ስደትና መፈናቀል እጣ ፈንታው የሆነው አማራ በቆቦ!
አማራነት ስዴት መከራና እንግልት ሆኗል ። አማራ እንኳን ከተኮለኮለለት ድንበር ውጭ በራሱም ባድማ ክብር ከተነፈገው ሁለት አስርተ አመታትን አስቆጥሯል ።
ሰሞኑን ከቤኒሻንጉል ጉምዝ በክልሉ መንግስት መዋቅር ተሳታፊነት ጭምር ኃብት ንብረታቸው ተወርሶ በግፍ ከተባረሩት ምንዱባን ኃዘንና ቁጭት ሳናገግም ከ406 በላይ የራያ አማራዎች ከኦሮሚያ ክልል ተፈናቅለው ያለ ታዛቢ ሜዳ ላይ ተበትነው ይገኛሉ ።
ከእነዚህ ተፈናቃዮች ውስጥ በጣት የሚቆጠሩት ብቻ መጠነኛ የመንግስት ድጋፍ የተደረገላቸው ሲሆን በርካታዎቹ በየቀበሌው ተበትነው አሳዛኝ ህይዎት እየገፉ እንደሚገኙ ተረድቻለሁ ።
የወገኖቻችንን ግፍና እንግልትጰ በመመከት የጀመርነው የማንነት ጉዞ የነዚህን ወገኖቻችንንም እምባ ሊያብስ ፣ ጠኔ ሊፈውስ ፣ጥም ሊያረካና እርዛት ሊሸፍን ይገባል የሚል ጽኑ እምነት አለኝ ። አማራ ለራሱ ለአማራ ሞልቶ ሲተርፍ በቅርቡ። አስተውለናል። ወደፊትም ይበልጥ እናያለን።
የተለመደው አኩሪ ትብብርና ድጋፋችን ፣ አለኝታነታችን ፣ ወገንተኝነታችን ለነዚህ ግፉዓን ሊደርሳቸው ይገባል ። ከዚህ ሰዓት ጀምሮ ድምጻችንን ከፍ አድርገን ስለነዚህ ወገኖቻችን እንድንጮህ ፣ እጃችንን እንድንዘረጋና ለርሃብና ጥማታቸው ፈውስ እንድንሰንቅ ወንድማዊ ጥሪየን አቅርቤያለሁ።
ጥሪየን በመቀበል፣ ጬኸቴን በማስተጋባት ኩራቶቼ እንደምትሆኑ በጽኑ አምናለሁ!
የቤኒሻንጉል ተፈናቃዮች መፍትሄ አላገኘንም ይላሉ
“ወደ ተፈናቀልንበት መመለስ ራስን ለሞት መስጠት ነው”
(ቄስ ምናለ አያሌው፤ ተፈናቃይ)
ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከማይ ዞን፣በለው ጅንጋፍወይ ወረዳ፣ ዴዴሳ ቀበሌ፣ ባለፈው ጥቅምት ወር በክልሉ ተወላጅ ወጣትና በአማራ ተወላጅ ወጣት መካከል በተፈጠረ ጠብ፣ የክልሉ ወጣት ህይወት ማለፉን ተከትሎ በተነሳ ግጭት 13 ሰው መሞታቸውን፣49 ከባድ