የቤተ ክርስቲያንን አስተዳደራዊ ለውጥ የማሰናከልና አንድነቷን የመጉዳት እንቅስቃሴዎችን ሕዝቡ አጥብቆ እንዲቃወም ማኅበረ ቅዱሳን ጥሪ አቀረበ

“ለመሪ ዕቅዱ ትግበራ ኹለንተናዊ አስተዋፅኦ ያደርጋል” /ሰብሳቢው አቶ ታምሩ ለጋ/ ~~~ በለውጡ ሽፋን ለግልና ለቡድን ጥቅም የሚደረግን የጎሠኝነት እንቅስቃሴ አጥብቆ ይቃወማል፤ የአባቶችን አንድነት የሚጎዱና ተልእኮዋን የሚያሰናክሉ ተግባራትን ይከታተላል፤ ያጋልጣል፤ ለቤተ ክርስቲያን አንድነት ሳይጨነቁ ፍላጎታቸውን ለማሳካት የሚሯሯጡትን እንቃወማቸው፤ በልዩነቶች ከመሽቀዳደም ይልቅ፣ለቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በማቅረብ መፍትሔ ይፈለግ፤ የተፈናቀሉ ወገኖችን ለመርዳት እና ወደተረጋጋ ሕይወት ለመመለስ ዜጎች ሊተጋገዙ …