ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል ከአውሮፓ የቀውስ ሥራ አመራር ኮሚሽነር ጄኔዝ ሌናርሲች ጋር መወያየታቸው ተገለፀ
ዣኔዝ ሌናርቺች ወደ ትግራይ ክልል፣ መቐለ ከተማ በማቅናት ከዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ጋር መክረዋል።
የአውሮፓ ህብረት (EU) የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽነር በኢትዮጵያ ጉብኝት እያደረጉ ሲሆን ትላንትና በአዲስ አበባ ከኢትዮጵያ ምክትል ጠ/ሚ እና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ጋር ከመከሩ በኃላ ወደ ትግራይ ክልል መቐለ ተጉዘው ክልሉን ከሚያስተዳድሩት ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ጋር መክረዋል።
በውይይቱ የተለያዩ የጋራ ጉዳዮች መነሳታቸውን ከሚገልፅ መረጃ ውጭ ዝርዝር ነገር አልተገለፀም።
ኮሚሽነሩ ከውይይቱ ቀደም ብሎ የዓይደር ሪፈራል ሆስፒታል መጎብኘታቸውን የህወሓት ቃል አቀባይ አቶ ጌታቸው ረዳ ገልፀዋል።
ኮሚሽነር ጄኔዝ ሌናርሲች ቀደም ብለው በመቀለ ከተማ የሚገኘውን የአይደር ሆስፒታል መጎብኘታቸውንም ቃል አቀባዩ ተናግረዋል።
President Debretsion GebreMichael received & held constructive discussions with Mr Janez Lenarcic , European Commissioner for Crisis Management & Humanitarian Aid. Various Issues of mutual concern were raised during the discussion. Mr Lenarcic had earlier visited #AyderHospital. pic.twitter.com/E5buUKXGUy
— Getachew K Reda (@reda_getachew) June 21, 2022