መጋቤ ካህናት ኀይለ ሥላሴ ዘማርያም፣የአጣሪ ኮሚቴው ሰብሳቢ ናቸው፤ ለኮንዶሚኒየም ግዥ የተበደሩትን መክፈል ስላቃታቸው ርዳታ ተፈቀደላቸው፤ ገንዘቡ የሚከፈላቸው ከሀገረ ስብከቱ ገቢ ላይ ሲኾን፣ማጣራቱ ግን አላለቀም፤ ለምን ከጠቅላይ ጽ/ቤቱ አይከፈልም?በምንስ አግባብ ሊፈቀድላቸው ቻለ? ††† ሌሎች ሊቃውንትና ሠራተኞችስ በተመሳሳይ ቢጠይቁ ይፈቀድላቸዋል ወይ? ኮንዶሚኒየም ከገዙ፣የተከራዩትን የጠቅላይ ጽ/ቤቱን ቪላስ ያስረክባሉ ወይ? “ልዩ ሀ/ስብከት ካልተነሣ የፓትርያርኩ የጓሮ ሽንኩርት መኾኑን ይቀጥላል፤” “የመዋቅር …