በሰሜን ዕዝ ላይ በተሰነዘረው ጥቃት የተጠረጠሩ አራት ከፍተኛ የጦር መኮንኖች ከእስር ተለቀቁ

በአራት ከፍተኛ የጦር መኮንኖች ላይ ሲካሄድ የነበረው የወንጀል ምርመራ ተቋረጠ
***************
የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ወንጀል ምርመራ ቢሮ በተለያዩ ወንጀሎች ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የሚገኙ አራት ከፍተኛ የጦር መኮንኖች ላይ ሲያካሂድ የነበረውን የወንጀል ምርመራ ማቋረጡን አስታወቀ፡፡
ምርመራቸው እንዲቋረጥ እና ከእስር እንዲለቀቁ የተደረጉት የጦር መኮንኖች፦
1. ሜ/ጀ መሀመድ ኢሻ ዘይኑ ትኩእ
2. ብ/ጀ ሙሉጌታ በርሄ ይልማ
3. ኮ/ል ገ/እግዚአብሔር ገ/ሚካኤል እና
4. ኮ/ል ገ/ዋህድ ኃይሉ መሸሻ ናቸው፡፡
በጥቅምት 24 በሰሜን ዕዝ ላይ በተሰነዘረው ጥቃት ላይ ተሳትፈዋል ተብለው የተጠረጠሩት መኮንኖቹ የመከላከያ ሰራዊት ባደረገው ክትትል ተይዘው ለምርመራ ቡድኑ ተላልፈው የተሰጡ መሆናቸውን የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል፡፡
በዚሁ መሠረት ተጠርጣሪዎቹ ፈጸሙ በተባሉበት ወንጀል ምርመራ ሲካሄድባቸው የቆዩ ቢሆኑም የምርመራ ቡድኑ ባደረገው ማጣራት የወንጀል ተሳትፎአቸው ዝቅተኛ መሆኑን በመገንዘብ ምርመራው ተቋርጦ ከእስር እንዲለቀቁ መደረጉን ቢሮው በተለይ ለኢቲቪ ገልጿል፡፡
May be an image of outdoors