የሶማሌ ክልል ነዋሪዎች እውነተኛ ፌደራሊዝምን ለመተግበር እየሰራ ያለውን ብልፅግናን እንደግፋለን በማለት ዛሬ በጅግጅጋ የድጋፍ ሰልፍ እያካሄዱ ነው። በድጋፍ ሰልፉ ላይ ከተለያዩ የከተማዋና አካባቢዋ ቀበሌዎች የተውጣጡ ነዋሪዎች መሳተፋቸው ታውቋል። በሰልፉ ላይ የክልሉ ምክትል ርእሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ መሃመድ እና ሌሎች ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።