የታሰሩ ሰዎች እንዲፈቱላቸው በጠየቁ የቆቦ ወጣቶች አላማጣ ቆቦ መንገድ ተዘግቷል

የትግራይን ክልል ከአማራ ክልል የሚያገናኘው አላማጣ ቆቦ መስመር ለተሽከርካሪዎች ከተዘጋ 4 ቀናት አስቆጥሯል። መንገዱ የተዘጋው በአላማጣ ከተማ የታሰሩ ሰዎች እንዲፈቱላቸው በጠየቁ የቆቦ ከተማ ወጣቶች ነው ተብሏል።