ሩሲያ ኢትዮጵያውያን ወዶ ዘማቾችን እየመለመለች ወይስ አጋርነታቸውን እየተቀበለች ?

የሩሲያ ኤምባሲ በር ላይ ኢትዮጵያዊያኑ ለምን ተሰለፉ ለሚለው ኤምባሲው አል-ዐይን አማርኛ ማብራሪያ ሰጥቷል

“ይህ አሳዛኝ ድርጊት ነው። አንድ ኢትዮጵያዊ በዚህ ጦርነት ህይወቱ ቢያልፍ ለዩክሬንም ሆነ ለኢትዮጵያ አሳዛኝ ክስተት ይሆናል።”የዩክሬን ኤምባሲ

ከሰሞኑ በአዲስ አበባ በሚገኘው የሩሲያ ኤምባሲ መግቢያ በር ላይ በርካታ ኢትዮጵያዊያን ሩሲያን ወግነው ዩክሬንን ለመውጋት ለመመዝገብ ወረፋ በመጠባበቅ ላይ ናቸው የሚል ምስል በማህበራዊ የትስስር ገጾች ላይ በመሰራጨት ላይ ይገኛል፡፡

አል ዐይን አማርኛ ጉዳዩን በሚመለከት በአዲስ አበባ በሚገኘው የሩሲያ ኤምባሲ ጠይቋል።

የኤምባሲው ፕረስ አታቼ ማሪያ ቸርኑኪና ለአል ዐይን እንዳሉት “ሩሲያ ለዩክሬን ጦርነት ኢትዮጵያዊያንን ለመቅጠር ማስታወቂያ አላወጣችም፣ በማህበራዊ ሚዲያዎች እየተሰራጨ ያለው መረጃም ሀሰተኛ ነው” ሲሉ ምላሽ ሰጥተውናል።

ነገርግን ኢትዮጵያውን ወደ ኢምባሲው መሄዳቸው እውነት መሆኑን ኢምባሲው ገልጿል፡፡

ኢትዮጵያውያን ወደ ሩሲያ ኢምባሲ የሄዱት ለምልመላ ሳይሆን ለሩሲያ ያላቸውን አጋርነት ለማሳየት መሆኑን የኤምባሲው ፕረስ አታቼ ገልጸዋል፡፡

ይሁንና ሩሲያ ከዩክሬን ጋር እያደረገችው ባለው ጦርነት “በርካታ ኢትዮጵያዊያን በኢሜይል እና በአካል ከሩሲያ ጎን መሆናቸውን እያሳወቁን ነው ለዚህ እናመሰግናለን” ሲሉም አክለዋል።

ኢትዮጵያዊያን ይሄንን እያደረጉ ያለው ረጅም እና ታሪካዊ በሆነው የኢትዮጵያ እና ሩሲያ ወዳጅነት ላይ ስለሚተማመኑ እንደሆነም ኤምባሲው ተገልጿል።

ዩክሬን የሰሜን አትላንቲክ ቃልኪዳን ጦርን ወይም ኔቶን እቀላቀላለሁ ማለቷን ተከትሎ ሩሲያ እና ዩክሬን ይፋዊ ጦርነት ከጀመሩ 54ኛ ቀኑን ይዟል።

እስካሁን ባለው ሂደት አምስት ሚሊየን ገደማ ዩክሬናዊያን ወደ ጎረቤት ሀገራት ሲሰደዱ በርካቶች ደግሞ ህይወታቸውን አጥተዋል።

ሩሲያ ከ23 ሺህ በላይ የዩክሬን ወታደሮችን እንደገደለች የተናገረች ሲሆን ዩክሬን በበኩሏ 20 ሺህ የሩሲያ ወታደሮችን ገድያለሁ ማለቷ ይታወሳል።

EthiopiaCheck Media Monitoring
አዲስ አበባ የሚገኙት የሩስያ እና ዩክሬን ኤምባሲዎች በዚህ ማህበራዊ ሚድያ ላይ በስፋት በተሰራጨ ምስል ዙርያ ለኢትዮጵያ ቼክ ምን አሉ?
ይህ ምስል ዛሬ በስፋት ማህበራዊ ሚድያ ላይ የተሰራጨ ሲሆን የሩሲያ ኤምባሲ የውጪ በር ላይ እነዚህ ኢትዮጵያውያን ወደ ሩሲያ ለመዝመት ለምዝገባ ተሰልፈው የሚያሳይ ምስል ነው ተብሏል። ምስሉ ላይ ዶክመንቶችን የያዙ በርካታ ሰዎች ይታያሉ።
ኢትዮጵያ ቼክ በዚህ ዙርያ አዲስ አበባ ከሚገኙት የሩስያ እና ዩክሬን ኤምባሲዎች መረጃ ጠይቋል።
የሩስያ ኤምባሲ መልስ: “እነዚህ ሰዎች ወደ ሩስያ ኤምባሲ የመጡት ለሩስያ እና [ለምታራምደው] ፖለቲካ ድጋፋቸውን በአካል ለማሳየት እና ለመግለፅ ነው። የተቻለውን ድጋፍ ሁሉ ለመስጠት ፍላጎታቸውን ገልፀዋል፣ ነገር ግን ኤምባሲያችን የቅጥር ድርጅት አይደለም። ለዚህ ድጋፍ ኤምባሲያችን ምስጋናውን ያቀርባል፣ ነገር ግን ምንም አይነት ቅጥር ኤምባሲያችን እያካሄደ አይደለም።”
የዩክሬን ኤምባሲ: “ይህ አሳዛኝ ድርጊት ነው። አንድ ኢትዮጵያዊ በዚህ ጦርነት ህይወቱ ቢያልፍ ለዩክሬንም ሆነ ለኢትዮጵያ አሳዛኝ ክስተት ይሆናል።”
May be an image of 6 people, people standing and outdoors