ሩሲያ ከኢትዮጵያ ጋር እያደረገችው ያለው የወታደራዊ ቴክኒክ ትብብር ከሕዳሴ ግድብ ጋር እንደሚያያዝ ተደርጎ የሚሰራጩ ዘጋባዎችን በኢትዮጵያ የሩሲያ ኢምባሲ ባሰራጨው መግለጫ አስተባብሏል።
О военно-техническом сотрудничестве с Эфиопией – Новости – Министерство иностранных дел Российской Федерации: https://t.co/VrmU7kfSnN pic.twitter.com/HEa0XkyhZR
— Russia in Ethiopia (@RusEmbEthiopia) July 27, 2021
የሁለቱ ሀገሮች ወታደራዊ ትብብር በማንም ላይ ስጋት የሚፈጥር እንዳልሆነ የገለጠው የኢምባሲው መግለጫ፣ ሩሲያ ከሱዳን እና ግብጽ ጋር ጭምር ተመሳሳይ የትብብር ስምምነቶች እንዳሏት ገልጧል።
የግድቡ ውዝግብ የሚፈታው በሦስትዮሹ የመርሆዎች መግለጫ እና በአፍሪካ ኅብረት ማዕቀፍ እንደሆነ፣ በኅብረቱ ማዕቀፍ ስር አስማሚ መፍትሄ የመገኘት እድሉም ገና እንዳልተሟጠጠ እና የግድቡን ግንባታ ፖለቲካዊ ገጽታ መስጠት እንደማይጠቅም ኢምባሲው ገልጧል።