ምርጫ በትግራይ ክልል
ረቡዕ ጳጉሜ 4 ቀን፣ 2012 ዓ:ም
–
DW : በትግራይ ምርጫ ዛሬ ጠዋቱ ከ12 ሰዓት ጀምሮ ኅብረተሰቡ ድምፅ እየሰጠ ነው፡፡
–
ጠንካራ ፉክክር ይኖርባቸዋል ተብለው ከሚጠበቁ የትግራይ ከተሞች አንዷ በሆነችው ዓዲግራት ሕዝብነዋሪው ከንጋቱ 11 ሰዓት ጀምሮ ድምፁን ለመስጠት ተሰልፎ ሲጠባበቅ እንደነበር በሥፍራው የሚገኘው የዶይቸ ቬለ (DW) የአማርኛው ክፍል ዘጋቢያችን ተመልክቷል፡፡
–
ከተቀረው ኢትዮጵያ ተለይታ ክልላዊ ምርጫ በምታካሂደው ትግራይ የድምፅ አሰጣጥ ሂደት እየተካሄደ ይገኛል፡፡
–
የመሪ ድርጅቱ ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ /ህወሓት መሪ እና የክልሉ ፕሬዚዳንት ደብረፂዮን ገብረሚካኤል (ዶ/ር) ለመወዳደር በተመዘገቡበት አደዋ የምርጫ ክልል በመገኘት በማለዳው ድምፃቸውን ሰጥተዋል፡፡
–
–
ዶክተር ደብረፂዮን ድምፃቸውን ከሰጡ በኋላ በስፍራው ለተገኙ ሚዲያዎች “የትግራይ ክልላዊ ምርጫ የማንንም ወገን ዕውቅና እና ይሁንታ የማይፈልግ የትግራይ ህዝብ ብቻ የሚወስንበት ዴሞክራሲያዊ ሂደት ነው” ብለዋል፡፡
–
2.7 ሚሊየን መራጮች በተመዘገቡበት የትግራይ ምርጫ ገዢ ድርጅቱ ህወሓትን ጨምሮ 5 የፖለቲካ ፓርቲዎች እየተሳተፉ ይገኛል፡፡
–
የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱ እስካሁን ሠላማዊ መሆኑን የክልሉ መገናኛ ብዙሃን የዘገቡ ሲሆን መራጩ ህዝብም ከንጋቱ ጀምሮ በየምርጫ ጣቢያዎች ተገኝቶ ለቀጣይ 5 ዓመታት ትግራይን ያስተዳድርልኛል ብሎ ላመነበት ፓርቲ ድምፁን እየሰጠ ይገኛል፡፡