በአዲስ አበባ ኮልፌ ቀራንዮ ረጲ አካባቢ በተለምዶ ቆሼ ተብሎ በሚጠራው ቦታ በዛሬው ዕለት በደረሰ የቆሻሻ መደርመስ አደጋ የአንድ ሰው ህይዎት ማለፉ ተገለፀ።
አደጋውን ተከትሎ በአካባቢው በተደረገ ቁፋሮ አንድ የ70 ዓመት አዛውንት በህይወት ማውጣት ቢቻልም አለርት ሆስፒታል ከደረሱ በኋላ ህይወታቸው ማለፉ ተገልጿል።
አደጋው የደረሰው ቆሻሻ ከተጠራቀመበት አካባቢ ላይ ከተሰሩ የፕላስቲክ ቤቶች እና መንገድ ዳር በመሆኑ እስካሁን ጉዳት የደረሰባቸውን ሰዎች ቁጥር ማወቅ አልተቻለም።
አሁን ላይም የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች ቆሻሻው በተደረመሰበት አካባቢ የሰው ህይወት ለማዳን በኤክስካቫተር የታገዘ ቁፋሮ እያካሄዱ ይገኛሉ።
በአዲስ አበባ ኮልፌ ቀራንዮ ረጲ አካባቢ በተለምዶ ቆሼ ተብሎ በሚጠራው ቦታ ከሁለት ዓመት በፊት በደረሰ ተመሳሳይ አደጋ ከ100 በላይ ሰዎች መሞታቸው ይታወሳል።
FBC