አርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳን ገድሏል የተባለው ጥላሁን ያሚ በዕድሜ ልክ ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ተወሰነ፡፡
በግድያው ተባብሯል የተባለው 2ኛ ተከሳሽ ከበደ ገመቹ ደግሞ በ 18 አመት ፅኑ እስራት የተቀጣ ሲሆን በወቅቱ ለፀጥታ አካል መረጃ ባለማሳወቅ ጥፋተኛ የተባለው 3ኛ ተከሳሽ አብዲ አለማየሁ ደግሞ በ 6 ወር ቀላል እስራት እንዲቀጣ ተወስኖበታል፡፡
የቅጣት ውሳኔውን ያሳለፈው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 2ኛ የፀረ ሽብርና የህገመንግስት ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ነው፡፡
ጋዜጠኛ ታሪክ አዱኛ