ዶ/ር ፍቅሩ ማሩ በ9 ሚሊየን ዶላር የህክምና ማሰልጠኛ ተቋም ሊከፍቱ ነው!

ዶ/ር ፍቅሩ ማሩ በ9 ሚሊየን ዶላር የህክምና ማሰልጠኛ ተቋም ሊከፍቱ ነው!

ለአገር አሳቢ የሆኑትን ዶክተር ፍቅሩ ማሩን ፍቱ ብለን ስንጮህ የነበረው ለዚህ ነው። ትልቅ ሰው ምን ጊዜም ትልቅ ነው። በሃሰት ክስ ተወንጅለው በእስር ሲንገላቱ የነበሩት ዶክተር ፍቅሩ ማሩ ከወራት በፊት መፈታታቸው ይታወቃል።

ያ ሁሉ መከራ የደረሰባቸው ዶክተር ፍቅሩ ማሩ ቂም አልያዙም አላኮረፉም። ዶክተር ፍቅሩ ማሩ በዘጠኝ ሚሊዮን ዶላር የሕክምና እና የማሰልጠኛ ማዕከል ሊከፍቱ ተዘጋጅተዋል። አምስት ዓመታት በእስር ያሳለፉት የሕክምና ባለሙያ ልባቸው በአገራቸው አልጨከነም። ከአዲሱ ጤና ጥበቃ ሚኒስትር ዶ/ር አሚር ጋር በዚህ ጉዳይ ላይ መወያየታቸውን ዶክተር አሚር በቲዊተር ገጹ አስታውቋል።

አብዱረሂም አህመድ።