ጠ/ሚ ዶ/ር አብይ በሱዳን እስር ቤቶች የነበሩ ኢትዮጵያዊንን በመያዝ በአዲስ አበባ ገቡ
ጠቅላይ ሚኒስር ዶክተር አብይ አህመድ በሱዳን እስር ላይ የነበሩ ኢትዮጰያዊያንን በመያዝ አዲስ አበባ ገቡ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሱዳን ተቃዋሚዎችና ወታደራዊ ሃይል በመሰረቱት የሽግግር መንግስት ዙሪያ የመጨረሻ የስምምነት ፈርማ ስነ ስርዓት አጠናቀው ሲመለሱ ነው ኢትዮጵያዊያኑን በመያዝ አዲስ አበባ የገቡት፡፡ኢትዮጵያኑ በተለያዩ ምክንያቶች በሱዳን እስር ቤቶች የነበሩ መሆናቸው ተነግሯል፡፡
በዛሬው ዕለት በተካሄደው የፊርማ ስነ ስርዓት በአዳራሹም ሆነ በጎዳናዎች የነበሩ ሱዳናዊያን ለኢትዮጵያና ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ ምስጋና ሲያቀርቡ ነበር፡፡የሱዳን የፓለቲካ ሀይሎች በደረሱት በስምምነቱ መሰረት የልዑላዊ ምክር ቤት የሚቋቋም ሲሆን ምክር ቤቱ ስድስት የሲቪል እና አምስት ወታዳዊ አመራሮችን በአባልነት ያካታል፡፡
የልዑላዊ ምክር ቤቱን ሁለቱ ወገኖች በየሶስት ዓመት እየተፈራረቁ የሚመሩት ሲሆን በዚህ መሰረት ለቀጣይ ሶስት ዓመታት የነፃነትና የለውጥ ሀይል ጠቅላይ ሚኒስትሩን የሚሾም ይሆናል፡፡በዚህ ስምምነት ላይ ደግሞ ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትሯ በኩል ከፍተኛ ሚና እንደነበራት የገለፀ ሲሆን ለዚህም ሱዳናዊያኑ ምስጋና አቅርበዋል::
(ኤፍ ቢ ሲ)