በጦርነቱ የወደሙ የመንግሥታዊ ተቋማት መረጃዎች እንደገና እየተደራጁ መሆናቸው ተገለጸ

በጦርነቱ የወደሙ የመንግሥታዊ ተቋማት መረጃዎች እንደገና እየተደራጁ መሆናቸው ተገለጸ

በሰሜን ኢትዮጵያ በአማራና በአፋር ክልሎች ሲካሄድ በነበረው ጦርነት፣ በሕወሓት ታጣቂዎች ወድመዋል የተባሉትን የተቋማት መረጃ እንደገና ለማደራጀት የሚረዳ ጥናት እንዳደረገ ያስታወቀው የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን፣ በክልሎቹ ተቋማት የወደመውን መረጃ መልሶ የማደራጀት ሥራ መጀመሩን አስታወቀ፡፡