የኦነግ አመራሮች ከእስር እንዲፈቱ ኢሰመኮ ጠየቀ

የኦሮሞ ነፃነት ግንባር አመራሮች በሕገወጥ እስር ላይ ስለሚገኙ፣ ‘በአፋጣኝ እንዲፈቱ’ ሲል የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።

ኮሚሽነር ዳንኤል በቀለን ጠቅሶ መግለጫ ያወጣው ኮሚሽኑ “አመራሮቹ ለረጅም ግዜ ከሕግ አግባብ ውጪ የታሰሩ በመሆኑ በአፋጣኝ እንዲፈቱ እና ለደረሰባቸው ጉዳት እንዲካሱ” በማለት አሳስቧል።

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ያወጣውን መግለጫ በተመለከተ ከኦሮምያ ፖሊስ ኮሚሽን እና ከኦሮምያ ጠቅላይ አቃቤ ሕግ ቢሮ ምላሽ ለማግኘት ያደረግነው ጥረት ግን ለግዜው አልተሳካም።