“ኃላፊነት የተሞላበት ትዕግስታችን ፍርሐት ከመሰላችሁ መሳሳታችሁን ለማሳየት ከባድ አይሆንብንም!” ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ

“ኃላፊነት የተሞላበት ትዕግስታችን ፍርሐት ከመሰላችሁ መሳሳታችሁን ለማሳየት ከባድ አይሆንብንም!”
ዶክተር ደሳለኝ ጫኔ

“ኃላፊነት የተሞላበት ትዕግስታችን ፍርሐት ከመሰላችሁ መሳሳታችሁን ለማሳየት ከባድ አይሆንብንም!”
ዶክተር ደሳለኝ ጫኔ

የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ ሊቀመንበር ዶክተር ደሳለኝ ጫኔ በትዊተር ገጻቸው “የአብን አመራሮች እንዲፈቱ ከመንግስት ጋር ብንስማማም ተግባራዊ መሆን አልቻለም ፣ ስለሆነም ቀጣዩ እርምጃ ህዝባዊ እምቢተኝነት ነው” ብለዋል። የእንግሊዘኛ ሙሉ መግለጫቸውን ወደ አማርኛ ተርጉመነዋል፣ እነሆ!

“የአብን አመራሮች ከታላላቅ የመንግስት ባለስልጣናት ጋር የታሰሩ መሪዎቻችን እንዲለቀቁልን ተነነጋግረን ነበር። በስምምነታችን መሰረትም ከአርብ በፊት እንደሚፈቱ ተወስኖ ነበር ፣ ነገር ግን ስምምነቱ ተግባራዊ አልተደረገም።

ኢትዮጵያ ውስጥ አሁን ባለው ያልተረጋጋ ፖለቲካ ወደፊት ለመጓዝ ውይይት እና ድርድር ብቸኛ አማራጮች ናቸው ብለን እናምን ነበር ፣ ግን ያ አልሆነም። ስለዚህ ቀጣዩ እርምጃ በህገወጥ መንገድ የታሰሩብን መሪዎችን ለማስፈታት የራሳችንን እርምጃ መውሰድ ነው። ኃላፊነት የተሞላበት ትዕግስታችን ፍርሐት ከመሰላችሁ መሳሳታችሁን ለማሳየት ከባድ አይሆንብንም!” ብለዋል።