ለ14 ቀናት የነበረውን አስገዳጅ የለይቶ ማቆያ ወደ 7 ቀናት ብቻ እንዲሆን ተወስኗል።
–
ኢዜአ — በተለያዩ ምክንያቶች ለሞት የሚዳረጉ ዜጎች አስፈላጊውን ጥንቃቄ በማድረግ በማህበረሰቡ የቀብር ሥነ-ሥርዓት እንዲፈጸም ተፈቀደ።
–
የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል በወጣው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ሥር ባሉ አንዳንድ መመሪያዎች ላይ ማሻሻያ መደረጉን የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ ተናግረዋል።
–
የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ በዛሬው ዕለት ለኢዜአ በሰጡት መግለጫ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አፈጻጸም መመሪያዎች ላይ ማሻሻያ መደረጉን ተናግረዋል።
–
በማሻሻያው መሰረት በተለያዩ ምክንያቶች ለሞት የሚዳረጉ ዜጎች አስፈላጊውን ጥንቃቄ በማድረግ በማህበረሰቡ የቀብር ሥነ-ሥርዓት መፈጸም ተፈቅዷል።
–
ይህም ከዚህ ቀደም የአስክሬን የላብራቶሪ ውጤት ከመምጣቱ በፊት የቀብር ሥነ-ሥርዓት መፈጸም አይቻልም የሚለውን መመሪያ መሻሻሉን ዶክተር ሊያ ተናግረዋል።
–
ይሁን እንጂ በቀብር ሥፍራ ላይ ከዚህ ቀደም የተቀመጠው 50 ሰዎች ብቻ ተገኝተው ሥርዓቱን ማካሄድ አለባቸው የሚለው መመሪያው አልተሻሻለም ብለዋል።
–
ግለሰቦች በኮሮና ቫይረስ ቢያዙ የሚያገለግሏቸው የቤተሰብ አባላትንና የራሳቸውን ፍላጎት ከግምት በማስገባት ተፈጻሚ የሚሆን መሆኑንም ጠቅሰዋል።
–
የግሰለቦችን የአኗኗር ሁኔታ በተቀመጠው መመሪያ መሰረት አግባብ ከሆነ በቤታቸው እንዲቆዩ እንደሚደረጉም ተናግረዋል፡፡
ከውጭ የሚገቡ ሰዎች በተለይም ወደ አገር ከገቡ በኋላ ባለፉት 3 ቀናት ውስጥ ከመጡበት አገር ተመርምረው ነጻ መሆናቸውን የሚያሳይ መረጃ ይዘው ከመጡ ናሙና ተወስዶ በቤታቸወ 14 ቀናት እንዲቆዩ ይደረጋልም ተብሏል።
–
በሌላ በኩል ነጻ መሆናቸውን የሚያረጋገጥ ሪፖርት ይዘው ለማይመጡ መንገደኞች ናሙናቸው ተወስዶ ለሰባት ቀናት በለይቶ ማቆያ እንዲቆዩ ይደረጋል ብለዋል ዶክተር ሊያ።
–
ይህም ከዚህ ቀደም ለ14 ቀናት የነበረውን አስገዳጅ የለይቶ ማቆያ ወደ 7 ቀናት ብቻ እንዲሆን ተወስኗል።