Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Fiyameta
Senior Member
Posts: 13280
Joined: 02 Aug 2018, 22:59

✈️ ✈ ለማመን የሚያስቸግር አስደናቂ እውነተኛ ታሪክ ✈ ✈️

Post by Fiyameta » 19 May 2024, 12:44

በኤርትራ ምድር በተፈጸመ አንድ አስገራሚ ታሪክ ዙሪያ ነው የምንቆየው። ይህንን ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በኢንተርኔት ሳነበው ማመን ከብዶኝ ነበር። ምክንያቱም 18 ሰዎች እንዲያ ዓይነቱን በጀብድ የተመላ ኦፕሬሽን ይፈጽማሉ የሚል ሐሳብ ሊመጣልኝ ስላልቻለ ነው። የደርግ መንግሥት ባለስልጣን የነበሩት አቶ ገስጥ ተጫነ "የቀድሞው ጦር" በሚል ርእስ በጻፉት ዳጎስ ያለ መጽሐፍ ውስጥ ታሪኩን ከዳሰሱት በኋላ ግን እውነት መሆኑን አምኜ ተቀብዬዋለሁ። እናም ያንን ጀብድ በራሴ አቀራረብ ልተርክላችሁ።
-----



የህዝባዊ ግንባር ሓርነት ኤርትራ (ሻዕቢያ) ታጋዮች በትጥቅ ትግሉ ዘመን ከሰማይ ቦምብ እያዘነበ በእንቅስቃሴአቸው ላይ ችግር የፈጠረባቸውን የኢትዮጵያ አየር ሃይል አጥቅተው ከችግሩ ለመገላገል ወሰኑ። በዚህም መሠረት በአስመራ ከተማ ዳር በሚገኘው ሰምበል የተሰኘ የአየር ሃይል ሜዳ ላይ የሚያርፉትን አውሮፕላኖች የሚያወድም ቡድን ያዘጋጁ ጀመር።

ለኦፕሬሽኑ የተመረጡት 16 ታጋዮች ናቸው (ሁለት ታጋዮች በኋላ ላይ ከአስመራ ከተማ ተቀላቅለዋቸዋል)።

ኦፕሬሽኑ ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚፈልግ በመሆኑ ለማጥቃት ዘመቻው የተመረጡት ወጣቶች በሙሉ የአስመራ ከተማን መግቢያና መውጫ በደንብ የሚያውቁ እንዲሆኑ ነበር የተወሰነው።




አስራ ስድስቱ ታጋዮች ለኦፕሬሽኑ የሚያስፈልጋቸው የኮማንዶ ስልጠና በሰሜን ኤርትራ በሚገኘው የሳሕል በረሃ ይሰጣቸው ጀመር። ስልጠናውም ሆነ ስምሪቱ በከፍተኛ ጥንቃቄና ሚስጢር መካሄድ ስለነበረበት ከሰልጣኞቹ፣ ከአንዳንድ የሻዕቢያ ወታደራዊ ሃላፊዎች እና ከጥቂት የግንባሩ መሪዎች በቀር ሌሎች የግንባሩ ታጋዮች ስለጉዳዩ የሚያውቁት ነገር አልነበረም።



ኮማንዶዎቹ በዚህ መንገድ ስልጠናቸውን ካጠናቀቁ በኋላ ከሳሕል ተነሱ። እጅግ ሚስጢር በተመላበት ሁኔታ 250 ኪሎ ሜትር ተጉዘው አስመራ ከተማ ዳርቻ ላይ ደረሱ። እዚያ ሲደርሱም በፊት የኮማንዶ ስልጠና የነበራቸውና መረጃ በማሰባሰብ ስራ ላይ የተሰማሩት ሁለት ኮማንዶዎች ተቀላቀሏቸው።

ኮማንዶዎቹ ያሰቡትን ጥቃት ለመፈጸም የያዟቸው መሳሪያዎች AK-47 ጠመንጃ (ክላሽኒኮቭ)፣ ቀላል ቦምብ ማስወንጨፊያ እና የእጅ ቦምቦዎች ብቻ ነበሩ።



እ.ኤ.አ. ግንቦት 21/1984..... May 21, 1984


ምሽቱ አልቆ ውድቅት ነገሷል። በሰምበል አየር ማረፊያ ያሉ የኢትዮጵያ ጦር ሰራዊት አባላት ጥቂት ወታደሮችን በዘበኝነት ከውጪ አቁመው በቤትና በድንኳን ውስጥ ለጥ ብለው ተኝተዋል።

በወታደራዊ አቆጣጠር በ20:00 ሰዓት ላይ ኮማንዶዎቹ የሰንበል አየር ማረፊያን በማጥቃት በነበልባል እና በጭስ ማንደድ ጀመሩ። በአየር ማረፊያው ላይ ያሉ የጦር አውሮፕላኖች በጥይትና በRPG ሲመቱ የሚፈጠረው ፍንዳታ እንደ ብራቅ ጮኸ። የሰንበል ሜዳ በነፍስ ግቢ፣ ነፍስ ውጪ ስሜት በሚተራመሱ ወታደሮች ተመላ። የኢትዮጵያ ሰራዊት አባላት ምን እየተካሄደ እንዳለ እና ማን እንደመጣባቸው ማወቅ ተሳናቸው። አውሮፕላኖቹ ወደ ሚቃጠሉበት ቦታ ለመጠጋት ሲሞክሩ ደግሞ በሻዕቢያ ኮማንዶዎች ተኩስ እየተቀነደቡ ይወድቁ ጀመር።

የሻዕቢያ ኮማንዶዎች በአየር ማረፊያው ላይ ቆመው የነበሩትን 33 አውሮፕላኖች በሙሉ አወደሙ። በአስራ ስምንት ደቂቃ ውስጥ ግባቸውን ፈጽመው ወደ መጡበት ማፈግፈግ ጀመሩ። ይሁንና በስተመጨረሻው ሰዓት "እምባዬ" የተባለው ኮማንዶ ከተቃራኒ ወገን በተተኮሰበት ጥይት ተመትቶ ወደቀ። አስራ ሰባቱ ኮማንዶዎች ግን በድል አድራጊነት ወደ ሳሕል ነጎዱ።




በሰንበል አየር ማረፊያ ላይ የተፈጸመው ጥቃት በደርግ መንግሥት መሪዎች ዘንድ ከፍተኛ ቁጣን ቀሰቀሰ። በማግሥቱ ጓድ ሊቀመንበር መንግሥቱ ኃይለ ማሪያም እሳት ለብሰው፣ እሳት ጎርሰው ወደ ሰንበል አየር ማረፊያ ከች አሉ። ጥቃቱ ወደተፈጸመበት ስፍራ ሲደርሱ በዚያ ያሉት የጦር ሰራዊቱ አባላት በጥቃቱ የወደቀውን ብቸኛውን የህግሓኤ ኮማንዶ አስከሬን በዱላ እየወገሩ እና በሳንጃ እየወጉ ሲጫወቱበት አገኟቸው።

መንጌ ባዩት ነገር በጣም ተናደዱ። ወታደሮቹንም እንዲህ ሲሉ ተቆጧቸው።
"በቶሎ አቁሙ! ወራዳ ሁላ! ይህ ልጅ ላመነበት ዓላማ ተሰውቷል። እናንተ ግን የእርሱን ያህል ለዓላማ መዋጋትን የማታውቁ ውርጋጦችና ልፍስፍሶች ናችሁ። አሁን አስከሬኑን በቶሎ አንሱትና በክብር ቅበሩት"



ከዚያ ጥቃት በኋላ የኢትዮጵያ አየር ሃይል እስከ ናቅፋ እና ቃሮራ ድረስ እየሄደ የሚያደርሳቸው ጥቃቶች በእጅጉ ቀንሰዋል። ኤርትራም ከሰባት ዓመት በኋላ ነፃነቷን ተቀዳጅታለች።





-----

Tog Wajale E.R.
Senior Member
Posts: 10680
Joined: 31 Oct 2019, 15:07

Re: ✈️ ✈ ለማመን የሚያስቸግር አስደናቂ እውነተኛ ታሪክ ✈ ✈️

Post by Tog Wajale E.R. » 19 May 2024, 13:17

☆ That Fenomenal Operations ☆ !!
☆ But You Forget To Mention One Lady Name ☆ !!
☆ Who Accomadated For This Operations ☆ !!
☆ To Happen, All Tegadeltti Spent A Night ☆ !!
☆ At Her House And Fed Them Properly ☆ !!
☆ Then Went From Her House To Do The ☆!!
☆ Unexpected Tough Operations At Airport ☆ !!
☆ Her Husband Is A Martyr In The Field ☆ !!
☆Was A Known Massawa NavalBase Comander☆!!
☆ It Happen To Be My Auntie And Now Lives ☆ !!
☆ In Vancouver Canada And Her Name Is ☆ !!
☆ Shemainesh G/ Egzeabiher ☆ !!
☆ እዚ፥ወ'ድሓንካ፥የ'ቐንየልና ☆ !!




kebena05
Member
Posts: 2415
Joined: 10 Nov 2019, 14:58

Re: ✈️ ✈ ለማመን የሚያስቸግር አስደናቂ እውነተኛ ታሪክ ✈ ✈️

Post by kebena05 » 19 May 2024, 16:26

Most of these heroic commandos are now martyred in various fronts since their heroic operation in Sembel. The sad part is, two of them martyred in Shire Enda Selasse, decimating the Derg's "best" military division, Core 603, liberation Shire from Derg in early 1990. One of these commandos are equal to over 100s Derg or Weyane soldiers. They train for 10 plus years in harsh environment in one of the toughest commando trainings in the world. Every Tegadelay Shaebia wants to be a member of this unique team but only very few make it. Most even die during the harsh training before even they see their first action, therefore, losing two in Shire was extremely a sadden day in Shaebia leadership back then. History will forever continue to celebrate that day operation in Sembel, burning down the entire EAF fighter plane fleets, Helicopters as well as cargo planes. The Derg lost over $2Billion in one day (3 years of Ethiopia's yearly budget at the time).


Fiyameta wrote:
19 May 2024, 12:44
በኤርትራ ምድር በተፈጸመ አንድ አስገራሚ ታሪክ ዙሪያ ነው የምንቆየው። ይህንን ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በኢንተርኔት ሳነበው ማመን ከብዶኝ ነበር። ምክንያቱም 18 ሰዎች እንዲያ ዓይነቱን በጀብድ የተመላ ኦፕሬሽን ይፈጽማሉ የሚል ሐሳብ ሊመጣልኝ ስላልቻለ ነው። የደርግ መንግሥት ባለስልጣን የነበሩት አቶ ገስጥ ተጫነ "የቀድሞው ጦር" በሚል ርእስ በጻፉት ዳጎስ ያለ መጽሐፍ ውስጥ ታሪኩን ከዳሰሱት በኋላ ግን እውነት መሆኑን አምኜ ተቀብዬዋለሁ። እናም ያንን ጀብድ በራሴ አቀራረብ ልተርክላችሁ።
-----



የህዝባዊ ግንባር ሓርነት ኤርትራ (ሻዕቢያ) ታጋዮች በትጥቅ ትግሉ ዘመን ከሰማይ ቦምብ እያዘነበ በእንቅስቃሴአቸው ላይ ችግር የፈጠረባቸውን የኢትዮጵያ አየር ሃይል አጥቅተው ከችግሩ ለመገላገል ወሰኑ። በዚህም መሠረት በአስመራ ከተማ ዳር በሚገኘው ሰምበል የተሰኘ የአየር ሃይል ሜዳ ላይ የሚያርፉትን አውሮፕላኖች የሚያወድም ቡድን ያዘጋጁ ጀመር።

ለኦፕሬሽኑ የተመረጡት 16 ታጋዮች ናቸው (ሁለት ታጋዮች በኋላ ላይ ከአስመራ ከተማ ተቀላቅለዋቸዋል)።

ኦፕሬሽኑ ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚፈልግ በመሆኑ ለማጥቃት ዘመቻው የተመረጡት ወጣቶች በሙሉ የአስመራ ከተማን መግቢያና መውጫ በደንብ የሚያውቁ እንዲሆኑ ነበር የተወሰነው።




አስራ ስድስቱ ታጋዮች ለኦፕሬሽኑ የሚያስፈልጋቸው የኮማንዶ ስልጠና በሰሜን ኤርትራ በሚገኘው የሳሕል በረሃ ይሰጣቸው ጀመር። ስልጠናውም ሆነ ስምሪቱ በከፍተኛ ጥንቃቄና ሚስጢር መካሄድ ስለነበረበት ከሰልጣኞቹ፣ ከአንዳንድ የሻዕቢያ ወታደራዊ ሃላፊዎች እና ከጥቂት የግንባሩ መሪዎች በቀር ሌሎች የግንባሩ ታጋዮች ስለጉዳዩ የሚያውቁት ነገር አልነበረም።



ኮማንዶዎቹ በዚህ መንገድ ስልጠናቸውን ካጠናቀቁ በኋላ ከሳሕል ተነሱ። እጅግ ሚስጢር በተመላበት ሁኔታ 250 ኪሎ ሜትር ተጉዘው አስመራ ከተማ ዳርቻ ላይ ደረሱ። እዚያ ሲደርሱም በፊት የኮማንዶ ስልጠና የነበራቸውና መረጃ በማሰባሰብ ስራ ላይ የተሰማሩት ሁለት ኮማንዶዎች ተቀላቀሏቸው።

ኮማንዶዎቹ ያሰቡትን ጥቃት ለመፈጸም የያዟቸው መሳሪያዎች AK-47 ጠመንጃ (ክላሽኒኮቭ)፣ ቀላል ቦምብ ማስወንጨፊያ እና የእጅ ቦምቦዎች ብቻ ነበሩ።



እ.ኤ.አ. ግንቦት 21/1984..... May 21, 1984


ምሽቱ አልቆ ውድቅት ነገሷል። በሰምበል አየር ማረፊያ ያሉ የኢትዮጵያ ጦር ሰራዊት አባላት ጥቂት ወታደሮችን በዘበኝነት ከውጪ አቁመው በቤትና በድንኳን ውስጥ ለጥ ብለው ተኝተዋል።

በወታደራዊ አቆጣጠር በ20:00 ሰዓት ላይ ኮማንዶዎቹ የሰንበል አየር ማረፊያን በማጥቃት በነበልባል እና በጭስ ማንደድ ጀመሩ። በአየር ማረፊያው ላይ ያሉ የጦር አውሮፕላኖች በጥይትና በRPG ሲመቱ የሚፈጠረው ፍንዳታ እንደ ብራቅ ጮኸ። የሰንበል ሜዳ በነፍስ ግቢ፣ ነፍስ ውጪ ስሜት በሚተራመሱ ወታደሮች ተመላ። የኢትዮጵያ ሰራዊት አባላት ምን እየተካሄደ እንዳለ እና ማን እንደመጣባቸው ማወቅ ተሳናቸው። አውሮፕላኖቹ ወደ ሚቃጠሉበት ቦታ ለመጠጋት ሲሞክሩ ደግሞ በሻዕቢያ ኮማንዶዎች ተኩስ እየተቀነደቡ ይወድቁ ጀመር።

የሻዕቢያ ኮማንዶዎች በአየር ማረፊያው ላይ ቆመው የነበሩትን 33 አውሮፕላኖች በሙሉ አወደሙ። በአስራ ስምንት ደቂቃ ውስጥ ግባቸውን ፈጽመው ወደ መጡበት ማፈግፈግ ጀመሩ። ይሁንና በስተመጨረሻው ሰዓት "እምባዬ" የተባለው ኮማንዶ ከተቃራኒ ወገን በተተኮሰበት ጥይት ተመትቶ ወደቀ። አስራ ሰባቱ ኮማንዶዎች ግን በድል አድራጊነት ወደ ሳሕል ነጎዱ።




በሰንበል አየር ማረፊያ ላይ የተፈጸመው ጥቃት በደርግ መንግሥት መሪዎች ዘንድ ከፍተኛ ቁጣን ቀሰቀሰ። በማግሥቱ ጓድ ሊቀመንበር መንግሥቱ ኃይለ ማሪያም እሳት ለብሰው፣ እሳት ጎርሰው ወደ ሰንበል አየር ማረፊያ ከች አሉ። ጥቃቱ ወደተፈጸመበት ስፍራ ሲደርሱ በዚያ ያሉት የጦር ሰራዊቱ አባላት በጥቃቱ የወደቀውን ብቸኛውን የህግሓኤ ኮማንዶ አስከሬን በዱላ እየወገሩ እና በሳንጃ እየወጉ ሲጫወቱበት አገኟቸው።

መንጌ ባዩት ነገር በጣም ተናደዱ። ወታደሮቹንም እንዲህ ሲሉ ተቆጧቸው።
"በቶሎ አቁሙ! ወራዳ ሁላ! ይህ ልጅ ላመነበት ዓላማ ተሰውቷል። እናንተ ግን የእርሱን ያህል ለዓላማ መዋጋትን የማታውቁ ውርጋጦችና ልፍስፍሶች ናችሁ። አሁን አስከሬኑን በቶሎ አንሱትና በክብር ቅበሩት"



ከዚያ ጥቃት በኋላ የኢትዮጵያ አየር ሃይል እስከ ናቅፋ እና ቃሮራ ድረስ እየሄደ የሚያደርሳቸው ጥቃቶች በእጅጉ ቀንሰዋል። ኤርትራም ከሰባት ዓመት በኋላ ነፃነቷን ተቀዳጅታለች።





-----

euroland
Member+
Posts: 7944
Joined: 08 Jun 2018, 12:42

Re: ✈️ ✈ ለማመን የሚያስቸግር አስደናቂ እውነተኛ ታሪክ ✈ ✈️

Post by euroland » 19 May 2024, 16:44

Essayas, this team commando leader who led the Sembel operation was killed in DeqeMehare’s operation in May 22, 1991, 2 days before the liberation of Eritrea in May 24, 1991. How sad. His heroine deed wiped out the entire Ethiopia’s “night owel” division who were camped out in DeqeMehare. The explosive he planted in the middle of thousands of these elite Derg soldiers blew up and wiped out all of them while he willingly sacrificed his life during the operation. He had killed hundreds of the enemies during his 20 plus years of service but this one toppled them all. He literally went out with a big “Bang!” Killing hundreds more to close his chapter.

Fiyameta
Senior Member
Posts: 13280
Joined: 02 Aug 2018, 22:59

Re: ✈️ ✈ ለማመን የሚያስቸግር አስደናቂ እውነተኛ ታሪክ ✈ ✈️

Post by Fiyameta » 19 May 2024, 16:47

Israeli commando did it in 90 minutes with 100 commandos.
The Eritrean commando did it in 18 minutes with only 18 commandos.








sesame
Member+
Posts: 6208
Joined: 28 Feb 2013, 17:55

Re: ✈️ ✈ ለማመን የሚያስቸግር አስደናቂ እውነተኛ ታሪክ ✈ ✈️

Post by sesame » 20 May 2024, 11:00

A book titled ቅያ 18 ደቓይቕ (18 Minute Operation) by Solomon Drar is narrated in 22 parts starting in the following youtube video!


Digital Weyane
Member+
Posts: 8717
Joined: 19 Jun 2019, 21:45

Re: ✈️ ✈ ለማመን የሚያስቸግር አስደናቂ እውነተኛ ታሪክ ✈ ✈️

Post by Digital Weyane » 20 May 2024, 14:08

ድሮ ልጆች ሆነን የሕወሃት ካድሬዎች <<አንድ የትግራይ ገበሬ ዲንጋይ በመወርወር የደርግን ሄሊኮፕተር ማረከ>> እያሉ ሲነግሩን እውነት መስሎን ዲንጋይ በኪሳችን ይዘን ስንዞር የልጅነት ትውስታዬ ነው።

ከድንቁርና ቀንበር ገና ነፃ ያልወጡ ተጋሩ ዎገኖቼ የሰለጠነ ሃገር ውስጥ ተቀምጠው እስከ ዛሬ ድረስ በአውሮፓና በአሜሪካ ዲንጋይ በኪሳቸው ይዘው ይዞራሉ። እነዚህ ራሳቸውን <<ብርጌድ ንሓመዱ>> ብለው የሚጠሩ የትግራይ ሕዝብ ነቀርሳዎች በስልጣኔ እና በእውቀት የሚበልጡዋቸው አፍሪካውያንን በተለያየ አጋጣሚ ሲያገኙ ድንጋይ በመወርወር የበታችነት ስሜታቸውን ይገልፃሉ። ዋይ ዋይ ዋይ ዋይ ዋይ :cry: :cry: :cry: :cry:

Fiyameta
Senior Member
Posts: 13280
Joined: 02 Aug 2018, 22:59

Re: ✈️ ✈ ለማመን የሚያስቸግር አስደናቂ እውነተኛ ታሪክ ✈ ✈️

Post by Fiyameta » 21 May 2024, 12:11

"People are interested in Talent. God is impressed by Character."


Fiyameta
Senior Member
Posts: 13280
Joined: 02 Aug 2018, 22:59

Re: ✈️ ✈ ለማመን የሚያስቸግር አስደናቂ እውነተኛ ታሪክ ✈ ✈️

Post by Fiyameta » 21 May 2024, 12:46

Today, May 21st, marks the 40th anniversary of the Eritrean Commando operation that heralded the dawn of a new era of Eritrean Independence. We honor the memory of the heroes who gave their lives for the total liberation of Eritrea.






Post Reply