Blog Archives

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያጉላላቸውን ሃጃጆች ይቅርታ ጠየቀ ።

በመጨረሻም አየር መንገዱ ይቅርታ ጠይቋል !!! ብዙ ሰበቦች ቢደረድርም በመጨረሻም ይቅርታ ጠይቋል ካሁን በሁላ እንደማይደገም ተስፋ አለን ! ይቅርታችሁን በቀጣይ መሰል ስህተት ባለመስራት ተገቢ መስተንግዶ በመስጠት ሀጃጆች ከሀጅ ሲመለሱ ተገቢ መስተንግዶ በመስጠት አሳዩ Image may contain: text    
Tagged with: , ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ኢትዮጵያውያን የሐጅ ተጓዦችን ማንገላታቱን ቀጥሎበታል

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ኢትዮጵያውያን የሐጅ ተጓዦችን ማንገላታቱን ቀጥሎበታል ዛሬም እንደ ተለመደው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ኢትዮጵያውያን የሐጅ ተጓዦችን ባልተገለፀ ምክኒያት የኢትዮጵያ-ሳውዲ አረቢያ በረራውን መሰረዙን በመግለፁ ምክንያት በአሁን ወቅት በኤርፓርት ውስጥ የሐጅ ተጓዦች እየተንገላቱ ይገኛሉ። ይህ አየር መንገድ በኢትዮጵያ ሓጃጆች ላይ የሚፈፅመው በደል ከልክ አልፏል። በአሁኗ ሰዓት እንኳ መንገደኞችን በረራ ሰርዞባቸው ውጭ ላይ እየተንገላቱ መሆናቸውን ከስር የተያየዘውን ፎቶ ተመልከቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በየአመቱ ከሚያቅዳቸው ዕቅዶች ውስጥ “ኢትዮጵያውያን የሐጅ ተጓዦችን ማንገላታት” የሚል ያለበት ይመስል ካቻምና፣ አምናም ዘንድሮም ኢትዮጵያውያን የሐጅ ተጓዦችን ማንገላታቱን ቀጥሎበታል
Tagged with: , , ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ከዛሬ 23 አመት በፊት ወደ ሳዑዲ አረቢያ የተሰደዱት ሼህ ሰኢድ አህመድ ወደአገራቸው ተመለሱ

ከዛሬ 23 አመት በፊት ወደ ሳዑዲ አረቢያ የተሰደዱት ሼህ ሰኢድ አህመድ ወደአገራቸው ተመለሱ ሼህ ሰኢድ አህመድ ሙስጠፋ ከ23 አመት ቆይታ በኃላ ወደሀገራቸው ተመለሱ። ሼህ ሰኢድ ከዛሬ 23 አመት በፊት ወደ ሳዑዲ አረቢያ የተሰደዱ የሀይማኖት አባት ናቸው። ሼሁ አገር ውስጥ በነበሩበት ጊዜ የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ማህበር መስራችና ሊቀመንበር ነበሩ። ከዚህም በተጨማሪ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የዳዕዋና የፈትዋ ኮሚቴ አባል፣ የኢትዮጵያ ቅዱስ ቁርዓን ማህበር አባል የነበሩ ናቸው። በአሁኑ ወቅትም በዳያስፖራ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች አንድነት የበላይ ጠባቂ ናቸው። በዚህም ወቅት የሀይማኖቱ ተከታይ ወጣቶችና የሀይማኖት አባቶች በቦሌ አለም አቀፍ አየር ማረፊያ ተገኝተው አቀባበል አድርገውላቸዋል።
Tagged with:
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የሀጅና ዑምራ ጉዞ ዘረፋ መጅሊስና የኢትዮጵያ አየር መንገድ

የሀጅ ጉዞ ዘረፋ መጅሊስና የኢትዮጵያ አየር መንገድ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዌብሳይት ጎራ አልኩና ስለ ሀጅ ጉዞ ወጪ ዝርዝር አየሁ፡፡ ባጠቃላይ 97,910 ብር ክፍያ እንደሚያስፈልገው ያሳያል፡፡ መጀመሪያ ላይ የተቀመጠው የአየር ቲኬት ነው፡፡ ዋጋውም 25,510 ብር ነው ይላል፡፡ ከሀጅ ውጭዎች ውስጥ ወደ ጅዳ ያለውን የትኬት ዋጋ ለማጣራት ሞባይሌን ከፍቼ የኢትዮጵያ አየር መንገድን ዌብ ሳይት ማየት ጀመርኩ፡፡ የትኬት ዋጋ ሌላ ቀናት ጊዜ መርጬ ትኬት ስሞክር የጅዳ የአየር ትኬት ዋጋ እስከ 12,786 ብር ወርዶ አየሁ፡፡ በርግጥ የበረራ ዋጋ በየወቅቱ የሚዋወጥ ቢሆንም ለኢኮኖሚ ተጓዥ ይሄንን ያህል ያለው ልዩነት ፈፅሞ አግባብ ያለው ጭማሪ አይደለም፡፡ የተጠየቀው ዋጋ 100 ፐርሰንት ጭማሪ ያለው ግልፅ የዘረፋ ድርጊት ነው፡፡ ይህ ዘረፋ እየተደረገ ያለው በመጅሊስና በኢትዮጵያ አየር መንገድ ትብብር ይመስላል፡፡ (የኢትዮጵያ አየር መንገድ ይህንን እስካላስተባበለ ድረስ) ለ5ሰአት30ደቂቃ በረራ 25,510 ብር! ልዩነቱን ለማጉላት ጅዳ እጅጉን ወደሚርቁ ወደተለያዩ ከተሞች በጁላይ መጨረሻ/ኦገስት መጀመሪያ ከአዲስ አበባ ተነስቼ ኦገስት መጨረሻ ወደ አዲስ አበባ ብመለስ ብዬ የምጠየቀውን የትኬት ዋጋ ለንፅፅር ላቅርብ፡፡ ለንደን (እንግሊዝ) 24,522ብር – ደርሶ መልስ የሚፈጀው የበረራ ሰአት 15፡35) አቢጃን (ኮት ዴቮዋር) 22,599 ብር ደርሶ መልስ የሚፈጀው የበረራ ሰአት 12፡30) ቦንቤይ/ሙምባይ (ህንድ) 18,536 ብር ደርሶ መልስ የሚፈጀው የበረራ ሰአት 10:20) ባንኮክ (ታይላንድ) 17,202 ብር (ደርሶ መልስ የሚፈጀው የበረራ ሰአት 17፡50) ጆሃንስበርግ (ደቡብ አፍሪካ) 10,430 ብር ደርሶ መልስ የሚፈጀው የበረራ ሰአት 10:50) እንደመጅሊስ አባባል ከሆነ ደርሶ መልስ
Tagged with: , , ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ ከክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋራ ያደረጉት ውይይት አሁን ማምሻውን በድል ተጠናቋል፡፡

የኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ ከክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋራ ያደረጉት ውይይት አሁን ማምሻውን በድል ተጠናቋል፡፡ በውይይቱ መጨረሻ ስድስት ዓላማዎችን የማሳካት ዓላማ ያለው ከኮሚቴው ሦስት፣ ከመጅሊስ ሦስት፣ ከገለልተኛ ወገን ሦስት በጥቅሉ ዘጠኝ አባላት ያሉት ዐዲስ ኮሚቴ ተዋቅረዋል፡፡ የዐዲሱ ኮሚቴ አባላትም አቡበክር አሕመድ፣ አሕመዲን ጀበል፣ ካሚል ሸምሱ፣ ረዳት ፕሮፌሰር ኢድሪስ ሙሐመድ፣ ፕሮፌሰር ሙሐመድ ሐቢብ፣ ሸይኽ ሙሐመድ ጀማል አጎናፍር፣ ሸይኽ ሙሐመድ አሚን፣ ፈዲለተል ሙፍቲ ሐጅ ዑመር ኢድሪስ፣ ሸይኽ ኸድር ሑሰይን መሆናቸው ታውቋል፡፡ ዝርዝሩን እንደደረሰን እናቀርባለን፡፡
Tagged with:
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ጠቅላይ ምኒስትር አብይ አሕመድ የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ ጋር ተገናኙ

ምንሊክ ሳልሳዊ : ሰኞ ለማክሰኞ ምሽት ሰኔ 25 ቀን 2010 ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት በተደረገ ድንገተኛ ጥሪ፤ የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ ዛሬ ዕለተ ማክሰኞ ሰኔ 26 ቀን 2010 ከክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጋራ አራት ኪሎ በሚገኘው የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽሕፈት ቤት ተገኝተው በሕዝበ ሙስሊሙ መሠረታዊ ጥያቄዎች ዙሪያ ውይይት እያኪያሄዱ ነው፡፡ አቡበክር አሕመድ ሐጂ ሑሰይን ላለምዳ ረ/ፕሮፌሰር አደም ካሚል አሕመዲን ጀበል ያሲን ኑሩ ካሚል ሸምሱ ሸይኽ ሱልጣን ሐጂ አማን ሸይኽ ዩሱፍ ሙዘሚል ጀማል ያሲን ሐጂ ከማል ኑሪ ዑመር ዐብዱረዛቅ ቃዲ አል-ቁዳት ሸይኽ መከተ ሙሔ ሐጂ አየነው ሙሐመድ ሸይኽ ዓብደላህ ኢድሪስ ሸይኽ ጧሂር ዐብዱል ቃድር …በአሁኑ ሰዐት የውይይቱ ተካፋይ የሆኑ የኮሚቴው አባላት ናቸው፡፡ በተያያዘ ዜና በትላንትናው ዕለት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት አመራር አባላት ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋራ በዚሁ ጉዳይ የተወያዩ መሆናቸውን ውስጥ ዐዋቂ ምንጮቻችን ነግረውናል፡፡
Tagged with: ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ መግለጫ ሰጡ ።

የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ያቀረቡትን ጥሪ መነሻ አድርገው በኢሊሌ ኢንተርናሽናል ሆቴል በግሪን ሆል አዳራሽ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል ፡
Tagged with: ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የቀድሞ የመጅሊስ ፕሬዝዳንት ዝምታውን ሰበሩ የደረሰውን በደል ተናገሩ

የቀድሞ የመጅሊስ ፕሬዝዳንት ዝምታውን ሰበሩ የደረሰውን በደል ተናገሩ ============ © ግዮን መፅሔት ዛሬ (ሰኔ 2/2010 ቅፅ 1 ቁጥር9) የተዳፈነው የሙስሊሙ ሐቅ! ከቀድሞው መጅሊስ ፕሬዘዳንት ሸይኽ ኺያር ሙሐመድ አማን ጋር የተደረገ ቆይታ። በ2005 በተደረገ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ምርጫ የምርጫው ዘመን ሳያልቅ እና የጠቅላይ ምክርቤቱ ደንብ ሳይፈቅድ የጠቅላይ ምክር ቤቱ ስራ አስፈፃሚ በ2007 እንዲበተን እና እዚህ ግባ በማይባል በሌላ ቡድን እንዲተካ መደረጉ የሚታወቅ ሀቅ ነው፡፡ የዚህ ህገ ወጥ ግልበጣ ዋና ተዋናኞች ደግሞ የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስትር እና ሚኒስትር ዴታው፣ የኮሚኒኬሽን ሚኒስቴር ዴታው የነበረው አቶ ሽመልስ ከማል (ለዚሁ አፍራሽ ስራው እንደ ሽልማት ከመንግስት የመንግስት ቤት በስሙ ካርታው ዙሮለታል)፣ የፔትራም ድርጅት ባለቤት፣ የአዲስ አበባ መጂሊስ ፕሬዝዳንት የነበረው ዶ/ር አህመድ፣ ከውጭ ሀገር ደግሞ አቶ ሳላሀዲን ወዚር የአህባሾቹ መሪ እንዲሁም በአንዳድ የመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት ተጽእኖ ስር በወደቁ የመጅሊስ ኡለማ ምክር ቤት አባላት ናቸው፡፡ የግልበጣው ዋነኛ ሰበብና ሽፋን የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዝዳንትና ለሐቅና ለትክክለኛ ሥራ ቁርጥ አቋም የነበረን አብዛኞቹ የሥራ አስፈጻሚዎች “ወሀብያ ናቸው ተብለን ” በተደጋጋሚ በሕዝብ ጆሮ እንዲናፈስ የተደረገው ውሽት እውነት እንዲመስል ተደርጐ መቅረቡ ነው፡፡ በመሰረቱ “ወሀብያ” የሚለው ቃል እና ጽንሰ ሀሳብ እስልምና የማያውቀው፣ በኢትዮጵያ መኖሩ ያልተረጋገጠ፣ ተረጋግጦም ከሆነ ያረጋገጠው አካል በሕግ እንዲታገድ አድርጎ፣ ይህን በዋህብያ የተፈረጀ ቡድን ወይም ግለሰብ እንድናውቀው አልተደረገም፡፡ እንዲህ አይነቱ ህገ መንግስታዊ አሰራር በሌለበት ሁኔታ እምነታችን፣ አስተሳሰባችንና ግብራችን ‹‹ዋህብያ›› የሚሉት
Tagged with:
Posted in Amharic News, Ethiopian News

መስጂዶችን በሃይል በማፍረስ የሚመጣ ዘላቂ ሰላም የለም!

መስጂዶችን በሃይል በማፍረስ የሚመጣ ዘላቂ ሰላም የለም! . ☞ ኡስታዝ አቡበከር አሕመድ . በቡራዩ ከተማ በልዩ ስሙ አሸዋ ሜዳ ፍሪዶሮ “ፀበል ማዶ” ተብሎ በሚታወቀው አካባቢ ሙስሊሙ ሲገለገልበት የነበረው መስጂድ በታጠቁ የመንግስት ሃይሎች እንዲፈርስ መደረጉ ብሎም በንፁሃን የአካባቢው ሙስሊሞች ላይ የተወሰደው ኢ ሰብአዊ የሃይል እርምጃ ሃገራችን በአዲስ የለውጥ ጎዳና ላይ ገብታለች የሚለውን እሳቤ ጥላሸት የሚቀባና ሙስሊሙ ማህበረሰብ ይዞት የነበረውን የለውጥ ተስፋ የሚያጨልም ተግባር ነው፡፡ ዜጎች የፈለጉትን እምነት የመከተል፣እምነታቸውን የሚያራምዱበት ቤተ አምልኮ የመገንባት መብት ህገ መንግስቱ ቢደነግግም ሙስሊሙ ማህበረሰብ በአብዛኛው የሚገነባቸው መስጂዶች የጊዜ፣የአካል እና የህይወት መስዋትነቶችን እየተከፈለባቸው ነው፡፡ ሃገራችን በሰላም፣በእርቅ ፣በይቅርታ እና በመደማመጥ ላይ የተመሰረተ አንድነት ተፈጥሮ የሁሉም ማህበረሰብ ችግሮችን በመነጋገር እና በሰላማዊ መልኩ ለመፍታት ጥረት ይደረጋል በተባለበት በዚህ ወቅት ሙስሊሙ ማህበረሰብ የሃገሪቱ ግማሽ አካል ቢሆንም እስካሁን የሙስሊሙ ማህበረሰብን ቅሬታዎች ለመፍታት የሚደረግ ጥረት ካለመታየቱ በተጨማሪ በአሸዋ ሜዳ የተከሰተው የመስጂድ ማፍረስ እና ሙስሊሙ ላይ ጥቃት የመፈፀሙ ተግባር መንግስት ለዘላቂ ሰላም እና ሃገራዊ መግባባት ሙስሊሙን ያማከለ ስራ እየሰራ አለመሆኑን አመላካች ነው፡፡ በቀደሙት አመታት በረመዳን ወራት በሙስሊሙ ማህበረሰብ ላይ የተፈፀሙት ግፎች ቁስል ሳይደርቁ ዘንድሮም የዚህን መሰሉ ተግባር በመንግስት ሃይላት መፈፀም መቀጠሉ በፅኑ የምናወግዘው ነው፡፡ እንደ ሙስሊም ዜጋ በሰላማዊ መንገድ ለመንግስት ያቀረብናቸው የመብት ጥያቄዎች በአዲሱ አመራር ምላሽ ይሰጥባቸዋል እንዲሁም ከሃይማኖት ነፃነት ጋር በተያያዘም እምነት ላይ ያነጣጠሩ ጥቃቶች እና ኢ ህገመንግስታዊ እርምጃዎች ይቆማሉ የሚል ፅኑ እምነት ሙስሊሙ
Tagged with: , ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ከሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ የተሰጠ መግለጫ

‹‹ለታላቁ የረመዳን ወር እንኳን አላህ አደረሰን!!›› ‹‹ጾሙ መላው ሙስሊም ማህበረሰብ በሁሉም የህይወት ዘርፍ በረከት እና ትሩፋት የሚያገኝበት እንዲሆን አላህን እንማጸናለን!›› አርብ ግንቦት 10/2010 አዲስ አበባ/ኢትዮጵያ በመጀመሪያ አላህ (ሱወ) ለተከበረው ታላቅ ወር ረመዳን ስላደረሰን ምስጋናችንን እናቀርባለን፡፡ ረመዳን የሰማያት በር የሚከፈቱበት፣ የጀሐነም በር የሚዘጋበት እና ኢብሊስም የሚታሰርበት የተባረከ ወር ነው፡፡ ረመዳን መላውን የሰው ዘር ከጭለማ ወደብርሃን ለማስገባት ለተላኩት ታላቁ ነቢይ ሙሐመድ (ሰዐወ) መመሪያ የሆነው ቁርአን የወረደበት፣ ኡማውም ለሰዎች ከተገለጹ ህዝቦች መካከል የበላይነትን የተጎናጸፈበት ክብር መገለጫነቱ የሚጎላበት ታላቅ ወር ነው፡፡ ታላላቅ ድሎች የተገኙበት እና በሙስሊሙ ልብ ውስጥ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው በጉጉት የሚጠበቅ ወርም ነው፡፡ ያለፉት ረመዳኖች ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ለዲናቸው ያላቸውን ቀናኢነት ያሳዩባቸው፣ እንዲሁም ለዲን መስዋእትነት የመክፈልን ክብር ያገኙባቸው እንደነበሩ የቅርብ ጊዜ ትዝታችን ነው፡፡ ለዲናችን ክብር ብለን የምንከፍላቸው መስዋእትነቶች ሁሉ በዱንያም ሆነ በአኼራ የሚያስከብሩን እንደመሆናቸው መጠን ሕዝባችን በከፈለው መስዋእትነት ታላቅ ክብር ይሰማናል፡፡ ይህ መስዋእትነት አላህ ዘንድ ተቀባይነት አግኝቶ ሁላችንንም በጭንቁ ቀን ሐዘን ከማያገኛቸው ባርያዎቹ እንዲያደርገን አጥብቀን እንለምነዋለን፡፡ ወደፊትም ሕዝባችን ለዲኑ መስዋእትነት የመክፈልን አስፈላጊነት ተረድቶ ሁልጊዜም ሙሉ ዝግጁነቱን እንደጠበቀ ሲኖር ማየት ምኞታችን ነው፡፡ አዎን! ለዲናቸው ሲሉ ጊዜያቸውን ከመስጠት አንስቶ ሕይወታቸውን እስከመሰዋት ለደረሱ ሁሉ አላህ (ሱወ) ምንዳቸውን አብዝቶ እንዲከፍላቸው፣ ምህረት እንዲለግሳቸው፣ ለቤተሰቦቻቸውም የተሻለ ምትክን እንዲያደርግላቸው አጥብቀን እንለምነዋለን፡፡ ይህ ረመዳንም ትክክለኛ ክብራችንን የምናገኝበት፣ እንዲሁም ለአገራችን ሰላምና ብልጽግና ከማንም በላይ አስተዋጽኦ ለማበርከት የምናደርገውን ጥረት የበለጠ በመጨመር ለተሻለ እርምጃ
Tagged with: , ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የሕወሓት የደሕንነት ቢሮው በሙስሊሞች ላይ አዲስ የማስፈራራትና የዛቻ ዘመቻ ጀምሯል።

↪የምሽት ሚስጢራዊ መረጃ የዛሬ ዛቻ ነገ እስርን ይወልዳል! ______________________________ ↪ዱዓቶቻችንና ወንድሞቻችን በጥበቃና ደህንነት ክፍሉ ጫናና ዛቻ እየደረሰባቸው መሆኑ ተገለፀ። ሙጂብ አሚኖ ዘ ኢስላም ______________________________ ↪ከ1997 ምርጫ አንስቶ የኢትዮጵያን ፖለቲካ በንቃት እየተከታተሉ የሚገኙት የፖርቱጋል ሶሻሊስት ፓርቲና የአውሮፓ ሶሻሊስት ፓርቲ አባል፤ እንዲሁም የአውሮፓ ፓርላማና የፓርላማው የውጭ ጉዳዮች ኮሚቴ አባል አና ማሪያ ሮሳ ጎምሽ የዶ/ር አብይ አሕመድ መሾም “ለኢትዮጵያም ሆነ ለኦሮሞ ሕዝብ በጎውን ሊያመጣ፣ ጥቅማቸውን ሊያስጠብቅ የሚችል ነው” የሚል ሃሣብ በብዙዎች ዘንድ እየተንፀባረቀ መሆኑን ጠቅሰው በመግለፅ “ጠቅላይ ሚኒስትሩ ግልፅ መልዕክቶችን ማስተላለፋቸው ጥሩ ምልክት ነው፤ ነገር ግን እስኪ ተግባሩን እንጠብቅ” ብለው ነበር ከጠቅላያችን ጣፋጭ ንግግር በስተጓዳኝ ትግበራው ላይ ጥርጣሪያቸውን አስምረው በማስቀመጥ ንግግራቸውን ያደረጉት። ↪እኛም በግላችን ለኢትዮጲያ ህዝብ እፁብ ድንቅ የዲሞክራሲ መርህ ይዞልን አዲሱ ጠቅላያችን ከተፍ ቢል ምንኛ ጮቤ እንደምንረግጥ ይታወቃል። ከዚህም በዘለለ ደግሞ ላለፉት ስድስት አመታት ህዝበ ሙስሊሙ ከአወሊያ የተማረዎች ንቅናቄ ጋር ተያይዞ ያነሳቸው የፍትህና የነፃነት ጥያቄ ጋር ተያይዞ በርካታ መጓተቶች ዛሬ ድረስ ተጉዘው መተዋል። በርካቶች ታስ�ረዋል፣ ተገርፈዋል፣ ተሰውተዋል፣ ከአይን ብሌናችን በላይ የምንሳሳላቸው እህቶቻችን አላህ በጀነት ይካሳቸውና ተደፍረዋል…ወዘ ተረፈ እኩይ ተግባራቶች ተፈፅመውብናል። ↪የኢህአዴግ መንግስት እስረኞችን ለበርካታ አመታት ከሌሎች እስረኞች በተለየ ሁኔታ /ባገለለ መልኩ/ አስሮ ካሰቃየ ቡሃላ ቀስ በቀስ ነጣጥሎ የኮሚቴውን አባላት በዚህ በያዝነው አመት አጠናቆ ፈቷል። ሌሎች ከዚህ እንቅስቃሴ ጋር ተያይዞ በእስር ላይ የነበሩ ወንድሞችና እህቶች ደግሞ እስራቸውን ጨርሰው የተፈቱ አሉ። ጥቂት የማይባሉት ደግሞ
Tagged with: , ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የህዝበ ሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባለት የዋልድባ ቄሶችን መዘየረያቸው ታውቁዋል።

በቅርቡ ከእስር የተፈቱት የኮሚቴው አመራሮች በዛሬው ዕለት በእስር የሚገኙትን የህዝበ ሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎች በዛሬው ዕለት በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት የሚገኙትን ንፁሃን ሙስሊም እስረኞች የመብት ተሟጓቾች የዋልድባ ቄሶችን መዘየረያቸው ታውቁዋል። Image may contain: 13 people, people smiling, text በሳለፍነው ግዜ እነዚህ ኡስታዞች በእስር ቤቱ በተደጋጋሚ ቢሄዱም በማረሚያ ቤቱን በሚመሩት ደህንነቶች “እናንተ ታስራቹህ ስለተፈታቹህ መግባት አትችሉም” በማለት በተደጋጋሚ መከልከላቸው ይታወቃል በዛሬው ዕለት ግን ወደ ስፍራው አመረወተው መግባታቸው ታውቁዋል በዛሬው ዕለት በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት የሚገኙትን የዋልድባ ቄሶች መዘየራቸው የታወቀ ሲሆን ቄሶቹም ለተደረገላቸው ዝያራ መደሰታቸው ታውቁዋል በሙስሊሙ መብት መከበር ሰሰብ የታሰሩ ሙስሊሞችን መዘየራቸው ታወቁዋል በዛሬው ዕለት በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ታስረው የሚገኙ ታሳሪዎችን የዘየሩት የህዝበ ሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባለት የኮሚቴው ህዝብ ሙስሊሙ ☞ኮሚቴ ፀሃፊ ኡስታዝ አህመድ ሙስጠፋ ☞የኮሚቴው ህዝብ ግንኙነት አህመዲን ጀበል ☞ኡስታዝ መሀመድ አባተ ☞ኡስታዝ ካሊድ ኢብራሂም መሆናቸው የታወቀ ሲሆን በቅርብ የተፈቱ ኮሚቴ አባላት በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ታሰው የሚገኙ ታሳሪዎችን መዘየራቸው ማህበረሰብ በቀጣይ ታሳሪዎችን መዘየር እና ማበሸር እንዳለበት ተገልፁዋል! >>>>>>>>>>>>>>> ፍትህ ለመላው ኢትዩጲያ
Tagged with: , , ,
Posted in Ethiopian News