መረጃ የማይሰጡ ተቋማትና ኃላፊዎች በህግ ይጠየቃሉ

መረጃ የማይሰጡ ተቋማትና ኃላፊዎች በህግ ይጠየቃሉ
• የሚዲያ ህግ ማሻሻያ እየተደረገ ነው
(ኢ.ፕ.ድ)

አዲስ አበባ:- በመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች መረጃ ሲጠየቁ ለመስጠት ፈቃደኛ ያልሆኑ የተቋማት ኃላፊዎች በህግ ሊጠየቁ እንደሚገባ ተጠቆመ። የመረጃ አሰጣጥ ስርዓቱን ለማሳለጥ የሚዲያ ህጉ ላይ ማሻሻያ እየተሰራ መሆኑም ተጠቁሟል።

የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ የህዝብ ግንኙነትና ኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ዝናቡ ቱኑ ለአዲስ ዘመን እንደተናገሩት በየተቋማቱ ያለው መረጃ የህዝብ ሀብት እንጂ የግለሰብ ንብረት አይደለም። በመሆኑም መረጃ ለህዝብ ጥቅም ተብሎ ሲፈለግ ወይም ህዝቡ ማወቅ እፈልጋለሁ ይሰጠኝ ሲል መረጃውን የያዙ ኃላፊዎች የመስጠት ግዴታ አለባቸው።

አቶ ዝናቡ ቱኑ እንደሚሉት የመንግሥት ተቋማት ቀዳሚ ተልእኮው ህዝብን ማገልገል፣ የህዝብን ደህንነት መጠበቅ እና የህዝብን ጥያቄ መመለስ በመሆኑ ህዝብ ለሚያቀርበው ጥያቄ ሁሉ ተገቢውን ምላሽ መስጠት ይጠበቅባቸዋል።

ለተጨማሪ ንባብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/Ama/?p=21135