መንግስት በፋኖ ላይ የከፈተው የማጥቃት ዘመቻ የቀጠለ ሲሆን የፋኖ መሪዎችን ሲያጣ ሕፃናት ልጆቻቸውንና ቤተሰቦቻቸውን ማስፈራራትና ማሰር ጀምሯል። ፋኖ አስረስ ማረ ዳምጤ ቤተሰቡ ያጋጠመውን እንደሚከተለው አስፍሯል።
ከፍተኛ ቁጥር ያለው የዶ/ር ይልቃል ከፋለ ገዳይ ቡድን ከትላንት 8:00 ሰዓት ጀምሮ ቤቴን እንደከበበ ነው። ቤት ውስጥ የነበሩ ሁለት እህቶቸን ትላንት 3ኛ ፖሊስ ጣቢያ አስሯቸው ውሏል።
–
ከዚህም የከፋ ነገር ስለምጠብቅ ነገሩ አልገረመኝም። ሆኖም እስካፍንጫው የታጠቀ የፈሪ ተላላኪ የሰባት ዓመት ልጀን አባትሽን አሳይን ብለው ማስፈራራታቸውን ስሰማ ለኋላ ቀርነታቸው ከልቤ አዘንኩ።
–
ፅዮንሻ አይዞሽ ያንች ብቻ ሳይሆን የብዙ ኢትዮጵያውያን እጣ ፋንታ ነው።
ሁሉም የፋኖ አባል ካልተሰላ ግጭት እና መስዋዕትነት ራሱን አርቆ እንዲጠብቅ እመክራለሁ።