የጥምቀት በዓል በዓለም ላይ በእምነታችን የምንታወቅበት ታላቅ በዓል ነው – ብጹዕ አቡነ ማቲያስ
–
(ኢዜአ) “የጥምቀት በዓል በዓለም ላይ በእምነታችን የምንታወቅበት ታላቅ በዓል ነው” ሲሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ ብጹዕ አቡነ ማቲያስ ገለጹ።
–
የከተራ በዓል በመላው ኢትዮጵያ በድምቀት ተከብሯል።
–
በአዲስ አበባ ጃንሜዳ በተከበረው የከተራ በዓል ላይ መልዕክት ያስተላለፉት ብጹዕ አቡነ ማቲያስ “ይህ በዓል ዓለም ዓቀፍ በዓል ሆኗል” ሲሉ ባለፈው ዓመት በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ ሳይንስና ባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) መመዝገቡን አስታውሰዋል።
–
የጥምቀት በዓል በዓለም ዓቀፉ ማህበረሰብ ዘንድ የሚታወቅ በመሆኑ በርካታ ቱሪስቶች የሚታደሙበት እንደሆነ ገልጸዋል።