Blog Archives

በሰሜን ወሎ ወልዲያ የተፈጸመውን አሰቃቂ ግፍ ( የሰብአዊ መብቶች ጉባኤ )

በሰሜን ወሎ ወልዲያ የተፈጸመውን አሰቃቂ ግፍ የሰብአዊ መብቶች ጉባኤ እንደሚከተለው አጠናቅሮታል። የሰብአዊ መብቶች ጉባኤ በ145ኛ ልዩ መግለጫ የተመለከተው በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በሰሜን ወሎ ዞን የተለያዩ ወረዳዎች ውስጥ የተፈጸሙትን የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶችን ሲሆን የመብት ጥሰቱ የተፈጸመው ከሕዳር 24 ቀን 2010 ዓ.ም ጀምሮ እስከ የካቲት 04 ቀን 2010 ዓ.ም ድረስ ነው። ሰመጉ ባለሙያዎቹን ወደ አካባቢው ልኮ የማጣራት ሥራውን የሰራው ከየካቲት 05 እስከ የካቲት 12 ቀን 2010 ዓ.ም. ድረስ ባለው ጊዜ ውስጥ ነው፡፡ በዚህም መሰረት በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ወልደያ ከተማ፣ ወልደያ ዙሪያ ወረዳ፣ ቆቦ፣ ሮቢት፣ መርሳ፣ ውርጌሳ እንዲሆም በደቡብ ወሎ ደሴ የተፈጠሩት የሰብአዊ መብት ጥሰቶች መርምሮ በዚህ መግለጫ አካቷል። በዚህም መሰረት ከዚህ በታች የተሰነዘሩ17 ዜጎች እንደጠፋ እና የአካል ጉዳት እንደደረሰ ሪፖርቱ በምስል አስደግፎ አቅርቧል። 1. ሟች መምህር ታምሩ በሪሁን፡- ዕድሜ 42፣ በፌደራል ፖሊስ በጥይት የተገደለ። 2. ሟች ተማሪ ዮሴፍ እሸቱ፡- ዕድሜ 15፣ በታጠቁ የመንግስት ሀይሎች በጥይት የተገደለ። 3. ሟች ገብረመስቀል ጌታቸው፡- ዕድሜ 35፣ በታጠቁ የመንግስት ሀይሎች በጥይት የተገደለ። 4. ሟች ወ/ሮ ዝይን ንጋቴ፡- ዕድሜ 60፣ በመከላከያ ሰራዊት አባላት ጭንቅላታቸውን በጥይት ተመተው የተገደሉ። 5. ሟች ንጉሴ አበበ፡- ዕድሜ 18፣ በታጠቁ የመንግስት ኃይሎች ግራ ጎኑ ላይ በጥይት ተመትቶ የተገደለ። 6. ሟች ህጻን ዳንኤል ካሳ፡- ዕድሜ 9፣ ታጠቁ የመንግስት ኃይሎች ጀርባው ላይ በጥይት ተመትቶ የተገደለ። 7. ሟች ሰይድ ፍሬው ፡- ዕድሜ 31፣ በታጠቁ የመንግስት
Tagged with: , , , ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News