የጉራጌ ተወላጆች ዝምታችን ይበቃል ሲሉ አደባባይ ለሰልፍ ወጥተዋል

አሥራት ቲቪ ልደታ ፍርድ ቤት ተገኝቶ ድምፃቸውን ለማሰማት ሲጥር እንዳይቀርፅ በፖሊስ ክልከላ ተደርጎበታል።

Image may contain: 6 people, people smiling, text

የጉራጌ ሕዝብ ለኢትዮጵያ አንድነት ቀናኢ ከሆኑት መካከል አንዱ ነው። አኩራፊውን ሁሉ የሚያባብለው የኢትዮጵያ ሚዲያና ፖለቲከኛ የጉራጌን ሕዝብ ልክ እንደ አማራው “ኢትዮጵያ! ኢትዮጵያ” እያለ እንዲዘምር እንጅ ጩኸቱ እንዲሰማ አይፈልጉም። ድምፅም አይሆኑለትም። ከአማራው ቀጥሎ ለበርካታ ጊዜ ድምፅ አልባ የሆነው የጉራጌ ሕዝብ ነው። የጉራጌ ሕዝብ ልክ እንደ አማራው ለኢትዮጵያ አንድነት ሲባል ሁሉንም መከራ ይቀበል ተብሎ የተፈረደበት ሕዝብ ነው። ችግር ሲደርስበት የሚጮህለት ግን የለም።

Image may contain: 5 people, outdoor and text

ይህ ዝምታ መቀጠል የለበትም ያሉ የጉራጌ ተወላጆች ሰሞኑን የሚዲያዎችን በር አንኳኩተዋል። ነገር ግን ቀና ምላሽ የሰጣቸው አላገኙም። በትናንትናው ሰልፋቸው የተገኘው አስራት ብቻ ነው። ጉራጌ ስለ ኢትዮጵያ እንዲዘምር ሲፈለግ፣ የስራ ባሕሉን ለመግለፅ በርካታ ሚዲያ ይገኙ ነበር። ከጉራጌ ሕዝብ ለመጋራት ሲባል እንጅ የጉራጌን ሕዝብ መከራ ለመጋራት ብቅ የሚል የለም። ትናንትም አይተነዋል።

Image may contain: 5 people, people standing and outdoor

አሥራት ቲቪ ልደታ ፍርድ ቤት ተገኝቶ ድምፃቸውን ለማሰማት ሲጥር እንዳይቀርፅ በፖሊስ ክልከላ ተደርጎበታል። ያም ሆኖ የቻለውን ለማስተላለፍ ጥሯል!

የጉራጌን ሕዝብ የምንፈልገው የስራ ባሕሉን ለመቅሰም፣ ስለ ኢትዮጵያ እንዲዘምር ብቻ አይደለም። መከራውን መጋራት፣ ጩኸቱን ማሰማትም ያስፈልጋል።