ለአ/አበባ ሀ/ስብከት ችግሮች አጣሪ ኮሚቴ ሰብሳቢው፣ ከሀገረ ስብከቱ ገቢ እንዲከፈላቸው የታዘዘው 50ሺሕ ብር እያነጋገረ ነው

መጋቤ ካህናት ኀይለ ሥላሴ ዘማርያም፣የአጣሪ ኮሚቴው ሰብሳቢ ናቸው፤ ለኮንዶሚኒየም ግዥ የተበደሩትን መክፈል ስላቃታቸው ርዳታ ተፈቀደላቸው፤ ገንዘቡ የሚከፈላቸው ከሀገረ ስብከቱ ገቢ ላይ ሲኾን፣ማጣራቱ ግን አላለቀም፤ ለምን ከጠቅላይ ጽ/ቤቱ አይከፈልም?በምንስ አግባብ ሊፈቀድላቸው ቻለ? ††† ሌሎች ሊቃውንትና ሠራተኞችስ በተመሳሳይ ቢጠይቁ ይፈቀድላቸዋል ወይ? ኮንዶሚኒየም ከገዙ፣የተከራዩትን የጠቅላይ ጽ/ቤቱን ቪላስ ያስረክባሉ ወይ? “ልዩ ሀ/ስብከት ካልተነሣ የፓትርያርኩ የጓሮ ሽንኩርት መኾኑን ይቀጥላል፤” “የመዋቅር …