ብርጋዴር ጀነራል ከማል ገልቹ የኦሮሚያ አስተዳደርና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ ሆነው በክልሉ ርዕሰ መስተዳደር አቶ ለማ መገርሳ ተሾሙ።
በሶስት ፓርቲዎች ጥምረት የተመሰረተውን የኦሮሞ አንድነት ነፃነት ግንባር ሲመሩ የቆዩት ብርጋዴር ጀነራሉ፥ መንግስት ያቀረበውን የሰላም ጥሪ ተከትሎ በቅርቡ ወደ ሀገር ውሰጥ መግባታቸው የሚታወስ ነው።
ኤፍቢሲ እንደዘገበው ከዚህ ባለፈ ኮሎኔል አበበ ገረሱ በርዕሰ መስተዳድሩ የኦሮሚያ አስተዳደርና ፀጥታ ቢሮ ምክትል ኃላፊ ሆነው መሾማቸው ታውቋል።
ብርጋዴር ጀኔራል አሳምነው ጽጌ ሹመቱ የተሰጣቸው በጸጥታው ዘርፍ ያላቸውን የረዥም ጊዜ ልምድና ብቃትን ከግምት ውስጥ በማስገባት መሆኑን ከምንጮቻችን ባገኘነው መረጃ አረጋግጠናል፡፡
ብርጋዴር ጀኔራል አሳምነው ጽጌ የአማራ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ(አዴፓ) የማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ሆነው መመረጣቸው ይታወሳል፡፡