mrgreen:

Re: ተስፋሚካኤል ትኩእ (1892 – 1964)] - ወለዶና ክነቦ ዝግባእ መኽዘን ታሪኽ

Posted: 13 Jun 2019, 19:59
by Mesob
Thank you. where can I get the book?

Re: ተስፋሚካኤል ትኩእ (1892 – 1964)] - ወለዶና ክነቦ ዝግባእ መኽዘን ታሪኽ

Posted: 14 Jun 2019, 08:09
by Meleket
Mesob wrote:
13 Jun 2019, 19:59
Thank you. where can I get the book?
ወዳጃችን፡ መጸሓፉ እዚህ ይገኝ ይሆናል ብለን ተስፋ እናደርጋለን!
http://www.mereb.shop/rs/?prodet=true&p ... 283&vid=88

Re: ተስፋሚካኤል ትኩእ (1892 – 1964)] - ወለዶና ክነቦ ዝግባእ መኽዘን ታሪኽ

Posted: 14 Jun 2019, 08:24
by Meleket
እኒህ ቁርጠኝነትንና የዓላማ ጽናትን ካባቶቻቸውና ካያቶቻቸው ወርሰው ለተተኪ ትውልዶች ያወረሱት ቆፍጣናና ኩሩ ኤርትራዊ አባት አርበኛና መሰሎቻቸው፣ ኢትዮጵያ ውስጥ ስላጋጠማቸው አድልዎ፣ የጣሊያን ሎሌ ሆድአደር ባለስልጣኖች ተግባር፣ የሕግና የተስተካከለ ደንብ አስፈላጊነትን፣ የመጻፍና ሃሳብን የመግለጥ መብት ታፍኖ እንደነበረ እንዲሁም የልጅ ኢያሱን ከእስር ማምለጥና ተያያዥ ጉዳዮችን እንዲህ አድርገው በብስለት ይተነትኑልናል። የመጨረሻይቱ አረፍተነገራቸው ደግሞ ትደንቃለች! መልካም ንባብ! :lol:

“ከደሴ ወደ አዲስ አበባ ግምሩክ እንደተዛወኩ . . . በዚሁም ጊዜ ሁሉ ለመንግሥት ሠራተኞችና ለወታደራዊም አስተዳደር በቂና ትክክለኛ ሕግና ወይም ደንብ ስላልነበረ። ሕግና የተስተካከለ ደንብ ያለበት ሀገር ለመጣን ኤርትራዊያን ሁሉ ጨለማ መሰለን። ቢሆንም ኢትዮጵያን ረድተን ነፃ ለማውጣትና የጋራ ጥቅም ለማግኘት ብለን የቀና መንገድ ብናሳያቸውና አጼ ምኒልክም ካንዳንዱ መሸጥና መለወጥ ልምድና ችሎታም ካላቸው ሰዎች ጋር ሆነው ኤርትራን የመሰለ የኢትዮጵያ ሕይወት መሸጣቸውንም ብናስረዳቸው አይቀበሉንም ነበር። ስለዚህ የታወረና ከእውነት የራቀውን ክርክራቸውና ፈረንጅንም አጥብቀው በማፍቀራቸው ያለ ልክ ኅዘን ስናዝን ነበር።” ገጽ 62

አስተዳዳሪ ለሌለው ወርቅና ወሰን ለሌለው የኢትዮጵያ ሀብት ሰብስቦ ለመብላት የተጣደፈው የጣሊያን መንግሥት ብቻ ሳይሆን እንግሊዝና ፈረንሣይም ከመመኘት ምንም አላቋረጡም። በዚሁ መሳይ የሌለው ለ፫ት ለመካፈል በመፈለጋቸው ጀርመንም ጕልበት እንዳያበጁ ብሎ “ጥንታዊ የሆነውን የኢትዮጵያ መንግሥት ልትካፈሉት ዓይገባችሁም” ቢል አንተ ምን አገባህ ቢሉት እንግዲያውስ ፬ኛ አድርጕኝ ሲላቸው፤ ስላልፈቀዱለት ተናደደ፤ በኢትዮጵያ ላይ ለማፍሰስ ያሰቡትን ኅሳብ እግዚአብሄር በቸርነቱ እርስ በእርሳቸውን አጣልቶ በ፲፱፻፯ ዓ.ም. በኤውሮጳ ላይ እሳት አዘነበበትና ትልቁ ጦርነትም ብለው ሰየሙት። እግዚአብሔርም ለኢትዮጵያ የግል አምላክዋና የግል ንጕሠ ነገሥትዋ መሆኑን እነሱ ራሳቸው መሰከሩ። ይመሰክራሉም።” ገጽ 62

“ኅሳብ የሌላት፣ ኅዘንም የማይሰማት ቆንጆይቱ ለምለምዋ ኢትዮጵያ ወደረኛ የሌለው ሀብትና መሬትም ታቅፋ፣ ተኝታም ትኖራለችና ተረዳድተን በመደምሰስም እንብላት እያሉ የኢትዮጵያን ጥፋት የሚመኙ መንግሥታት ራሳቸው ሲጠፉ በመታየታቸው ያስደንቃል። በዚሁም ስስታም ፍላጎታቸው የኤውሮጳ ልጆች ተላለቁ፤ በከንቱም ተጣፉ። ለኛም ተንኮላቸውንና ፖለቲካቸውን አወረሱን፤ ኣናዝንላቸው አለን እንጂ አናዝንባቸውም።” ገጽ 63

እኔም ከወሎ የጕምሩክ ዲረክተርነቴ ወደ አዲስ አበባ ስዛወር ከመንግሥት የተሰጠኝን ማዕርግና ደመወዝ ይዤ ባለመዛወሬ ምክንያት የተነሳ በየጊዜው ወደ ንጉሠ ነገሥቱ አቤቱታ ለመጻፍ የተገደድሁ በመሆኔ፣ ስጽፍ ትልቅ ኅዘን ሲሰማኝ በትእግሥት ለማሳለፍ በብዙ ደከምኩ። ባልታገሥ ኑሮ ግን እንደ ዘመዴና ወዳጄ እንደ አቶ ወልደማርያም ተወልደ ዓዲሹም ሃብትት በችግርና በጉዳት ማስኜ ዕለቱን እሞት ነበር።” ገጽ 63

ዘመዶቻችንና ንብረታችንን ለጠላት ትተን ለመጣን ኤርትራዊያን ስለ መርዳትና የሀገር ፍቅራችንን ስለ ማጠንከር ለማጣላትና ለማለያየት አሳልፈውም ለመስጠት በመደሰታቸው ለኅዘናችን ወሰንና መሳይ አልነበረዉም። ይህና ይኸን የመሰለውን ሊታረም የማይቻለውን ጕድለት በማየታቸው የኢትዮጵያ ወጣቶች ሁሉ ቢናደዱና ትክን ድብንም ቢሉ ከሞት የሚያተርፋቸው አላገኙም፤ በታች በድንጋይ በላይ በብረታዊ ቀንበር ተጨቁነው በመዳመጣቸው የመረረውን ኅዘን ከመመገባቸው በቀር።” ገጽ 63

ስለዚህ ለጠላት ጋሻና ርዳታም በመሆን በማለያየት መጥፎ ክርክርና ኅሳብ በሚያቀርቡ ሰዎች ምክንያት ኢትዮጵያ ተደፈረች፤ ክብርዋም በየጊዜው ከቀን ወደ ቀን እየቀነሰ፣ የሰማዕቶችዋ ቁጥር እያነሰ፣ ወሰንዋም በመቆረሱ እየተቀነሰ በመሔዱ። ዋኖቹ የኢትዮጵያ ጠላቶች አቶ ስስትነትና፣ አቶ እኔብቻ ጌታልሁን፣ አቶ ድንቁርና ከበው ማስከበባቸውን በአዋቂዎች ዘንድ ተመሰከረባቸው፤ ቢመሰከርባቸውም አላፈሩበትም። በዚሁም እፍረተኛው መጥፎ ሥራቸው የኢትዮጵያ አንድነትና ስምምነት፣ የሰላምም ባላጋሮች የሚባል ስም ወጣላቸው። በኛም ህይወት ዘራቸው ሁሉ ፈጽሞ በመመተሩ አስደነቀን። ከዚህ በላይ የተጠቀሱት ሰዎች መልካምዋ ወተታሚቱ ኢትዮጵያ እናታቸው ዙሪያዋን በጠላቶችዋ ተከባ በመጨነቅ ስታለቅስ፣ በተቀደሰ መንፈስ ርህራሔ አልተደረገላትም፤ ከኅዘንዋም የሚያጥናና እውነተኛና ጉድለት የሌለበት ርዳታ አላገኘችም። ምክንያቱም ምን እንደሆነ ከሥሩ ለመጻፉም በቂ ድፍረት እንኳ ባይሆንልኝ፣ በኢትዮጵያ ማተሚያ ቤት ስለማይገኝለት (በኢትዮጵያ ውስጥ መታተም ስለማይችል) ለታደሉ ለመጭው ትውልድ ልጆች ትቸዋለሁ። ኢትዮጵያም ከተገዥነት መጥፎ ቀንበር ወደ የበላይ ገዥነት ሥልጣንና ክብር የምታገኝበት ጊዜ ቅርብ መሆኑ የማይጠረጠር ነው።” ገጽ 64

እኔም ባለመታደሌ ምክንያት ከመስከረም ፲፱፻፳፫ እስከ መጋቢት ፳፯ ቀን ፲፱፻፳፮ ዓ.ም. ድረስ በአዲስ አበባ ጕምሩክ ሥሠራ ሳለሁ በጣሊያን ሰላዎችና ረዳቶች ያሳለፍሁት ጭንቅና መከራም ሊቆጠር አይቻልም። ደሴ ሳለሁ እኸል ስለተወደደ እንዳልጠቀም ብለው በወር ፭ት ዳውላ የ፲፭ት ወር ፸፭ ዳውላ አንዱ ዳውላ በ ፲ብር ሂሳብ ፯፻፶ ብር እንዲሠጠኝ ከጽሕፈት ሚኒስቴር በጃንሆይ ቃል ለንግድ ሚኒስቴር ማዘዣ ያመጣሁበትን ፯፻፶ብር ንግድ ሚኒስትር ነጋ ድራስ ኃይለ ወልደ ሩፌ በነገ በነገ አስቀሩብኝ።” ገጽ 64

የንግድ ሚኒቴር ዋና ዲረክቴር አቶ መኰንን ሀብተ ወልድና የጽሕፈት ሚኒስቴር ዋና ዲረክተር ቀኛዝማች ተክለ ማርቆስ ሆነው በየ በኩላቸው ሲያሳድዱኝ ስለነበሩ መድረሻ አጣሁ። ሀገራቸውን አፍቃሪ፣ ቅን ፈራጅና እውነተኛው፣ በጠላቶች የማይደለሉ ራስ እምሩ ኃይለ ሥላሴ አባይነህ አሳሳቢነትም ጃንሆይ የጐጃም ዲራክተርነት ቢሾሙኝ እንኳን ራሳቸው ስለተሳሙ (በጠላት ስለተደለሉ ወይ በክፋት ስለተጠመቁ) አቶ መኰንንና ቀኛዝማች ተክለ ማርቆስ “ተስፋሚኢካኤል ትኩእ እኛ ሳንሰማ እንዴት ዲረክተርነት ይሾማል” ብለው ለጃንሆይ ቢያመለክቱ የቁጣ መልስ ስለሰጡዋቸው በበለጠ ተቃጠሉ።” ገጽ 64

ምንም እንኳ ሁሉም ራስ እምሩ በቀጥታ ከጃንሆይ አስፈቅደው የተወሰነልኝ ደመወዝና ስንቅም ቢሰጡኝ አቶ መኮንን ሀብተወልድና ቀኛዝማች ተክለ ማርቆስ ግን እስከ መጨረሻ ስንቅና ደመወዝም እንዳይሰጠኝ አንድላይ ተስማምተው ያልሆነ ምክንያትም እየሰጡ ለማጕላላቴ አልሆነላቸውም እንጂ ሙከራ ሞክረው ነበር። እኔና እኔን የመሰሉ ቤተሰዋቸውና ንብረታቸው ለሀገር ፍቅር ለውጠውና ለጠላታቸው ለጣሊያን ጥለው የመጡትን የኤርትራ ወጣቶች ጭንቅና ወሰን የሌለው መከራ ከኔው ስቃይና መጕላላት የበለጠ ችግርና ረሀብ መጐዳትም ነበረባቸው። እኛም ይኸን ፈተና ከጣሊያን ለጋሲዮን ይዘንብብን ኣንደነበረ ስለተገነዘብነው በትዕግሥት ለመቀበል ገና ያኔ አሥመራ ሳንነሳ ውሳኔ መወሰናችንን መካን ለማድረግ ለሚያደርጕት ትግል መከትን፤ መንፈሳችንንም ከፍ አድርገን በብርታትና በወንድነት ጠበቅናቸው።” ገጽ 65

“የኢትዮጵያ መንግሥት አልጋ ወራሽ ልዑል ልጅ ኢያሱ ሚካኤል በራስ ካሣ ኃይሉ እጅ ከታሠሩበት ፍቼ በማይበርደው የጣሊያን መንግሥት ቂምና በቀል በራስ ኃይሉ ተክለ ሀይማኖትም መስማማት አምልጠው ከፍቼ ወጡ። ከዚሁ የጠበቀና ፈጽሞ ለመውጣት የማይቻለው የሰላሌ ፍቼ ብርቱ እሥራት አምልጠው በግንደበረት ዓባይን ተቻግረው ጐጃም ሲገቡ፣ ለጣሊያ ሆኖ ይህን ሁሉ የሠራና ወጭም ከራሱ ያደረገ ባሮነ ፍራንከት በዚሁ ጊዜ አዲስ አበባ መጥቶ በመቀመጡ ስንደነቅ ሳለን ራስ ኃይሉን አሥመራ ለመውሰድ በስውር አንድ አረዩፕላን አዲስ አበባ አስመጣ። ቢጠየቅም ያልሆነውን ምክንያት ሰጠ። አረዩፕላኑም ቢወስዱበት ጦርነት እንዳያነሳ ተፈራና ተለቀቀለት። ወጣትም ሁሉ በብዙ አዘነ፤ ሕይወቱን ጠላ፤ እፍረትና ውርደት መሆኑንም ተሰማው። ሕዝቡም አንድ ኅሳብ ያለው ሕዝብ አለመሆኑን በጠላቶቹ መንግሥታት ዘንድ በጥብቅ ተገመተ።” ገጽ 65

“በልዑል ልጅ ኢያሱ ከፍቼ መወጣት በኢትዮጵያዊ ጥንታዊ ሕዝብ ዘንድ ትልቅ መለያየትና ሽብርም አመጣ፤ ኤውሮጵችም የኢትዮጵያን ስትገለባበጥና የእርስ በርስዋ ጦርነት ስትደመሰስ ገብተው ለመካፈልም ብዙ ተስፋ አደረጕ። በኛም ሞኝነት ሳቅ ሳቁ፤ ልጅ ኢያሱ ግን ጐጃም ከተቻገሩ በኋላ ከእሥር ቤት በመውጣታቸው ተጸጸቱ”” “በኔም ምክንያት የብዙ ሰዎች ደም ፈሰሰ፤ ለወደፊቱም በከንቱ እንዲፈስ አልፈቅስም፤ የነገሠዉም ንጕስው ወንድሜ ነው” ብለው በፈቃዳቸው ፊታውራሪ ገሰሰ በለውን ጠርተው እጃቸውን ሰጡ።” ገጽ 65

“ራስ ኃይሉም ልጅ ኢያሱ ሲወጡ ሌት ተቀን ብለው ጐጃም ለመቻገር ድፍረት ሳያገኙ ቀርተው አዲስ አበባ ተይዘው የሞት ፍርድ ተፈረደባቸው። በዚህ ጊዜ ከሴት ልጃቸው ከፊታውራሪ ኃይለ ሚካኤል የሚወለደው የትግሬ ወጣት ማሞ በራስ ኃይሉ ቤት ምትረየስ ደግኖ አላስገባም ብሎ ቢያስቸግር ዘመዱ የሆኑት ራስ ሥዩም መንገሻ በብዙ ማባበል ባያሲዙት ኖሮ አዲስ አበባን ሊያፋርሰው ነበር።” ገጽ 65

“ልጅ ኢያሱን የተከተሉና ያሳደሩ የተጻጻፉትም ሰዎች ሁሉ ተያዙ፤ ዋኖቹም ተገደሉ፤ አንዳንዶቹም ተገረፉ፤ተወረሱም። የልዑል ልጅ ኢያሱ ሚካኤል ጠባቂ የሆኑት ራስ ካሣ ኃይሉም በምስጢር ፬ት ቀን ራስ ሥዩም ቤት እንደተቀመጡ፣ ልዑል ራስ ሥዩም መንገሻ በልጅ ኢያሱ ትግሬ ማስቀመጣቸው ምክንያት ተግዘው (በግዞት) አዲስ አበባ ሲኖሩ ነበርና ከኣንጦጦ መተማ ድረስ የሚገዙትን ባለ ብዙ ሠራዊት ቢታሠሩ በጎንደርና በሰላሌ ያሉትን ልጆቻቸው ይከዱና ጦርነት ከሚያነሱብን ራስ ካሣን አለማሠር የተቻለው ነው ብለው ለጃንሆይ አስረድተው ነፃ አወጡዋቸው። ልዑል ራስ ካሣ ኃይሉም ልዑል ራስ ኃይሉ ልጅ ኢያሱን ከሰላሌ እሥር ቤት ለማስወጣት ጣሊያንና ራስ ኃይሉ የተዋዋሉት ውልና ምክር ስምምነት ውስጥ የለሁም ሲሉ ማሉ፤ ተግዘቱ፤ ንፁሕም ሁኑ። ደሐም በነገሩ ተደነቀ፤ አማ፤ አሳማ፤ ተራገመም። ራስ ኃይሉም ከሞት ወደ እሥራት ተለወጠላቸውና በደንድ ባህር ውስጥ ታሰሩ።” ገጽ 66

“የኢትዮጵያ ነጕሠ ነገሥት ኃይለ ሥላሴም ልዑል ልጅ ኢያሱ በእጃቸው አድርገው ጋራሙለታ በተባለው የሐረር ገደልማ ምሽግ ውስጥ በጥብቅ ታሥረው በ፬ት ሻምበሎች ተከበው ታሠሩ። ልዑል ልጅ ኢያሱን ከእሥር ቤት አሠወጥተው ኢትዮጵያን ስትደመሰስ ለማየት የሚጠባበቁትም በብዙ ሊያዝኑ ሳሉ፣ የጣሊያን መንግሥትም ሕዝብና መሳፍንትን ለማጣላት በዓድዋና በደሴ፣ በሐረርና በጎንደር፣ በጐጃምና በባሌ በአዲስ አበባም ቆንሱሎቹን አስቀመጠ። በድፍን ኢትዮጵያም ስብከቱን አስፋፋ፤ ገንዘቡንም በተነ። ንጉሥ ነገሥትም ወገኖቻቸውን ለማበረታታት ሲሉ ለልጃቸው ባል ለደጃዝማች ደስታ ዳምጠውና ለወንድማቸው ለደጃዝማች እምሩ ኃይለሥላሴ አባይነህ በሲዳማና በጐጃም ራስ ብለው ሾሙዋቸው፤ ጠላትና ወዳጃቸውን ለዩ።” ገጽ 66

“ ምንም እንኳ ንጕሠ ነገሥት አጼ ኃይለ ሥላሴ የኤርትራ ልጆች በሥራችን ታማኝነትና ትጋት፣ ችሎታም አጥብቀው ቢያምኑንና ቢያቀቡን ባለሥልጣኖቻቸው ቅናት በመቅናታቸውና ጣሊያንን ለመደገፍ ሲሉ “ሀገራቸውን አጥፍተው ሀገራችንን ለማጥፋት የመጡ ኤርትራዊያን” እያሉ ስለሚሰድቡን አዘንንላቸው እንጂ አላዘንባቸውም። እኔም እንደዚህ በመሰለ ሁናቴ ስድብ ስሰደብና “ብትፈልግ የሰጠነህን ሥራ ሥራ፣ ባትፈልግ የፈቅድህበት ለመሔድ ትችላለህ” እያሉ እነ አቶ መኰንን ሀብተወልድ በኛ በኤርትራ ሕዝብ አለማቋረጥ በመሳደባቸውና ማላገጣቸው ምን ጊዜም ሊረሳ የማይቻል ስድብ ነው።” ገጽ 67

“ይህነኑ ስድብና ችግር ለተሸከሙ ሰዎች ሁሉ ከፍ ያለ ምስጋና ይገባቸዋል። ይመሰገናሉ። ኤርትራዊያንንም መጥላታቸው እውነትን በመጥላታቸው ብቻ ነው።” ገጽ 67

እኒህ ኩሩ አርበኛ “በአዲስ አበባ ንግድ መቋቋሙን” የሚል ርእስ የሰጡት ትረካቸውን በቀጣይ እንኮመኩማለን! ጣልያንም በድንኳን ስም በአጋሰስ አስጭኖ ወደ ጎንደር ይወስዳቸው የነበሩ ነገሮች ምን ሆነው እንደተገኙም አርበኛው አፍረጥርጠው ይገልጹልናል።
:mrgreen:

Re: ተስፋሚካኤል ትኩእ (1892 – 1964)] - ወለዶና ክነቦ ዝግባእ መኽዘን ታሪኽ

Posted: 15 Jun 2019, 04:46
by Meleket
አባት አርበኛዉ ስለ የግዚያቸዉ የንግድ ሁኔታ፣ ከፊተዉራሪ አረጋይ እንዲሁም ከልጃቸዉ ከባላምባራስ በኋላም ራስ አበበ አረጋይ ጋር የነበራቸዉን ግንኙነት፣ በተለይም ሊመጣ ስለሚችለው የጣሊያን ወረራ ስለመግለጣቸው፣ እንዲሁም “ልምድ በሌለዉ በባዶ አንጐል የሚነጫነጩ” ብለው በገለጿቸዉ በአቶ መኰንን ሀብተወልድ አማካኝነት በሳቸውና በኤርትራዊያን ላይ ይደረግ የነበረዉን ወደር የሌለው የስነልቦና ትንኮሳና ጥቃትን ባጭሩ ይገልጡልናል። መልካም ንባብ!

በአዋቂው ሊቅ ነጋድራስ ገብረ ሕይወት ባይከዳኝ ተቋቁሞ፣ እሳቸው መሰላቸው የትግሬ ተወላጅ አቶ ገብረ እግዚአብሄር (ፍራንሱዋ) ደስታን እስክተኩ ድረስ የኢትዮጵያ ንግድ ማንም ሰው መጫወቻና ቤት መሥሪያ፣ የነ መሐመድ አሊም መከበሪያ ሆኖ በመቅረቱ በነ ሙሴ ያዕቆብ መዝገብ ከ፯፻ ሺህ ብር የዓመት ገቢ አልነበረም። በወጣቱ አቶ ገብረ እግዚአብሄር ደስታ ጊዜ ግን ካዲስ አበባ ጕምሩክ ብቻ ያመት ገቢ ካንድ ሚሊዮን እስከ ፭ሚሊዮን ብር በላይ በመግባቱ ሕዝቡ በብዙ ተደነቀ፤ አቶ ገብረ እግዚአብሄርን አመሰገነ። በአዲስ አበባ የንግድ ሚኒስቴር ተቋቋመ። በሌሎቹም አውራጆች ሥራው በደንብ ለማሠማራት ሲጀመር፣ ሻለቆቹ በርና(ኬላና) ገበያ መንግሥት ከወሰደብን አሽከሮቻችንን በምን እናሳድራቸዋለን ብለው በብዙ አጕራመረሙ፤ ተማከሩ፤ ለማስቀረት ግን አልቻሉም።" ገጽ 68

ፊታውራሪ አረጋይ ለሥራ ታዘው አኵሱም ሄደው ሳለ የጣሊያን መንግሥት ቆንሱል ኢትዮጵያን ለማፍረስ ሲል መድፎቹን በድንኳን ስም ወደ ጎንደር ለመውሰድ በአጋሰስ ጭኖ አኵሱም እንደ ደረሰ ፊታውራሪ አረጋይ በግድ ሲፈትሹት ድንኳን ብሎ በማስመስለ ያስመጣውን መድፎች ሆነው ስለተገኙ ተያዙ። በዚሁ የፊታውራሪ አረጋይ ብርታትና ንቃት ጣሊያን በብዙ ተዋረደ፤ አዘነ። ስለምን አወቁብኝ ብሎም ፊታውራሪ አረጋይ ከትግሬ መሬት ተሽረው ካልተነሱ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር ወዳጅነታችን ቀርቶ ጦርነት እናነሳለን አላቸው። ባለሥልጣኖቹ ጥቅማቸውን ትተው ጣሊያንን ደስ ለማሰኘት የተያዘውን መድፍ ወደ አሥመራ እንዲመለስ ለቅቀው ፊታውራሪ አረጋይን ሺረው ተራረቁት፤ እሱ እንዳለውም ፈጸሙለት፤ እኛ ኤርትራዊያን ግን በዚሁ መሻርና መሣርያ ነፃ መልቀቅ በብዙ ስናዝን ነበር።" ገጽ 68

"እኔ ከሀገሬ ከኤርትራ በሀገር ፍቅር ሰንሰለት ተጐትቼ አዲስ አበባ እንደወጣሁ ልዑል አልጋ ወራሽ ተፈሪ መኰንን ፊታውራሪ አረጋይን የወሎ እንደራሴ አድርገው በ፲፱፻፲፰ ዓ.ም. ሲልኩዋቸው እኔንም በጕምሩክ ዲራክተር አድርገው ደሴ ስለላኩኝ በዚሁ በብርቱ በአኵሱም የሠሩት ሥራቸው ያለ ልክ ተፋቀርን።" ገጽ 68

በዚሁም ፍቅር ምክንያት ከልጃቸው ከባላምባራስ አበበ ከዛሬው ራስ አበበ አረጋይ ጋርም በብዙ ስለተፋቀርን የጣሊያን መንግሥት በኢትዮጵያ መንግሥት ላይ ብርቱ ጦርነት ማንሳቱንና እኛ ባለ መሰናዳታችን ድል ሆነን መሸሻ ፈጽመን ማጣታችንን ሳስረዳቸው፣ እንኳንስ ባላምባራስ አበበ አረጋይ ይቅርና በአዲስ አበባ ጕምሩክ የሚሠሩትም አማሮችና ኤርትራዊያንም ጭምር ምንም አላመኑም ነበር። አንዳንዶቹም “ጣሊያን ሲያብል ከዓድዋ ጦርነት እስከ ዛሬ ድረስ መጣሁ እያለ ይፎክራል፤ አይመጣም፤ ቢመጣም እንደዱባ በጕራዴ እንቀረድደዋለን” እያሉም መሰረት የሌለው መልስ ይሰጡኝ ነበር። እንባዬ ዝም ብሎ እስኪንጠበጠብ በኅዘን፣ ተከብቤ ሳለቅስ ዋዛ ፈዛዛ ይመስላቸው የነበሩት ሰዎች ሁሉ፣ ጣሊያን በሚያዝያ ፳፯ ቀን ፲፱፻፳፰ ዓ.ም. አዲስ አበባ ገብቶ ፲፱፻፴፫ ዓ.ም. ሚያዝያ ፳፯ ቀን በእግዚአብሄር ተአምራታዊ ኃይል ወርደትና እፍረት ለብሶ ከኢትዮጵያ ሲወጣ እነዚያ ሰዎች በግልጽ ተናዘዙልኝ።" ገጽ 69

የኤርትራም ልጆች ባልደረባ የነበሩ የንግድ ሚኒስትር ዋና ዲረክተር እውነተኛው ፍርድና ቅን እውቀት፣ መልካም አስተዳደርና ልምድ የሌላቸው በባዶ አንጐል መነጫነጭ ተግባራቸው የሆኑ አቶ መኰንን ሀብተወልድ ጣሊያንን ደስ ለማሰኘት ኤርትራዊያንን ጐዱን፤ አበሳጩን፤ በማጉላላትና ስቃይ በመሰቀየታቸውም ብዛት ሁላችን ኤርትራዊያን በኅዘን ተቃጥለን፣ ሁላችን ታመምን፤ ችግርም ጋለበብን። በዚሁም ህመሜ ምክንያት በብዙ ትግል ከዶክቶር ሐነር የአንድ ወር ስንብት (ፈቃድ) ተቀብዬ ከወዳጄ ከአቶ ዮሐንስ አሊና ከልጅ ዓባይ ጋር አምቦ ለጠበል ወረድን። ገጽ 69

እኒህ ቆፍጣና ቀብራራና ኩሩ አባት የነጻነት ታጋይ አምቦ ለጠበል ብለው በሄዱበት፣ አጼ ኃይለሥላሴም በአጋጣሚ ወደ አምቦ ጎራ ብለው ስለነበር፣ አርበኛው ከአጼው ጋር ያደረጉትን ረዢም የፖለቲካና የዲፕሎማሲ ቆይታ ይዘረዝሩልናን። ቀኛዝማች ተክለማርቆስ የአርበኛዉን ደብዳቤዎች ወደ አጼው እንዳይደርሱ ጠልፈዉ ያስቀሯቸዉ እንደነበር፣ ደብዳቤያቸው ወደ ጣሊያን ሊጋሲዮን እንዳይመራባችዉ ሥጋት እንደነበራቸዉ፣ ጣሊያን ኢትዮጵያን ለመዉረር ሊከተላቸው የሚችለዉን መንገዶች ሁሉ ከጦርነቱ በፊት አስቀድመዉ ፍንትዉ አድርገዉ ለአጤዉ በመተንተን የጣሊያንን የጥቃት መንገዶች ማምኸኛ ስልቶችንም መጠቆም ብቻ ሳይሆን አጤዉንም የአስተዳደር አካሄዳቸዉን በሚገባ እንዲያስተካክሉ ያለ አንዳች ስጋትና ይሉኝታ ኃያለቃልም እየጨመሩ እንደመከሯቸዉ በቀጣይ ክፍል እንቃኛለን!
:mrgreen:

Re: ተስፋሚካኤል ትኩእ (1892 – 1964)] - ወለዶና ክነቦ ዝግባእ መኽዘን ታሪኽ

Posted: 17 Jun 2019, 08:54
by Meleket
ከዚያኛው ትውልድ አናብስት አንዱ ኣባት አርበኛው ተስፋሚካኤል ትኩእ ትረካቸውን ይቀጥላሉ፣ ከአጤው ጋር በአንቦ ያደረጉት ውይይት ባጭሩ ይህን ይመስላል። ወራሪዉን ጣልያን ለመመከት መካሄድ ስለነበረበት አይቀሬ ጦርነት በኢትዮጵያ በኩል መደረግ ስለሚገባው ቅድመ ዝግጅት፣ አንዳንድ ባለሥልጣኖች ከጣሊያን ጕቦ እየተቀበሉ መሬት ይሸጡ እንደነበርም ጠቆም አድርገውናል። እንዲህ አድርገውም ይገልጡታል “የዚያን ሀገር ባላባት ፊታውራሪ ዳዲ ተረ ሉክም ቢሆን የኛ ነው፤ እንጂ ጣሊያን መሬተ የላትም እያሉ ሲሉ በጕቦ የታወሩት ሰዎች ዝም ብለው ስላስወደሱት፣ ዛሬም በጣሊያን እጅ ነው ያለው፤”። የጀግኖቹ የራስ ሉልሰገድና የልጃቸው የደጃዝማች አሰፋ እጣ ፈንታ ይገልጡልናል በተጨማሪም የትልቁ ጦርነትን ጀርመን እንዴት እንደጀመረውም ከኢትዮጵያ ጋር አያይዘው ያቀርቡልናል። ትክክለኞቹ ኤርትራዊያን አናብስት አባት አርበኞች ለተተኪው ትውልድ የሚያወርሱት ሃሳብን በሃሳብ የመሞገትና በውይይት ሃሳብን የመግለጥ ጥበብና ባህርይም በዛሬው ትረካቸው ተካቷል። :mrgreen:

“ለዕድሌ ጃንሆይ አጼ ኃይለሥላሴ አምቦ መጡ። ህዳር ፲፱ ቀን ፲፱፻፳፮ ዓ.ም. ሰኞ ጡዋት ቤተ ክርስቲያኑን እያስከደኑ እኔን በቀኛዝማች በልሁ አስጠሩኝና በወርካ ሥር ባጌጠ ምንጣፍ ተነጥፎ በወንበር ተቀምጠው ተናገር አሉኝ። ግርማዊ ሆይ ፫ት ደብዳቤዎች ጽፌለዎት ነበር፤ ለእነዚህም በብዙ ድካም ለተጻፉ፣ መዝገብ ሆነው ለተጠረዙት ደብዳቤዎች “መልካም ነው፤ ወይም መጥፎ ነው፤” የሚል መልስ ባለማግኜቴ አዝናለሁ። ለወደፊቱም ተበራትቼ ለመሥራት አልችልም ስላቸው” ለማን ሰጠኸው” አሉኝ፤ “ለቀኛዝማች ተክለ ማርቆስ” ብዬ መለስሁላቸው። ዝም አሉና ሲያስቡ ከቆዩ በኋላ “ይሆናል” አሉኝ። እኔም አጥብቄ መጠየቄ ጃንሆይ ሳያዩዋቸው ወደ ጣልሊያን ለጋሲዮን እንዳይተላለፉ ጠረጠርሁ።” ገጽ 70

“የእነዚህም በኔ የተጻፉት መዝገቦች አርእስቶች በቃሌ ለግርማዊነትዎ ለማስረዳት እችላለሁ ስላቸው መልካም ነው ተናገር አሉኝ። ፩ኛ መቃድሾና ወጋዴን ሐረርና ጂማ ፪ኛ አሰብና ደሴ መቅደላ ፫ኛ አሥመራ ሰቲት ጎንደር ደብረማርቆስ፤ አሥመራ መረብ ዓድዋ መቐለ።” ገጽ 70

አሥመራ ዓዲቀይህ ዓዲግራት መቀለ መንገድ ይዞ ጣሊያን ለጦርነት ይመጣል። ስለዚህ ግርማዊነትዎ በድፍን ኢትዮጵያ ዙሪያ ሥልክ መዘርጋትና ራዲዮም በ፬ት ማዕዘን ማቆም፣ ሥልኩ የዕለት ዕለቱን ደስታና ኅዘን እየቀሰመ ለራዲዮን እንዲያቀብለውና ያዲስ አበባም ራዲዮ ተቀብሎ በየሰዓቱ እንደመስተዋት ሲያቀርብለዎት ለሁሉም በቅጽበት መልስ መስጠት ይችልላ። ጦረኛው ሕዝብዎም በረሐብና በወሃ ጥም እንዳይፈታ የወሃ ኩሬ ማጠራቀሚያ ጐድጓድ ማበጀት፣ የእኸል ጐተራ መሥራት፣ በየቦታው ወፍጮ አሠርቶ እኸሉን እያስፈጩ ለወታደር በመቁነን መስጠት ያስፈልጋል። ወታደርም ምሽግ ከተመሸገለትና ያለ ዋጋ ወሃና ዶቄት ከመንግሥት በየቀኑ ጭብጦ የሚሆን ዶቄት በደንብ ከተቀበለ የኢትዮጵያ ልጅ በጦርነት ኣይፈታም። ይህንን ካልተደረገለት ግን ካለ ሥንቅና መሣሪያ ረጅም ጊዜ ለመከላከል ያዳግታል።” ገጽ 70

“ግርማዊ ሆይ ከዚህ ቀደምና ዛሬም ሐኪምና የኦባ መድኃኒት ስንቅም ሳይኖረው በወጋዲነ በረሐ ርጥብ ሥጋ እየበላ የወይብ ሸበሊና የገናለን ወንዝ እየጠጣ፣ ብነዳድና በግር የሞተዉን የሚሞተው ነጭ ለባሽ ወታደር ቁጥር የለውም። ስለዚህ ለኔ እንደሚመስለኝ በወጋዴን ወይብ ሸበሊና በገናለ ፈሳሾች በሠልፍ የሰለጠኑ፣ ኮት የለበሱ መድኃኒትና ሐኪም የያዙ ምሽግ እየመሸጕ፣ በመቁነና በንጽህና ተጠብቀው የሚኖሩ ወታደሮች ካልተላኩ በነጭ ለባሽ ጣሊያንን ለመዋጋት ዓይቻልም። ስለዚህ በየጐተራው ተሰብስቦ ያለውን እኸል በያይነቱና ቡና፣ በርበሬ ለወጋዴን ዘማች ስንቅ መስጠት፣ ተራሮችና ሸሎቆቹም በጥብቅ ምሽግ ማስመሸግና ማስጠበቅም አስፈላጊም፣ ጠቃሚም ነው፤ ብዬ ስላቸው አዎ ፊታውራሪ ሺፈራው ባልቻን ልከናል መለሱልኝ።” ገጽ 71

“በዚህ ጊዜ የኔ አእምሮ ተለዋወጠና በድፍረት ቃል “እንኳንስ አንድ ፊታውራሪ ሺፈራው ይቅርና ፲ ሺፈራው ቢልኩም የጣሊያን ወታደር ሊመልሱት ዓይችሉም፤ ወታደሮችዎም በጠቅላላው የሰባችዋን የወጋዴን ላምና በግ ከማረድና ባላባቶቹን በከንቱ እያሠሩ ከማባረር በቀር ለማስተዳደር የሚሠሩት ሥራ የላቸውም። ላብነት ከብዙ ጊዜ ጀምሮ ለኢትዮጵያ ረዳት ሆኖ ጣሊያንን ሲከላከል የነበረውን አሎል ዲለ የሚባለውን ባላባት ደጃዝማች ገብረማርያም ዋስጥራ ብለው እያሠሩ እየፈቱ ስላስቸገሩት ተመሮ ወደ ጠላቱ ወደ ጣሊያን ገባ ማለትን እሰማለሁ። እኔ ግን ከደጃዝማች ገብረማርያም ጋር እንኳንስ ጥል መጣላቴ ይቅርና እውቀት እንኳ ምንም የለንም ስላቸው “አምናለሁ” ሲሉ መልስ ስለመለሱልኝ ፍራት ከመፍራቴ ተጥናናሁኝ።” ገጽ 71

የጣሊያን መንግሥት እንደ እኛ ኢትዮጵያዉያኖች ተገዥዎቹን ዋስ ጥራ በእግር ብረት ታሠር እያለ አስጨንቆና አስጠብቦ ግብር አያስገብራቸውምይልቁንስ ለሹሞቹ ቡንና ሻሂ፣ ስኳር፣ ሰይፍና ጌጠኛው (ቱርባንቲ) መጠምጠሚያ ይሸልማቸዋል፥ አጥብቆ እስክይዛቸው ድረስ ለምሽቶቻቸው ሳይቀር የሐር ጐፍታና ሹቶም ይሰጣቸዋል፤ ብዬ ስላቸው ግርማዊ ጃንሆይ በብዙ ተከዙ። ግርማዊ ሆይ አጼ ምኒልክ በትልቁ ስሕተታቸው ብዛት ከመቃድሾ ወዲህ ፵ ኪሎ ሜትር ላይ የሚገኘውን በልአድ የተባለ የራስ ሉልሰገድ ምሽግ በሽረት በማለቀቃቸውና እንደገናም ልጃቸው ደጃዝማች አሰፋ ሉል ሰገድንም ካፒተን ደ ጆባኒና ካፒተን ሞሊናሪ ከነ ጦራቸው ባይደዋ ላይ ድል መተው ቢደመስሱዋቸው፣ አጼ ምኒልክ ስለመሾምና መሸለም ፈንታ ጀግናው ደጃዝማች አሰፋ ከነ አባታቸው ጭምር፣ ከራስ ሉል ሰገድ ጭምር ከሁሉ በባሰ ስሕተታቸው ብዛት በወኽኒ ቤት ማሠራቸውን ነው።” ገጽ 72

"አጼ ምኒልክ የጣሊያንን መንግሥት ደስ ለማሰኘት ደጃዝማች አሰፋ፣ ራስ ሉልሰገድን ስላሠሩዋቸው፣ ለሀገራቸውና ለመንግሥታቸው ተዋግተው ድል ያደረጕትን ጀግኖች ካሠሩዋቸው እኛ ምን አደከመን ብለው፣ የሻለቆቹ ሁሉ በጣሊያን ቃልና ክርክር ሀገረ ገዥ የሚሻርና የሚታሠር ከሆነ እኛ ምን አገባን ብለው፣ ጣሊያንን ወዳጅ አድርገው ጕቦ እየበሉ በስውር ለጠላታቸው ለጣሊያን የለቀቁለት ሀገሮች ቁጥር የላቸውም። በዚሁም በተሰወረ ወዳጅነታቸው ልዩ ደመወዝ ከጠላታቸው ከጣሊያን መንግሥት ይበላሉ። ከብዙዎቹ መካከል የተሸጡትም ሀገሮች ባይደዋ፣ ሉክ ዶሎ፣ ባሮናና ነጭ ዓባይ፣ መለይካልና ሪሰሪስ ተሰነይና ዑምሐጀር ስለሆኑ፣ የሸጡትን ሰዎች ዝርዝር ማግኘት የግርማዊነትዎ ፈንታ ነው ስላቸው የበለጠ ኅዘን አዘኑ፤ ያንዳንዳቸውን ሰዎች ስም አነሱልኝ ና በነገሩ በብዙ ተደነቁ።” ገጽ 72

“ጃንሆይም “ከመቃድሾ ዶሎ ድረስ ምን ያህል ቀን በእግር ያሥኬዳል” ሲሉ ጠየቁኝ። ከመቃድሾ ዋንለወን ፫ት፣ ከዋንለወን ቡራካባ ፬፣ ከቡራካባ ባይደዋ ፬፣ ከባይደዋ ሉክ ፬፣ ካሉከ ዶሎ ድረስ ፬ቀን በድምሩ ፲፱ ይሆናል። ለወደፊቱ የሚሆነው የጣሊያንና የኢትዮጵያ ጦርነት ከመቃድሾ ወጋዴን፣ ሐረርና ጂማ በአየርና በታንክ፣ በእግረኛም ወታደር ያለብሳታል፤ እኛም ከጣልያን ጋር ስንዋጋ ባስተዳደርና በግብር የተመረረውም ሕዝብ ባይወጋን ዓይረዳንም፤ ስለዚህ መግብያ ፈጽመን አናገኝም። በልጅ ኢያሱም ጊዜ የጣሊያን መንግሥት ከዶሎ ለዎ ወደ ሉክ እንዲመለስ ቢያስገድዱትም ጣሊያን በካፒተን ቹስተርኒ የሚታዘዝ ኮሚሲዮን ልኮ ከኢትዮጵያ መንግሥት የተላኩትን ሰዎች ፲ሺህ ጕቦ አዲስ አበባ ያሉት ዘመዶቻቸው ደርሶናል ብለው እስክልኩላቸው ድረስ ዝም ብለው ሲተኙ፣ ጣሊያን ዝም ብላ ካርታ አነሳቹ፤ የዚያን ሀገር ባላባት ፊታውራሪ ዳዲ ተረ ሉክም ቢሆን የኛ ነው፤ እንጂ ጣሊያን መሬተ የላትም እያሉ ሲሉ በጕቦ የታወሩት ሰዎች ዝም ብለው ስላስወደሱት፣ ዛሬም በጣሊያን እጅ ነው ያለው፤ ልጅ ኢያሱም በአጼ ምኒልክ ስሕተት ሁሉ ምንም ሊከራከሩ አልቻሉም ስላቸው። በዚህ ጊዜ አጼ ኃይለሥላሴ በኅሳብ ተከበቡ፤ ቃሌንም በብዙ ደስታ ተቀበሉት።" ገጽ 73

“ጦርነቱም እስከ ዛሬ የቆየበት ምክንያት ሌላ አልነበረም። የእንግሊዝ መንግሥት ከጎንደር ጻና በባህርና በጉጃምና የለቀምት አጋማሽ ፣ ጂማና ሲዳማን በሙሉ እንዲሠጠውና ከግብፅ በሱዳን በጣና፣ ኢትዮጵያን በምድር ባቡር አቋርጦ በቦሮና ከኪሲማዮ ባህር ጋር አገናኝቶ፣ በህንድ ውቅያኖስ ካሉት መርከቦቹ ጋር አገናኝቶ፣ ኢትዮጵያንና ህንድን አንድ አድርጎ ለመግዛት፣ ሕያው በሆነው ክርክር ከጣሊያንና ከፈረንሣይ መንግሥታት ጋር ያለ መስማማቱን ጠብ አንስቶ በመጣላቱ ምክንያት ነው የጠቀመን እንጂ እንግሊዝና ፈረንሣይ ጣሊያን ፫ቱ መንግሥታት ለመካፈል ቢስማሙ ኑሮ ኢትዮጵያ እስከ ዛሬ በነፃነት ባልቆየች ነበር። ትልቁ ጦርነትም ጀርመን ከኤውሮጳ ያነሳው ኢትዮጵያን አትካፈልዋት እምቢ ብላችሁ ከተካፈላችኋት ግን እኔን ፬ኛ አድርጉኝ ሲላቸው እነሱም መካፈላችንን አንለቅም አንተንም አናስገባም ስላሉት ነው በእውስትሪያ መስፍን መገደል ሰበብ አድርጎ ጦርነት ያነሳባቸው።” ገጽ 73

“የጂማ ባላባቶችም የከረን ሰይድ ጀዕፈርን ኅሳብ በመቀበል ጣሊያንን ስለመረጡ ምንም እንኳ እንግሊዝ በብዙ ቢያባብላቸውም አልፈቀዱለትም ስለነበረ ነው።” ገጽ 73

“፪ኛ አሰብና ደሴ መቅደላ። የኢትዮጵያ መንግሥት ከጣሊያን መንግሥት ጋር ከአሰብ እስከ ደሴ ድረስ መንገድ ጠርጎ ንግድ እንዲያስፋፋና የአሰብን በር ለኢትዮጵያ እንዲሠጥ የኢትዮጵያ መንግሥት ይህን ውል ፈቅዶ መዋዋሉ ጥፋት ነው። ስለምን? የጣሊያን መንግሥት በቀን ብዛት ከብዙ ጊዜ በኋላ የኢትዮጵያን በረኞች በገንዘብ አታልሎ ከአሰብ ደሴ በመቅደላ ምሽግ መድፎቹን ተክሎ ከመቅደላ ማይጨውንና በጌምድር፣ ጐጃምና ደብረብርሃን በመድፎቹ ደብድቦ የኢትዮጵያን እምብርት በሐሰተኛው ውል ስም አታልሎ ከሚይዛት ይልቅ፣ የወሎን አውራጃ ስጦታ ሰጥተንሐል በማለት የተቻለ ነው ብዬ ለጃንሆይ ስላቸው፣ አንተ በወሎ ለራስ እምሩና ለአቶ ኃይሉ ሹምዬ በፖለቲካና በሥራም መርዳትክን በሰፌው ነግረውናል፤ እኛም ድካምህን ሁሉ እናውቀዋለን ብለው ሲሉኝ ደነገጥሁ፤ ስለምን በዚሁ የአሰብ ውል ምክንያት ከክቡር ራስ እምሩ ጋር ስንነጋገር፣ የኢትዮጵያ መንግሥት ከጣሊያን ጋር የተዋዋለውን ውል ስሕተት ነው ብላቸው፣ መነግሥት የተዋዋለው ውል ስህተት ነው ብለህ ማለት አትችልም፤ ብለው ለእኔ ይቆጡኝ እንጂ በነገሩ አዝነውበት፣ ይህን ውል ሕዝብ አልፈቀደም ብለው ለማፍረስ መድከማቸውን በብዙ መንገድ ተረዳሁት። ገጽ 74

በቀጣይ ክፍል ጣልያን በአሥመራ ዓዲቀይህ ዓዲግራት መቀሌ መንገድ ምን ማድረግ እንዳሰበ፣ የትሪፓሊ ዐረብ ጣልያንን ደግፈው ይወጉናልን ተብለው ሲጠየቁ ምን መልስ እንደሰጡ፣ አመሻሹንም ምን እንደሆነ ይገልጹልናል። ታሪከኛው አባት አርበኛ፡ ጃንሆዩን “ጃንሆይ ጎንደርን ያኸል የኢትዮጵያ እምብርት የሆነውን ሰፊ ሀገር እንደሌሎቹ ሀገሮች ነጋድራስ ሳይሾምበት በመቅረቱ እንዲህ እንዲህ እንዲህ ሆነ” እያሉ ምክንያታዊነታቸውን ዘርዝረው በድፍረት አጤውን የገሰፁበትና የመከሩበትን ትረካ፡ በተጨማሪም ኤርትራን ይገዙ ከነበሩት የጣሊያን ሃገረ ገዢዎች ስለ “የአይሁዳዊው ያዕቆብ ጋስፓሪኒ ፖለቲካ” በቀጣይ እያስኮመኩሙናል፣ እኒህ ኩሩ ቀብራራና ትሁት አባት አርበኛ።

ይህን ታሪክ ብርቅ የሚያደርገው አሁን ያለው አዛውንት ትውልድ ንፍጡ ባፍንጫው ይዝረከረክበት በነበረ ወቅት ለነጻነቱ ሲል ብርቱ ገድልን ባከናወነ ኤርትራዊ አባት አርበኛ የዓይን እማኝነት የተጻፈ በሳል ፖለቲካዊ ትንታኔ መሆኑ ነው። :mrgreen:

Re: ተስፋሚካኤል ትኩእ (1892 – 1964)] - ወለዶና ክነቦ ዝግባእ መኽዘን ታሪኽ

Posted: 18 Jun 2019, 05:03
by Meleket
የኒህ አባት አርበኛ ትረካ ቀጥሏል፣ በቀጣይ ቀናት የሃገሬ የኤርትራ እውነተኛ አንበሶች ማለትም ሰማእታት በልዩ ሁኔታ የሚዘከሩበት ቀን በመሆኑ ለግዜው ትረካውን ገታ አድርገን እውነተኞቹን አንበሶች የሰው ገንዘብን የማይመኙት አንበሶች፣ የተወረሰን ለማስመለስ እንጂ እንደ ደርጎቹና እንደ ወያኖቹ የሰዉን ንብረት ለመውረስ ከቀያቸው ያልወጡትን አንበሶች፣ የሰዉን ንብረት ለመውረስ የሚያቆበቁቡትንም የሚጠየፉት አንበሶች፣ በሃይማኖት እኩልነት የሚያምኑትን አንበሶች፣ በነጻነት የሚያምኑትን አንበሶች፣ ስደት እንዲቆምም ህይወታቸውን ከፍለው ለብዙሃን እፎይታ ለማምጣት ያለፉትን ኤርትራዉያን እውነተኛ አንበሶች ማለትም የተሰዉ ሰማእታቶቻችንን ሁሉ እንዘክራለን። በመሆኑም እስከዚያዉ እስከዛሬ የተካፈልናቸውን ታሪኮች እንድታጣጥሙ እንመክራለን። መልካም ንባብ።

“ኣሥመራ ዓዲቀይህ፣ ዓዲግራት፣ መቀሌ መንገድ ይዞ ጣሊያን ኢትዮጵያን ለመደምሰስ ይመጣል። ለትግሬም ሕዝብ የጣሊያን መንግሥት በማባበል ስብከት ሳይሰብከው አልቀረም፤ እሽ ዓይለዉም እንጂ! ምንም እንኳ በቂ መሣሪያ ባይኖረውም ጣሊያንን ከልቡ ይወጋል። ስለዚህ ከዚህ በላይ ለግርማዊነት እንዳሳሰብሁት በድፍን ትግሬ ምሽግ መመሸግና እኸል መሰብሰብ፣ ወፍጮ ማቆም፣ አስፈጭቶም ዶቄቱን ያለ ዋጋ ስጦታ ሰጥቶ የወታደርን ችግር ካቃለሉለትና እነዚያ የመሠላለፊያ ቦታዎች በጥብቅ አስቀድሞ ማስጠበቅን ነው ስላቸው በደስታ አዳመጡኝ። የትሪፓሊ ዐረብ እሳ ለጣሊያን ረዳት ሆኖ ኢትዮጵያን ለመውጋት ዘመቻ ይዘምት ይመስልሐል? ሲሉኝ።" ገጽ 74

“ግርማዊ ሆይ ከዚህ ቀደም የሙሶሎኒ ፋሽስታዊ መንግሥት ለትሪፓሊ ዐረቦች “ሀገራችሁ መጥተው፣ ሰዋችሁን ገድለው ያስያዙን ኢትዮጵያኖች ናቸውና እናንተም ብድራችሁን ለመመለስ ዘመቻ ትዘምታላችሁ” ቢላቸው “አንዘምትም” ብለውታል ስለተባለ የሚዘምቱ ዓይመስለኝም” ስላቸው “በርግጥ ይዘምታሉ።” እንዳሉት ዐረቦች በብዙ ማታለል አዘመታቸውና አሥመራና ሽሬ፣ ጎንደር ባሌም በብዙ ጭካኔ ሕዝብን የፈጁና የሴትቶች መሣሪያ የነጠቁ ጨካኞች የትሪፓሊና ቸርረናይካ ዓረቦች ናቸው።” ገጽ 74

“ከአሥመራ ጎንደር ምን ያህል ቀን ያስኬዳል?” አሉኝ። ፷፻ ኪሎሜትር ስለሆነ በበጋ በ፰ት ቀን ሊገባ ይችላል። ከአሥመራ በሰቲት ጎንደር ለመግባት በመንገድ ተያዘ የተባለው የጣሊያን አውቶሞቢል እንደምን ሆነ፤ “አንድ ቀኛዝማች መንግሥቱ ጐሹ የሚባል የደጃዝማች አያለው ጠንካራ ሰው ይዞት ነበርና ጣሊያን ተከራክሮ አስለቅቆ ወሰደው ማለት ሰማሁ። ከአሥመራ በሰቲት አርማይጭሆ መንገድ ጎንደር ባጠገብ ካለው ተራራ በቀር ደብረ ማርቆስ ድረስ እየጠረገ ያለ ችግር ለመግባት ይችላል”።" ገጽ 74

“ጃንሆይ ጎንደርን ያኸል የኢትዮጵያ እምብርት የሆነውን ሰፊ ሀገር እንደሌሎቹ ሀገሮች ነጋድራስ ሳይሾሙበት በመቅረቱ የመተማና የሰቲት በር፣ የበርና ገቢያም የበጌምድር ገቢ የሻለቃ አሽከር መጫወቻ ከመሆኑ ይልቅ ለብዙ ወታደሮች ባሳደረና ከሱዳንና ከግብፅም ሕዝብ ጋር ብዙ የወዳጅነት ሥራ ሊሠራ በተቻለ ነበር። የጎንደርም ሕዝብና መኳንንት፣ ሊቃውንትና ካህናት ባመት ባል ቀን የጣሊያን ቆንሱልን ግብር በመብላቱና ብርና መሣሪያ፣ ተማሪዎቹ ሳይቀሩ አሸቦ በኩባያ ስጦታ እየተቀበሉ ወደ ጠላት መሔዳቸው እጅግ አድርጎ ያሳዝናል። በዚሁም የጎንደር ሕዝብ ምክንያት ግርማዊነትዎ በእግዚአብሄር ፊት ይወቀሳል። የጎንደርም ሕዝብ የኢትዮጵያ ንጕሠ ነገሥት መንግሥት መኖሩንና አለመኖሩንም ፈጽሞ አያውቅም” ስላቸው ጃንሆይ አጼ ኃይለ ሥላሴ መኰንን ፊታቸው በኅዘን ጥቁር ለበሰ። እኔም ደነገጥሁ፤ ሁሉንም ገልጨ በመናገሬም ተጸጸትሁ፤ ሞትንም ተመኘሁ። እብድም መሰልሁ እስከዚህ የድፍረት ቃል መናገሬንም በሀገር ፍቅር ሰንሠለት ተገድጄ መናገሬን ከንጕሠ ነገሥት ብርሃናዊ ልቦና አልተሰወረም።" ገጽ 75

“ኤርትራን ይገዙ ከነበሩት የጣሊያን ሀገረ ገዢዎች የማናቸው ፖለቲካ ነው ኢትዮጵያን የሚጐዳ” ብለው ቢሉኝ “የአይሁዳዊው ያዕቅቆብ ጋስፓሪኒ ያኸል ጎጂ ፖለቲካ ያለው የለም። ይህ ጋስፓሪኒ ነጋድራስ ሆኖ ከኢትዮጵያ ወደ ኤርትራ ብዙ ንግድ አጋሰሶች ጭኖ ለመጣ ሰው ሁሉ ሰላም እየሰጠና እየጠየቀም፣ ጠበንጃና ሽጕጥ በመሸለሙ፣ ድፍን የኢትዮጵያ ነጋዴ በዚሁ ስጦታው ወደ ኤርትራ ብቻ እንዲመላለስ በማድረጕ ለመንግሥቱ ብዙ ጥቅም አስገኘ። ፖለቲካም ሠራ። በብዙ ድካማና ወጭም ራስ ጕግሣ ወሌን ያስከዳና ፵ አጋሰስ ጭነት መሣሪያና ጥይት ኢትዮጵያን እርስ በእርስዋ ለማዋጋት የሰጣችው እሱ ጋስፓሪኒ ራሱ ነው” ስል መለስሁላቸው።" ገጽ 75

“የኢጣሊያ መንግሥት የኢትዮጵያን መንግሥት በጦርነት ለመውጋት ሲያስብ ምን ምልክት አለው? “ ብለው አሉኝ። እኔም “ጣሊያን ጦርነት ከማንሳትዋ በፊት በተማሪ ቤት ዑፍሴርነት ማዕርግ ያልወጣ በአምባጋሮኛነቱ ጄኔራል የተባለ የሙሶሊኒ ወዳጅና ቀኝ ክንድ የሆነ ግራሲያኒ በኤርትራ ወይም በሶማሊያ የጦር ሠራዊት ኣዛዥ ሆኖ ተሹሞ ይመጣል” ብዬ መልስሁላቸው። በዚሁም ወሰን የሌለው በአርእስቱ “ከንጕሠ ነገሥት ጋራ የዲፕሎማሲ ፖለቲካዊ ረጅም ቆይታ ማድረጌን” በብዙ ጊዜ ጀምሮ ሲያቃጥለኝ የነበረውን የሀገር ፍቅርና የጣሊያንም ተንኮል ንዴቴን ለግርማዊ የኢትዮጵያ ንጕሠ ነገሥት ቀዳማዊ አጼ ኃይለ ሥላሴ ከ፪ ት ሰዓት የበለጠ ጊዜ በመነጋገሬ ኃዘኔ ተቀነሰ፤ ሕመሜም በረረ፤ ከዚህ በላይ የተናገርሁት ነገር ሁሉም የተፈጸመ መሰለኝ።” ገጽ 75

“በዚህም ህዳር ፳፱ ቀን ፲፱፻፳፮ ዓ.ም. ማታ እኔና አቶ ዮሐንስ አሊ ከባለቤቶቻችን ጋር ከአምቦ በአቶሞቢል ተነስተን ጡዋት አዲስ አበባ በየሥራችን ገባን። ማታም የክቡር ራስ እምሩን የአደራ ደብዳቤ ተቀብዬ ሳነብ፣ አቶ መኰንን ሀብተወልድ መጥተው ራስ እምሩ በአረዮጵላን ከጐጃም መጥተዋልና ሔደው ይገናኙዋቸው አሉኝ። እኔም ኬጄ መድኃኔ ዓለም ቤታቸው ተገናኘሁዋቸው። ስገናኛቸው “ወደ ጎንደር እሔዳለሁና ከኔ ጋር ጎንደር ለመሄድ ትፈቅዳለህ?” ሲሉኝ “አዎ” ስል መለስሁላቸው። እንግዲያውስ ማንም እንዳይሰማው አሉኝ። ነገሩስ ሹም ሽር ተደርጎ ኑሮ በዚሁ ከጠላት ጋር በምንሰላለፍበት ሰዓት ምንም የሻለቃ ሳይሻር በየ ሀገሩ ጦሩን ያደራጅ ብለው የልዑል ራስ ሥዩምና የልዑል ራስ ካሣ፣ የፊታውራሪ ብሩና የራሳቸው የራስ እምሩንም አይሆንም ብለው በመሰረዛቸው በብዙ ተመሰገኑ። (ራስ እምሩ ከጎጃም ገዢነት ወደ ጎንደር እንዲዛወሩ የተሰጣቸውን ትእዛዝ መቃወማችውን ከግል ታሪካቸው ውስጥ ማየት ይቻላል)። የጣሊያን ወገን የሆነ ሲያዝን፣ ኢትዮጵያዊ ወጣትና ሀገሩን የሚያፈቅር ሕዝብና ነፍጠኛ ራስ እምሩ ኃይለ ሥላሴን እውነተኛው ኢትዮጵያዊ ናቸው እያለ ከልብ አመሰገናቸው።” ገጽ 76

“እኔም ከአምቦ የወጣሁኝ ማታ ግርማዊነታቸው እቴጌ መነን ጋር ለማገናኘት ፈልገውን መታጣቴንና ዛሬም በግቢ መፈለጌን ቀኛዝማች ተክለ ማርቆስ በሥልክ አሥጠርተውኝ ወደ ጽሕፈት ሚኒስቴር ብሄድ እኔ ከግርማዊ ጃንሆይ ጋር አምቦ በሰፊው መነጋገሬን ሰምተው እሳት ለብሰው እሳት ጐርሰው አገኘሁዋቸው። እተጌ ይፈልጉዎታልን ሔደው ይገናኙዋቸው አሉኝና ሰው ሰጥተውኝ ተገናኘሁዋቸው። በዚሁም ጊዜ ቀኛዝማች ተክለ ማርቆስ የኛ የኤርትራዊያኖችን ነው እንጂ፤ ሀገራቸውንና ንጕሠ ነገሥታቸውን ፈጽመው መካዳቸውን አልተገነዘብነውም ነበር።” ገጽ 76

በቀጣይ ክፍል “የአልፋረዶ ካርሎን መሞት፣ የጣሊያን መንግሥት ኢትዮጵያን ካሣ መጠየቅ፣ አቶ ጊላጊዮርጊስን ባሻይ ዑቁባ ሚካኤል ገብረ ኢትዮጵያን በተሰወረ ፖለቲካ መደገፍ” የሚለውን ገርመም አድርገነው እናልፋለን።

ይህን ታሪክ ብርቅ የሚያደርገው አሁን ያለው አዛውንት ትውልድ ንፍጡ ባፍንጫው ይዝረከረክበት በነበረ ወቅት ለነጻነቱ ሲል ብርቱ ገድልን ባከናወነ ኤርትራዊ አባት አርበኛ የዓይን እማኝነት የተጻፈ በሳል ፖለቲካዊ ትንታኔ መሆኑ ነው። :mrgreen: