ኢትዮጵያ በተለያዩ ጊዜያት ወደ ህዋ ካመጠቀቻቸው ኹለት ሳተላይቶች የሚገኙ መረጃዎች አገልግሎት ላይ እየዋሉ አለመሆኑ ተገለጸ።

ኢትዮጵያ ካመጠቀቻቸው ሳተላይቶች የሚገኙ መረጃዎች ጥቅም ላይ እየዋሉ አይደለም ተባለ
ኢትዮጵያ ታኅሣሥ 10/2012 ያመጠቀቻት የመጀመሪያዋ ‹‹ETRSS1›› ሳተላይት እና ያንን ተከትሎ ከዓመት በኋላ የመጠቀችው ኹለተኛዋ ‹‹ET-Smart-RSS›› ሳተላይት የሚልኩትን መረጃ ወስዶ፣ አገራዊ ጥቅም ላይ የሚያውል ተቋም አለመኖሩን አዲስ ማለዳ ከተለያዩ ምንጮች አረጋግጣለች።
የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ለአዲስ ማለዳ እንደገለጸው፣ መረጃዎችን ከሳተላይቶች ተቀብሎ እና ተንትኖ መረጃ ቢያመርትም፣ መረጃዎች ለተፈለገው ዓላማ የሚጠቀም ተቋም የለም።