የጅማ ፣ ባህርዳርና ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲዎች በሺዎች የሚቆጠሩ ተማሪዎችን አስመረቁ፡፡
ዩኒቨርሲቲዎቹ በመጀመሪያ ድግሪ ፣ በሁለተኛና ሶስተኛ ድግሪ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ናቸው፡፡
የጅማ ዩኒቨርስቲ 2 ሺ 182 ፣ የባህርዳር ዩኒቨርስቲ 11 ሺ 227 ተማሪዎችን እንዲሁም የሃዋሳ ዩኒቨርስቲ 8 ሺ 6ዐዐ ተማሪዎችን ነው በተለያዩ የሙያ ዘርፎች ያስመረቁት፡፡
ተመራቂ ተማሪዎቹም በሰለጠንበት ሙያ በሃገሪቱ የተጀመሩ የልማት ስራዎችን እንደግፋለን ብለዋል፡፡
የሃገሪቱን ሁለተንዊ ዕድገት ለማስቀጠል በትምህርት ጥራትና በሥነ- ምግባር የታነፀ ትውልድን ማፍራት ቅድሚያ ሊሰጠው እንደሚገባ በስነ ስርዓቱ ላይ ተመልክቷል፡፡
ebc ፤ etv