ኢትዮቴሌኮም፣ ወደ መኖሪያ አካባቢያቸው የሚመለሱ የሐገር ውስጥ ተፈናቃዮችን ለማቋቋም የሚያስችል “6020” የተሰኘ የገቢ ማሰባሰቢያ የአጭር የፅሁፍ መልዕክት መስመር ይፋ ማድረጉን አስታውቋል፡፡ በመላ ሐገሪቱ ከቤት ንብረታቸው የተፈናቀሉ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችንን ለመርዳትም 40 ሚሊየን ብር መለገሱን ተመልክተናል፡፡