የ2012 መግቢያ ነጥብ!
የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር የ2012 የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ነጥብን በዛሬው እለት ይፋ አደረገ።
በዚሁ መሰረት፦
በተፈጥሮ ሳይንስ •ለወንድ 176 •ለሴት 166
ማህበራዊ ሳይንስ •ለወንድ 174 •ለሴት 164
ለታዳጊ ክልሎች
√በተፈጥሮ ሳይንስ •ለወንድ 166 •ለሴት 156 √
በማህበራዊ ሳይንስ •ለወንድ 164 •ለሴት 154
ልዩ መቁረጫ ነጥብ
መስማት ለተሳናቸው
በተፈጥሮ እና በማህበራዊ ሳይንስ •ለወንድ 120 •ለሴት 115
አይነ ስውራን
በማህበራዊ ሳይንስ ብቻ •ለወንድ 110 •ለሴት 105
ለግል ተፈታኞች
በማህበራዊ እና በተፈጥሮ ሳይንስ •ለወንድ 190 •ለሴት 185
አጠቃላይ ወደ ግል የትምህርት ተቋማት ገብተው ለመማር ለሚፈልጉ የማለፊያ መቁረጫ ነጥብ ደግሞ 140 መሆኑን የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል። ሚኒስቴሩ በመግለጫው ላይ እንዳስታወቀው፥ በዘንድሮው ዓመት በአጠቃላይ ወደ መንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሚገቡ ተማሪዎች ቁጥር 142 ሺህ 821 ነው።
የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች መግቢያ በአራት መሰረታዊ የትምህርት አይነቶች ውጤት መሠረት አድርጎ እንደሚወሰን መገለጹ ይታወሳል። የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ነጥቡ የሚቆረጠው በእንግሊዝኛ፣ በሂሳብ፣ የስኮላስቲክስ አፕቲትዩድ፣ ከተፈጥሮ ሳይንስ በፊዚክስ ፣ ከማህበራዊ ሳይንስ ደግሞ በጂኦግራፊ የትምህርት ዓይነቶች ነው።