Blog Archives

ያለመታከት ለዘጠኝ አመት የአገር ሀብት እየተዘረፈ ነው ሲሉ የሚጮኹት ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣን ሰሚ አላገኙም ።

በምድረ በዳ የሚጮህ ሰው ድምጽ …………….. ሰሚ ሳይኖር ተስፋ ሳይቆርጥ ዝም ብሎ የሚጮህ ሰው ታውቃላችሁ ? እኚህ ሰው እንዲህ ናቸው ። አቶ ገመቹ ዱቢሶ ይባላሉ ። እናም እኚህ ሰው ላለፉት ሁለት አመታት አይደለም ፡ ሶስት አራት አመታትም አይደለም ። ስድስት ሰባት አመታትም አይደለም ። ይኸው የፌዴራል ዋና ኦዲተር ሆነው ከተሾሙ ከዛሬ ዘጠኝ አመት ጀምሮ አንድ ቀን ጩኸቴ ይሰማ ይሆናል እያሉ የኦዲት ሪፖርታቸውን ለምክር ቤቱ ሲያሰሙ ፡ ኸረ የህዝብ ገንዘብ እየጠፋ ነው ፡ ኸረ የመንግስት ሃብት እየተመዘበረ ነው እያሉ በተለያዩ ተቋማት ላይ በሚደረግ ምርመራ ላይ የሚገኘውን ጉድለት አቅርበው እርምጃ እንዲወሰድ አቤት ! እያሉ ይኸው አሉ ። ስለ እኚህ ሰው ሳስብ ጽናታቸው ይገርመኛል ። ሪፖርት ባቀረቡባቸው ተቋማት ላይ ከአመት አመት እርምጃ እንዳልተወሰደ እያወቁ ተስፋ ባለመቁረጥ ሁሌ እንደተናገሩ ነው ። አሁን አሁን ግን እኚህ ሰው ተስፋ ወደ መቁረጥ ተቃርበዋል ። ላለፉት ዘጠኝ አመታት እጮሃለሁ ነገር ግን ጩኸቴ ፍሬ አላፈራም እያሉ ነው ። በምድረ በዳ እንደሚጮህ ሰው ድምጽ ጩኸታቸው ሰሚ አላገኘም ። አቶ ገመቹ እንግዲህ ምን እንላለን ጽናቱን ይስጦት
Tagged with: , ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

‹‹እኔ መቼ ሙስና አሳሰረኝ፡፡ የማይሆን ክር ባልመዝ ኖሮ ጫፌን የሚነካኝ እንዳልነበረ ከእኔ በላይ የሚያውቅ አልነበረም፡፡›› አቶ ገብረዋሕድ

አቶ ገብረዋሕድ  በአጠቃላይ በስርዓቱ ዉስጥ አብረዋቸው ስለቆዩት ከፍተኛ ባለሥልጣናት የሐብት መጠን ሲዘረዝሩ ይቆዩና ‹‹እኔ መቼ ሙስና አሳሰረኝ፡፡ የማይሆን ክር ባልመዝ ኖሮ ጫፌን የሚነካኝ እንዳልነበረ ከእኔ በላይ የሚያውቅ አልነበረም፡፡›› ሲሉ በቁጭት እንደሚናገሩ ጽፏል፡፡ የዉብሸት ታዬ የግዞት ወጎች መጽሐፍ አታሚውም ሆነ አሳታሚውም በዉል አይታወቅም ‹‹ሞጋች እውነቶች›› ዋዜማ ራዲዮ– ከዛሬ አምሰት ዓመታት በፊት ሰኔ 12፣ 2003 ከሁለት ዓመት ሕጻን ልጁ ፊት በካቴና ታስሮ ወደ ማረሚያ ተወረወረ፡፡ ሽብርተኛ በሚልም የ14 ዓመት ፍርድ ተፈረደበት፡፡ በ2006 ዓ.ም. ‹‹የነጻነት ድምጾች›› የሚል መጽሐፉን ለንባብ አበቃ፡፡ ከ2 ዓመታት የእስር ቆይታ በኋላ ደግሞ ትናንት ረፋድ ላይ ‹‹ሞጋች እውነቶች›› የተሰኘውን መጽሐፍ ለአንባቢ አቀረበ፡፡ ጋዜጠኛ ዉብሸት፡፡ የመጽሐፉ ዋጋ 71 ብር መሆኑን የሚገልጽ መረጃ ከሽፋኑ ማግኘት ይቻላል፡፡ ‹‹ሞጋች እውነቶች›› የትኛው ማተሚያ ቤት እንደታተመ የሚገልጽ መረጃ ግን ፈልጎ ማግኘት አይቻልም፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየጠነከረ ከመጣው አፈና ጋር ተያይዞ ማተሚያ ቤቶች ስማቸው ፖለቲካዊ ይዘት ባላቸው መጽሐፎች ላይ እንዳይገለጽ አጥብቀው ይማጸናሉ፡፡ ‹‹ሞጋች እውነቶች›› የቀድሞው የአውራምባ ታይመስ ምክትል ዋና አዘጋጅ የዉብሸት ታዬ የግዞት ወጎች የተሰባሰቡበት ባለ 224 ገጽ መጽሐፍ ሲሆን እንደ አታሚው ሁሉ አሳታሚውም በዉል አይታወቅም፡፡ በመጽሐፉ የሽፋን ምስል ላይ ዶሮና አንበሳ በፍጥጫ ምልክ ሲጮኹ የሚያሳይ ፎቶ የሚታይ ሲሆን ይህንኑ ለማብራራ ይመስላል በመጀመርያው የመጽሐፍ ቅጠል እንዲህ የሚል መግለጫ ሰፍሯል- ‹‹ሁለቱም ቡድናቸውን ይመራሉ፤ ሁለቱም ለቡድናቸው ይፋለማሉ፡፡ አንዱ ጥሮ አዳሪ፣ ሌላው ሰብሮ አዳሪ ናቸው፡፡›› ዉብሸት ታዬ በእስር ሳለ አባቱን
Tagged with: , , , ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሌሎች አራት ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎችን ሹመት አነሱ

አቶ አባይ ፀሐዬ – የጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ የነበሩ አቶ ቴዎድሮስ ሀጎስ – የመለስ ዜናዊ አመራር አካዳሚ ፕሬዚደንት የነበሩ አቶ ጌታቸው አምባዬ- ጠቅላይ አቃቢ ህግ የነበሩ ኮሎኔል ታዚር ገ/እግዚአብሄር – የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት (ኢንሳ) ም/ዋና ዳይሬክተር የነበሩ ሲሆን ከሚያዚያ 12 ቀን 2010 ዓ.ም ጀምሮ ከሀላፊነታቸው መነሣታቸውን የሚገልፅ ደብዳቤ የደረሣቸው መሆኑን ተገልጿል፡፡ ህጋዊ ተጠያቂነትን ችላ በማለት በከፍተኛ ደረጃ የሃገርንና የሕዝብን ሃብትና ንብረት ሲዘርፉ የነበሩት የገዢው ፓርቲ አባላት ከስልጣን እየተነሱ በስርዓቱ ፉሮጎ ውስጥ በመሸሸግ ለተከታይ ዘረፋ መዘጋጀታቸውን ያሳያል፡፡ የሙስና ኔትወርክ በመዘርጋት ላለፉት ሃያሰባት አመታት የሃገሪቱን ኢኮኖሚ ገድለውታል፣ እንዲሁም በፖለቲካው መስክም በርካቶችን ገድለዋል፣ አስረዋል፣ አሰቃይተዋል፣ ፍትሕ እንዲጓደል ግንባር ቀደም ሚና ተጫውተዋል።
Tagged with: , ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News