ነፃነት ወርቅነህና የቤተሰብ ጨዋታ ከኢቢኤስ ቴሌቭዥን ጋር ፍቺ ፈጸሙ ተባለ

ነፃነት ወርቅነህና EBS TV ተለያዩ

ለ3 ዐመት ያህል በEBS ቴሌቪዥን ሲተላለፍ በነበረው “የቤተሰብ ጨዋታ” የቴሌቪዥን ፕሮግራም አዘጋጅነት የሚታወቀው አርቲስት ነፃነት ወርቅነህ ከEBS ቴሌቪዥን ጋር መለያየቱ ተሰምቷል።

አርቲስቱ በኢትዮ ኤፍ ኤም ራድዮ ጣቢያ በሚተላለፈው ታዲያስ አዲስ ፕሮግራም ላይ በያዝነው አዲስ አመት በአዲስ የፕሮግራምና በአዲስ የቴሌቪዥን ጣቢያ ብቅ እንደሚል ተናግሯል።

መስከረም ወር አጋማሽ ይጀምራል የተባለው ይኸው አዲስ ፕሮግራሙ በናሁ ቴሌቪዥን እንደሚተላለፍ ከታዲያስ አዲስ ለመስማት ተችሏል።

ምንጭ፦ ኢትዮ ኤፍ ኤም ፤ ታዲያስ አዲስ