Blog Archives

አማራን የሚያገልና የሚጨቁን የፌዴራሊዝም አተገባበር ነው የነበረው!!

በኩር፤ ሐምሌ 23 ቀን 2010 ዓም አማራን የሚያገልና የሚጨቁን የፌዴራሊዝም አተገባበር ነው የነበረው!!   ዶክተር ሲሳይ መንግሥቴ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የህግና አስተዳደር መምህር ናቸው:: በሰብዓዊ መብት ዙሪያም የረዳት ፕሮፌሰርነት ማዕረግ አላቸው:: ዶክተር ሲሳይ በአማራ ክልል ፍትህ ቢሮ በምክትል ሀላፊነት ያገለገሉ ሲሆን በቀድሞ ስሙ የኢህዴን (ብአዴን) ታጋይም ነበሩ:: ዶክተሩ የዚህ እትም እንግዳችን ናቸው:: መልካም ንባብ! ስምዎ በተለየ ሁኔታ ከራያ ህዝብ ጋር ብዙ ጊዜ ይነሳል:: ምክንያቱ ምንድን ነው? ተወልጀ ያደግሁ ራያ ውስጥ ነው:: በራያ ስማር በነበረው የፖለቲካ ትኩሳት ወደ ኢህዴን ገብቸም ታግያለሁ:: ኢህዴን /ብአዴን/ በነበርኩበት ጊዜ የራያን ህዝብ መብትና ጥቅም እንዲጠበቅ እታገል ነበር:: የራያ ህዝብ ፍላጐት ሳይጠየቅ በሁለት ክልሎች እንዲተዳደር ተደርጓል:: በ2005 ዓ.ም የራያ ህዝብ የማንነት ጥያቄ እና የማዕከላዊ መንግሥታት ምላሽ ከአፄ ዮሐንስ እስከ ኢህአዴግ የሚል መጽሀፍ ከጓደኛዬ ጋር ሆነን አዘጋጅተናል:: የራያን ህዝብ ታሪክ እና ተጋድሎም እያሳወቅሁ ነው:: የራያን ህዝብ ተጋድሎ ትግራዮች ደግሞ ቀዳማዊ ህዝብ ወያኔ ትግል የሚሉትን ታሪክ በተመለከተ በማስረጃ ሞግተናል:: ቀዳማዊ ህዝብ ወያኔ የራያ ህዝብ ታሪክ ነው:: በዚህ ጉዳይ ጽፌያለሁ፤ሞግቻለሁ:: ለዚህ ይመስለኛል ስሜ ከራያ ህዝብ ጋር ጐልቶ የሚነሳው:: የራያ ህዝብ ስነ ልቦናዊና ባህላዊ ቅርበቱ ከየትኛው ማህበረሰብ ጋር ነው? የራያን ህዝብ ሠዎች በተለያየ መንገድ ይገልፁታል:: የራያ ህዝብ ስንል በድሮው የራያ ቆቦና አዘቦ አውራጃ የሚኖር ህዝብ ድምር ነው:: የራያነት ስነ ልቦና አለው:: ራያ የነ ጥላሁን ግዛው ሀገር ነው:: አማርኛ ይነገራል:: ትግረኛ የሚመስል
Tagged with: , ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News