መንግሥት ጦርነቱ በክልሎች ላይ ያደረሰውን ጉዳት ፈረንሣይ እንድታጠና መጋበዙ ተነገረ

መንግሥት ጦርነቱ በክልሎች ላይ ያደረሰውን ጉዳት ፈረንሣይ እንድታጠና መጋበዙ ተነገረ
ለላሊበላ ውቅር አብያተ ቤተ ክርስቲያናት ዕድሳት ተጨማሪ በጀት ያስፈልጋል ተባለ
በአማራና በአፋር ክልሎች ሕወሓት በከፈተው ጦርነት በክልሎች ላይ የደረሰውን ጉዳት ፈረንሣይ እንድታጠና፣ ከፌዴራልና ከክልል መንግሥታት ጥያቄ እንደቀረበላት ተነገረ፡፡
እ.ኤ.አ. ከመጋቢት ወር 2022 እስከ መጋቢት 2023 ድረስ ለአንድ ዓመት በተለያዩ ሁነቶች (ክንውኖች) የሚከበረውን የኢትዮጵያና የፈረንሣይን 125ኛ ዓመት የዲፕሎማሲ ግንኙነት አስመልክቶ በተሰጠ መግለጫ ላይ እንደተነገረው፣ ካለፈው ዓመት ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም. የተጀመረውንና ቀጥሎ የሚገኘው ጦርነት ያደረሰውን ጉዳት መጠንና የወደሙ ንብረቶችና ተቋማትን መልሶ ለማቋቋም የሚያስፈልገውን ለማወቅ፣ ፈረንሣይ ጥናት እንድታካሂድ በፌደራልና የክልል መንግሥታት ጥያቄ መቅረቡ ተገልጿል፡፡
ተጨማሪ ያንብቡ: http://bit.ly/3i8cWSO