Blog Archives

የጌዴኦና የጉጂ ህዝቦች ለዘመናት የገነቡት አብሮነት ላይነጣጠል የተሳሰረ ነው አሉ የጌዴኦና ጉጂ አባ ገዳዎች

የጌዴኦና የጉጂ ህዝቦች ለዘመናት የገነቡት አብሮነት ላይነጣጠል የተሳሰረ ነው አሉ የጌዴኦና ጉጂ አባ ገዳዎች በሁሉቱ ህዝቦች መካከል ችግር ልፈጥሩ የሚቀሳቀስ ሃይሎች ከአሁን ቦሃላ ምንም አይነት ቦታ ሰለማይኖራቸው ወጣቶች ይህን በመረዳት እራሳቸውን ከእኩይ ተግባር እንዲቆጥቡ አሳስበዋል ። በምዕራብና ምስራቅ ጉጂ ዞኖችና በጌዴኦ ዞን አጎራባች አከባቢዎች የተከሰተውን ግጭት በዘላቂነት ለመፍታት የሚያስችል የሰላም ኮንፍራንስ ተኳሂዷል። በመድረኩም መልዕክት ያስተላለፉት የጌዴኦና ጉጂ አባ ገዳዎች የጎንዶሮ ስርዓት የፈረሰበትን ምክንያት በሰፋት ውይይት በማድረግ አሁን ሠላም ማውረድ ሰለቻልን የእኛ የሆናችሁ ህዝቦች በሙሉ እርቀ ሠላም እንዲታወርዱና እንዳለፈው ጊዜ በጋራ በፍቅር እንዲትኖሩ ሲሉ ተናግረዋል ወጣቶች በበኩላቸው በቀጣይ ተፈናቃዮች ወደ አከባቢያቸው ሲመለሱ ተገብውን ድግፍ በማድረግ የበደልነውን ህዝብ ለመካስ ዝግጁ ነን በማለት ገልጸዋል የፌዴራል የአርብቶ አደር ልማት ጉዳች ሚኒስቴር በበኩሉ በጌዴኦና ጉጂ ህዝቦች መካከል ሠላም መውረዱ በአከባቢው ዘላቅ ሠላም እንዲወርድ የሚደረገውን ጥረት ከመደገፉ ባለፈ ለመንግስትም ሆነ ለህዝብ ትልቅ ድል መሆኑን ገልጸዋል። ምንጭ፡ የዞኑ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት
Tagged with: , , ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

በደቡብ ኢትዮጵያ ከስምንት መቶ ሺህ በላይ ዜጎች በሀይል ከቀያቸው ተፈናቅለዋል።

(ምንሊክ ሳልሳዊ) ሮይተርስ የተባበሩት መንግስታትን ዋቢ በማድረግ ባቀረበው ዘገባ በደቡብ ኢትዮጵያ ከስምንት መቶ ሺህ በላይ ዜጎች በብሔር ግጭት የተነሳ በሀይል ከቀያቸው ተፈናቅለዋል። የምግብና ሌሎች አስቸኳይ እርዳታዎች ይፈልጋሉ። ካለፈው ሚያዚያ ጀምሮ በተከሰተው የብሔር ግጭት ከአዋሳ 250 ኪሜ ርቀት ጌዲዮ ላይ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ተፈናቃዮች ፈሰዋል በተጨማሪ የአከባቢው ባለስልጣናት እንዳሉት በጌዲዮና በጉጂ ኦሮሞዎች መካከል በተከሰተ ግጭት በጌዲኦ 642,152 ተፈናቃዮች በጉጂ ዞን 176,098 ተፈናቃዮች ካለፈው ሰኔ 2010 ጀምሮ ተመዝግበዋል ። (ምንሊክ ሳልሳዊ) ሙሉ ዘገባው እነሆ፦   https://mobile.reuters.com/article/amp/idUSKBN1JU14W?
Tagged with: ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የጌዲዮ እና የጉጂ ማህበረሰቦችን ግጭት ተከትሎ የጌዲዮ ህዝብ ለከፍተኛ ችግር ተዳርጓል

የጌዲዮ እና የጉጂ ማህበረሰቦችን ግጭት ተከትሎ የጌዲዮ ህዝቡ ለከፍተኛ ችግር ተዳርጓል።
Tagged with: ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ኦሕዴድ በጌድኦ ሕዝብ ላይ ግድያና ማፈናቀሉን ተከትሎ በዲላና አከባቢው የሚኖር ሕዝብ ስጋት ላይ ነው ።

እየበረታ የሔደው ግድያና መፈናቀል ይቁም። በጉጂና በጌዴኦ ዞኖች እየተደረገ ያለው ዘርን መሰረት ያደረገ ጥቃት እጅግ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ደርሷል። በሺዎች የሚቆጠሩ ጌዴኦዎች ከኦሮሚያ እየተፈናቀሉ እየሞቱ ይገኛሉ። ጌዴኦዎች ይህንን ግፍ ለመመለስ በዞናቸው ያለውን ሌላውን ብሄር ለማጥቃት እየዛቱ ይገኛሉ። በዲላና ሌሎች ቦታዎች ሰዎች በፍርሃት በመሸማቀቅ ላይ ነው ያሉት መከላከያው እንደጉድ ፈሷል። ስለ ሕዝብ በደል ሁላችንም በጋራ ቆመን ልንጮህ ይገባል ።
Tagged with: , ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News