ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ የጅቡቲ ዓለም አቀፍ ነፃ የንግድ ቀጠና ማዕከል ምረቃ ላይ ተገኙ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ የጅቡቲ ዓለም አቀፍ ነፃ የንግድ ቀጠና ማዕከል ምረቃ ላይ ተገኙ

በ340 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ወጪ የተገነባውን የጅቡቲ ዓለም አቀፍ ነፃ የንግድ ቀጠና ማዕከል ዛሬ ተመርቋል።

በምረቃው ላይ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ፣ የሱዳኑ ፕሬዝዳንት ኦመር ሀሰን አልበሽር፣ የሱማሊያው ፕሬዝዳንት መሀመድ አብዱላሂ፣ የአፍሪካ ህብረት የወቅቱ ሊቀመንበርና የሩዋንዳ ፕሬዚዳንት ፖል ካጋሜን የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ኮሚሽነር ሙሳ ፈቂ ማሃማት ተግኝተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ በምረቃው ላይ፥ ጅቡቲ ዓለም አቀፍ ነፃ የንግድ ቀጠና ማዕከል በማስገንባቷ የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት አስተላልፈዋል። ማእከሉ ለጅቡቲ ብቻ ሳይሆን ለቀጣናው ሀገራትም የጋራ ሀብት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ፥ ኢትዮጵያ ማእከሉ እንደራሷ ፕሮጀክት ትቆጥራለች ብለዋል።
#FBC