Blog Archives

“ኢትዮጵያዊነት የአማራ ፕሮጀክት ብቻ አይደለም” (ዶ/ር ደሣለኝ ጫኔ፤ የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ ሊቀመንበር )

ከሰሞኑ የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ (አብን) በባህር ዳር በተደረገ መስራች ጉባኤ የተመሰረተ ሲሆን የፓርቲውን ሊቀ መንበርና የስራ አስፈፃሚ አባላትንም መርጧል፡፡ ፓርቲውን በመመስረት ሂደት ውስጥ ተሳታፊ የነበሩ አሁን በሊቀ መንበርነት የተመረጡትን ጨምሮ 16 ሰዎች በኮማንድ ፖስት ታስረው መፈታታቸው የሚታወስ ሲሆን ፓርቲው ሲመሰረት የክልሉ መንግስት የመሰብሰቢያ አዳራሽ ትብብር አድርጎላቸዋል፡፡ ለመሆኑ የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ (አብን) አላማና ግብ ምንድን ነው? የትግል ስልቱስ? በሚሉና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ የፓርቲው ሊቀመንበር፣ የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ መምህሩን ዶ/ር ደሣለኝ ጫኔን፣ የአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ አለማየሁ አንበሴ በአጭሩ አነጋግሯቸዋል፡፡ የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄን (አብን) ለመመስረት ምክንያታችሁ ምንድ ነው? መሠረታዊ መነሻ ምክንያታችን፣ በአማራ ህዝብ ላይ ባለፉት ዓመታት እየደረሰ ያለው፣ ሁሉን አቀፍ የሆነ ግፍና መከራ ነው፡፡ የአማራ ህዝብ ህልውና አደጋ ውስጥ ወድቋል፡፡ ያንን ደግሞ በአግባቡ ይዞ መታገልና ለህልውናው መከበር የሚሠራ ድርጅት ስለሌለ፣ ክፍተቱን ለመሙላት ነው ድርጅቱን የመሰረትነው፡፡ የፓርቲያችሁ ዓላማና ግብ ምንድን ነው? ዓላማዎቹ ብዙ ናቸው፡፡ አንደኛው፤ አሁን የአማራ ህዝብ ከኢትዮጵያ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ሁኔታ ተገልሏል፡፡ ጥቅሞቹ እየተከበሩ አይደለም፤ ስለዚህ እነዚህን ጥቅሞቹን ማስከበር የመጀመሪያው አላማ ነው፡፡ ሁለተኛው፤ማንነታቸውን እየጠየቁ ያሉ አማሮች መገለጫዎቻቸው እየተከበሩ አይደለም። የአማራን ህዝብ ሁለተንናዊ ማንነት ማስከበርና ማስጠበቅ ሌላው ነው፡፡ ሌላው አጠቃላይ በአማራ ክልልም ሆነ ከክልላችን ውጪ ያሉ ወገኖቻችን የመገደል፣ የመሠደድ፣ የመፈናቀል፣ ሃብታቸው የመውደም ችግር እየደረሰባቸው በመሆኑ፣ እነዚህን የመመከት፣ የመከላከልና እንዲቆም የማድረግ ትግል ነው፡፡ የአማራ ህዝብ ለኢትዮጵያ የሚያበረክተውን ሁለንተናዊ አስተዋፅኦና በዚህች ሃገር ሊኖረው የሚገባውን ድርሻ ማሳደግም
Tagged with: , , ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

“ቄሮን እዚህ ያደረስነው እኛ ነን” – የመድረክና ኦፌኮ አመራር

· “ኦህዴድ የታችኛው መዋቅር ላይ ሙሉ ለውጥ ማምጣት አለበት” · “ኢትዮጵያዊነት ብሔር ብሔረሰቦችን ያቀፈ እንጂ ባዶ ቅል አይደለም” · “ያለፈውን ሥርዓት ሁሉ መውቀስ የለብንም በጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ሰሞነኛ እንቅስቃሴዎችና ንግግሮች ዙሪያ የመድረክና ኦፌኮ አመራሩ የቀድሞ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባልና የፓን አፍሪካ ፓርላማ አባል የተከበሩ አቶ ገብሩ ገ/ማሪያም ተከታዩን ቆይታ አድርገዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተለያዩ አካባቢዎች ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ያደረጉትን ስብሰባ እንዴት ይመለከቱታል? ንግግሮቹ እንደተባለው ተስፋ ጫሪ ናቸው። ተስፋ ጫሪ የሚያደርገው ሰውየው ወደ ስልጣን የመጡት ሃገሪቱ አጣብቂኝ ውስጥ ባለችበት ወቅት በመሆኑ ነው፡፡ በዚህ ወቅት የሁሉንም ህብረተሰብ ልብ የነካ ንግግር ማድረግ ትልቅ ነገር ነው፡፡ የህዝብን ተስፋ ያለመልማል፡፡ ጠ/ሚኒስትሩ በንግግራቸው ስለ ፍቅር፣ አንድነት፣ ይቅርታ ስለ ኢትዮጵያዊነት አንስተዋል፡፡ እነዚህ የሰው ልብ ውስጥ የራሳቸውን ቅሪቶች ፈጥሯል። ግን አካሄዱ ጥንቃቄ የሚያስፈልግ ነው፡፡ ጠንካራ የህዝብ እንቅስቃሴና ችግሮች በነበረባቸው አካባቢዎች ተንቀሳቅሶ፣ ከህዝብ ጋር መገናኘት ቀላል ግምት የሚሰጠው አይደለም፡፡ እኔ በበኩሌ ወድጄዋለሁ። ለመሪ ህዝብን በቀጥታ የማግኘት ያህል ጠንካራ ስራ የለም፡፡ ክልሎችን በማናገር ሂደት ውስጥ ጊዜም ቢወስድ ያለ ልዩነት ሁሉንም ማዳረስ ያስፈልጋል፡፡ አንዳንድ ወገኖች ጠ/ሚኒስትሩ ጥያቄ ያለውን ህዝብ ጋር በቀጥታ አላናገሩም፤ በስብሰባዎቹ እንደቀድሞው የፓርቲ አባላት ናቸው የተሳተፉት ሲሉ ይተቻሉ … በአንድ ጊዜ ሁሉንም ለውጥ ስለማልጠብቅ በአሁኑ አካሄድ ብዙም ችግር የለብኝም፡፡ በሚሊኒየም አዳራሽ 25 ሺህ ህዝብ ነበር፡፡ ሁሉም የፓርቲ አባላት አይመስሉኝም፡፡ ዋናው ጉዳይ ጠ/ሚኒስትሩ ቀጥሎ ከተቃዋሚ ፓርቲዎች ጋር የሚኖራቸው
Tagged with: , , , , ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News