የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር ዶክተር ይልቃል ከፋለ በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ጊታ ፓሲ ጋር በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ትኩረቱን ያደረገ ውይይት አድርገዋል።
–
በውይይቱ ርእሰ መሥተዳድር ይልቃል ከፋለ (ዶ.ር) አሸባሪው የትህነግ ወራሪ ኀይል በአማራ ክልል እያደረሰ ያለውን ሰብዓዊና ቁሳዊ ውድመት አስመልክቶ ለአምባሳደሯ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
–
በሽብር ቡድኑ የተፈናቀሉ ወገኖችን አስቸኳይ ሰብዓዊ ድጋፍ ማድረግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይም መክረዋል።
–