ልማት ባንክ ለ34 ሺሕ ሠልጣኞች 20 ቢሊዮን ብር ብድር አዘጋጀ
ባንኩ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች ብድር ወስደው ወደ ሥራ እንዲገቡ ለማድረግ ከግንቦት 1 እስከ 5 ቀን 2014 ዓ.ም. የሚቆይ ሥልጠና በመስጠት ላይ መሆኑን፣ በሥልጠናውም 34,000 ሠልጣኞች እንደሚሳተፉ የልማት ባንክ ፕሬዚዳንት ዮሐንስ አያሌው (ዶ/ር) ገልጸዋል። ከዓለም ባንክ ጋር በመተባበር የተዘጋጀው ሥልጠና በ20 ከተሞችና በ32 ማዕከላት በመላ አገሪቱ ለሦስተኛ ጊዜ የሚሰጥ መሆኑን አክለዋል።
–