ምዕራብ ሆቴል አካባቢ የሚገኝ የአንድ ባንክ ሰራተኛ በኮሮና ቫይረስ መያዛቸውን ተከትሎ በባንኩ ሰራተኞች ላይ ከፍተኛ ድንጋጤ ተፈጥሯል
–
የጥበቃ ሰራተኛ የሆኑት ይህ ሰው የአብነት አካባቢ ነዋሪ ሲሆኑ ለምርመራ ናሙና ሰጥተው እንደነበርና ናሙና መስጠታቸውን ሳይናገሩ እስከዛሬ ጠዋት ድረስ በስራ ገበታቸው ላይ እንደነበሩ የባንኩ ሰራተኞች ለናፍቆት ሚዲያ ገልፀዋል::
–
የባንኩ ሰራተኞች እንደሚሉት የየባንኩ የጥበቃ ሰራተኛ በቫይረሱ መያዛቸውን የናሙና ውጤታቸው ያረጋገጠ ሲሆን የጤና ቢሮ ሰዎች ሰውየውን ለመውሰድ መጥተው የነበረ ሲሆን ሰውየው ስራ አድረው ዛሬ ጠዋት ወደቤታቸው መሄደቸውን ሰራተኞቹ ገልፀውልናል:: ይህን ተከትሎ ባንኩ ወዲያው በሩን ዘግቶ የሚሆነውን ሲጠብቅ የነበረ ሲሆን በሗላም የባንኩ ሃላፊዎች ሰራተኞቻቸውን ከ14 ቀን በፊት ወደስራ እንዳይመጡ ነግረው ማሰናበታቸውንም ምንጮቻችን ገልፀዋል::
–
በአሁኑ ወቅት ቫይረሱ በማህበረሰብ ደረጃ ስርጭት መጀመሩንና የዚህም ማሳያው አብዛኞቹ ተጠቂዎች የጉዞ ታሪክም ሆነ በቫይረሱ ከተያዘ ሰው ጋር ንክኪ የሌላቸው መሆኑን የኢትዮጵያ ህክምና ሳይንስ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ተግባሩ ይግዛው የዛሬው አዲስ አድማስ ላይ ባደረጉት ቆይታ ተናግረዋል!!
ናፍቆት ሚዲያ