መንግሥት በኢትዮ-ሱዳን ድንበር ከአካባቢ ሚሊሻ ጋር የተፈጠረውን ክስተት በቅርበት እየተከታተለው መሆኑን ጠቅላይ ሚስትር ዐቢይ አህመድ አስታወቁ፡፡”ክስተቱን እንደ መልካም አጋጣሚ ወስደው በማራገብ ልዩነትን ለማስፋት የሚጥሩ አካላት የሁለቱን ሀገራት ታሪካዊ ትስስር ያልተረዱ ናቸው” ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፡፡”ሁለቱ ሀገራት እንዲህ ያሉ ችግሮችን ለመፍታት ሁሌም የውይይትን አማራጭ የሚከተሉ በመሆናቸው ክስተቱ የሁለቱን ሀገራት ጥብቅ ትስስር አያላላውም” ብለዋል ጠቅላይ ሚስትሩ በትዊተር ገፃቸው ላይ ባሰፈሩት አስተያየት፡፡
The gov’t is closely following the incident with local militia on the Ethio-Sudan border. Such incidents will not break the bond b/n our two countries as we always use dialogue to resolve issues. Those fanning discord clearly do not understand the strength of our historical ties.
— Abiy Ahmed Ali 🇪🇹 (@AbiyAhmedAli) December 17, 2020