ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢህአዴግ በሚዋሐደዉ ፓርቲ ቁልፍ የፕሮግራም አቅጣጫዎች ዙሪያ ተመካክሮ ማጽደቁን አብስረዋል።

የኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ በዛሬ ውሎው በሚዋሐደዉ ፓርቲ ቁልፍ የፕሮግራም አቅጣጫዎች ዙሪያ ምክክር ተደርጎ መፅደቁን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ አስታወቁ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በይፋዊ የፌስቡክ ገፃቸው እንደገለፁት ኮሚቴው ከትላንቱ የፓርቲ ውሕደት ወሳኝ ውይይት በመቀጠል ዛሬም በሚዋሐደዉ ፓርቲ ቁልፍ የፕሮግራም አቅጣጫዎች ዙሪያ ተመካክሮ ማጽደቁን አብስረዋል።

አዲሱ ፓርቲ የኢትዮጵያን የፌደራል ሥርዓት እና ዴሞክራሲን ያጠናክራል፤ አካታች ሆኖ ብዝኃነታችንን ያከብራል፤ ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኅብረ ብሔራዊነትን ያከበረ አንድነትን መሠረት እንደሚያደርግም ገልፀዋል።

*******************************************************************

የኢትዮጵያ ብልፅግና ፓርቲ የመተዳደሪያ ደንብን ከታች ያለውን ሊንክ/ምስል በመጫን ማውረድ (Download) ይቻላል።
ምንጭ፦ Addis Standard

Please click here to download draft copy of “Prosperity Party Regulation” exclusively obtained by Addis Standard