እነጀዋር መሀመድ በአቅራቢያችን ችሎት ጉዳያችን ይታይልን ብለው ያቀረቡት ጥያቄ ውድቅ ሆነ
የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድቤት ልደታ ምድብ አንደኛ የህገመንግስትና የፀረ ሽብር ወንጀሎች ጉዳይ ችሎት የእነ ጀዋር መሀመድን ጉዳይ ዛሬ ተመልክቷል፡፡
–
ከዚህ በፊት አቶ ጀዋር መሀመድ፣ በቀለ ገርባ፣ ሀምዛ አዳነ እና ሸምሰዲን ጠሀ ባቀረቡት የጽሁፍ አቤቱታ ለደህንነታችን ስለምንሰጋ ችሎቱ በአቅራቢያችን ይሁንልን ሲሉ መጠየቃቸው ይታወሳል፡፡
–
ይህንን የመረመረው ችሎቱ ጥያቄያቸውን ውድቅ በማድረግ በዚሁ ችሎት ጉዳያቸው እንዲታይ አዝዟል፡፡
ለጥር 4 ቀን 2013 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
–
ዛሬ አራቱ ተጠርጣሪዎች በችሎቱ ያልተገኙ ሲሆን በመዝገባቸው ስር የተካተቱ ቀሪዎቹ ግን ተገኝተዋል ሲል የዘገበው ኤፍ ቢ ሲ ነው።