ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ከፔይኒ ሞርዳንት ጋር ተወያዩ
የኢፌድሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ክብር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የእንግሊዝ ዓለምአቀፍ የልማት ተራድኦ ድርጅት (ዲ.ኤፍ.አይ.ዲ) ሃላፊ የሆኑት ፔይኒ ሞርዳንትን ዛሬ በፅ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ፡፡ የውይይቱ ማጠንጠኛ በኢኮኖሚ እና በድህነት ቅነሳ ዙርያ ላይ ያደረገ ነው፡፡ ፔይኒ ሞርዳንት በኢትዮጵያ ውስጥ የሚካሄደው ለውጥን አድንቀው የሚመሩት ድርጅት ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ያለውን ትብብር እንደሚያጠናክር ገልፀዋል፡፡